Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 19

2023-01-20 15:07:01
በኢትዮጲያ ከ 20 ሚሊዮን በላይ እንስሳት የሞት ስጋት ተጋርጦባቸዋል ተብሏል፡፡

ይህንን ያለው በአሜሪካው ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤይድ) ስር የሚገኘው ‹‹ፊውስ›› ተቋም ሲሆን ባለፈው የአውሮፓውያኑ 2021 እና 2022 ዘመን በኢትዮጲያ ከ 3 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ የቤት እንስሳት በድርቅ ምክንያት መሞታቸውን ገልጾ እስከ መጪው ሚያዚያ ወር ባሉት ጊዜያት ደግሞ ከ 20 ሚሊዮን በላይ እንስሳት የሞት ስጋት ተጋርጦባቸዋል ነው ያለው፡፡

የአየር ንብረት መዛባቱ ድርቁ የሚያስከትለው ጉዳት ለመባባሱ ዋነኛው ምክንያት ቢሆንም በተለይም የሰሜኑ ጦርነት በአፋር ክልል ላይ ያሳደረው ጫና ፣ እንዲሁም በኦሮምያና ደቡብ ክልሎች በተደጋጋሚ የሚከሰቱት ግጭቶች ለችግሩ አስቸኳይ ምላሽ በመስጠት ረገድ ተግዳሮት መሆናቸውንም ባወጣው ሪፖርት ገልጻል፡፡

አሃዱም ጉዳዩን አስመልክቶ የግብርና ሚኒስቴርን አነጋግሯል፡፡ በሚኒስቴሩ የእንስሳትና አሳ ሃብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪው ዶክተር ዮሃንስ ግርማ ‹‹በድርቅ ምክንያት የሞቱትን የቤት እንስሳት ጉዳይ በሚመለከት በየጊዜው ሪፖርት እንደምናወጣ ይታወቃል ፣ ስጋት ቢኖርም የተገለጸው አሃዝ ግን የተጋነነ ነው›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡

‹‹በየክልሉ ጉዳት የደረሰባቸውና የሞቱ እንስሳትን ቁጥር የተመለከተ ሪፖርት በየጊዜው ይፋ ስለምናደርግ አሁን ላይ በእኛ በኩል የተቀመጠ የአሃዝ መረጃ የለም›› ሲሉም አክለዋል፡፡

ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
2.2K views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 16:43:34
በቡርኪናፋሶ የሚንቀሳቀሱት የጂሃድ ሀይሎች በርካታ እንስቶችን አግተው መውሰዳቸው ተገልጿል፡፡
የቡርኪናፋሶ ባለስልጣናት በሰጡት ማብራሪያ በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የሚንቀሳቀሱት አሸባሪ የጂሃድ ሀይሎች በትንሹ 50 ሴቶችን አግተው መውሰዳቸውን አረጋግጠዋል፡፡
በቡርኪናፋሶ በተከሰተው እጅግ ከባድ የረሃብ አደጋ ልጆቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ለመመገብ በቅጠላቅጠልና ፍራፍሬ መሰብሰብ ስራ ላይ ከተሰማሩበት ጫካ በአሸባሪዎቹ የጂሃድ ሀይሎች ታፍነው በሁለት ጊዜ መውሰዳቸውም ነው የተገለጸው፡፡
ከዚያ የጂሃድ ሀይሎቹ እጅ ያመለጡ ጥቂት ሴቶች እየጮሁ የዱረሱልን ጥሪ በማሰማታቸው ህዝቡ ለድጋፍ ቢመጣም በጂሃድ ሀይሎቹ የታገቱትን ሴቶች ማስለቀቅ ቀርቶ የት እንዳደረሷቸው እንኳን ፍንጭ ለማግኘት ያለመቻላቸው ነው የተዘገበው፡፡
አሁን እነዚያ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሴቶች በጂሃድ ሀይሎቹ የታገቱባት ስፍራ አርቢንዳ በተደጋጋሚ በአሸባሪዎቹና በታጣቂዎቹ ሀይሎች ደም የሚፈስባትና ህይወት የሚቀጠፍባት ቦታ እንደሆነች ያስታወሰው የኮመን ስፔስ ዘገባ ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24
1.8K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 16:39:15
አሜሪካ በጀርመን ለዩክሬን ሀይሎች የምትሰጠውን ወታደራዊ ስልጣና ማጠናከሯ ተነግሯል፡፡
በአሜሪካ የጥምር ጦር አዛዡ ጀነራል ማርክ ሚሌይ በሰጡት ማብራሪያ የአሜሪካ መንግስት ሀይሎች በጀርመን ምድር ለዩክሬን ሀይሎች የሚሰጡትን ወታደራዊ ስልጠና ከእሁድ እለት ጀምረዋል ነው ያሉት፡፡
እንደ ጀነራል ማርክ ሚሌይ ማብራሪያ አሜሪካ በጀርመን ስልጠና የምትሰጣቸው ከአምስት መቶ በላይ የዩክሬን ጦር ሀይል አባላት ጥልቅ የሆነ ስልጣና ከወሰዱ በኃላ በቀጣዮቹ ከአምስት እስከ ስምንት ሳምንታት ድረስ ወደ ዩክሬን ተመልሰው የሩሲያ ጦር ሀይልን ይዋጋሉ ብለዋል፡፡
በጀርመን የወታደራዊ ማሰልጠኛ ለጉብኝት የተሰናዱት ጀነራል ማርክ ሚሌይ አሁን በጀርመን ምድር ስልጠና እየወሰዱ ያሉት ዩክሬናዊያን ወታደሮች ከበርካታ ምዕራባዊያን ሀገራት የተሰጠውን የጦር መሳሪያ እንዴት መጠቀም እንደልባቸውና የስነ ልቦና ግንባታም የተካተተበት እንደሆነ አስታዉቀዋል፡፡
ዘገባው፡-የኒውዮርክ ፖስት ነው
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24
1.7K views13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 16:36:34
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በደረሰ የእሳት አደጋ 1ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ ብር የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገለፀ፡፡
የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙ አቶ ንጋቱ ማሞ እንደገለፁት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታ አንበሳ ጋራጅ ጀርባ ባለስድስት ወለል ህንጻ በሆነዉ በስሪ ሳይ ኮሌጅ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 1 ሚሊየን 500 ሺህ ብር የተገመተ ንብረት የወደመ ሲሆን ሶስት መቶ ሚሊየን ብር የተገመተ ንብረት ግን ማዳን መቻሉን ገልፀዋል።
የእሳት አደጋዉ ሲደርስ በህንጻዉ ዉስጥ የነበሩ ሶስት ሰዎችን የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጉዳት ሳይደርስባቸዉ በመታደግ ከህንጻዉ ዉስጥ አዉጥተዋቸዋል ሲሉም አክለዋል።
የእሳት አደጋዉ የተነሳዉ ከ3ኛ ፎቅ ላይ እንደሆነና ወደ ሌሎች ወለሎች ሳይዛመት መቆጣጠር እንደተቻለም አብራርተዋል፡፡
የእሳት አደጋዉን ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር 1ሰዓት ከ23 ደቂቃ የፈጀ ሲሆን የአደጋዉ መንስኤ እየተጣራ እንደሚገኝም አቶ ንጋቱ ለአሀዱ ገልፀዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24
1.6K views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 16:31:05
የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ለነጋዴ የሚያስረክቡበትን ዋጋ እስከ ታህሳስ 27 ድረስ እንዲያሳውቁ ቢነገራቸውም እስካሁን ሊያሳውቁ አለመቻላቸው ተገለፀ፡፡
የሲሚንቶ ግብይት በነፃ ገበያ እንዲከናወን መወሰኑን ተከትሎ ፋብሪካዎች ለነጋዴዎች የሚያስረክቡበትን የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እስከ ታህሳስ 27 2015 ዓ.ም ድረስ እንዲያሳውቁ የተነገራቸው ቢሆንም እስካሁን እያሳወቁ እንዳልሆነ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ ቁምነገር እውነት ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡
ፋብሪካዎቹ ዋጋውን እንዲያሳውቁ የተፈለገው ገበያው ላይ የሚሸጥበትን መንገድ ለመቆጣጠር እንደሆነ ጠቅሰዉ ትክክለኛውን ዋጋ ማወቅ ካልተቻለ የግብይት ስርአቱ ለ-ህገወጥ አሰራሮች ምቹ እንዲሆን ሊያደርገው እንደሚችል ገልፀዋል፡፡
የመሸጫ ዋጋውን እንዲያሳውቁ አስገዳጅ መንገዶችን ከመጠቀም ይልቅ ከፋብሪካዎቹ አመራሮች ጋር እየተነጋገሩ እንደሚገኙ የገለጹት ወይዘሮ ቁምነገር በያዝነዉ ሳምንት መጨረሻ ድረስ እንዲያሳውቁ በማድረግ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ለህብረተሰቡ ይፋ እንደሚሆንም አስታውቀዋል፡፡
የሚያስረክቡበትን ዋጋ ላለማሳወቃቸው የተለያዩ ሰበቦችን እያቀረቡ እንደሚገኙ የተናገሩት ዳሬክተሯ አንደኛው ከሌላኛው ፋብሪካ ቀድሞ ማሳወቅ አለመፈለግ ዋነኛው ቢሆንም አሳማኝ በሆኑ ምክንያቶች ከማሳወቅ የዘገዩ እንዳሉም ጠቁመዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
1.6K views13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 16:29:01
የድሬዳዋን አከላለል በተመለከተ የቀረበውን ጥያቄ በተሳሳተ መንገድ መመልከት አይገባም ሲሉ የከተማዋ ተወካዮች ገለጹ፡፡
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ራሱን የቻለ ክልል እንዲሆን አሊያም ከኦሮምያ ክልል ወይም ሱማሌ ክልል ጋር እንዲጠቃለል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ጥያቄ የቀረበው ከተማ አስተዳደሩ የራሱ የሆነ በጀት ስለሌለው እንጂ የመሬት ማስፋፋት ጉዳይ አይደለም ሲሉ ነው ተወካዮቹ የገለጹት፡፡
አሃዱ ያነጋገራቸው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተወካይ አቶ አብዱጀዋድ ሞሃመድ ‹‹ሌሎች ክልሎች የሚያገኙትን ገቢ ከፌደራል መንግስቱ ጋር ሲካፈሉ ድሬዳዋ ከተማ በቻርተር የተዋቀረች ከተማ እንደመሆኗ፣ የራሷ ገቢ ስለሌላት ከሌሎች ክልሎች የምታመነጨውን ገቢ በቀጥታ ለፌደራል መንግስት ገቢ ታደርጋለች›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡
ይህ ደግሞ የከተማ መስተዳድሩ ለከፍተኛ የበጀት እጥረት እንዲዳረግ በልማትም ረገድ ከተማዋ ኋላ እንድትቀር አድርጓታል ብለዋል፡፡ ስለሆነም ይህንን በተሳሳተ መንገድ መመልከት አይገባም ነዉ ያሉት፡፡
የኢህአዴግ መንግስት ከተማዋ ከ1996ዓ.ም ጀምሮ በቻርተር በፌደራሉ መንግስት ስር እንድትደዳደር ያደረገ ሲሆን ይህም በወቅቱ ከኦሮምያና ሱማሌ ክልል በኩል ይነሳ የነበረውን የይገባኛል ጥያቄ ለማለዘብ በሚል የተወሰደ አማራጭ መሆኑ ይታወቃል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
1.6K views13:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 16:26:23
በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ኃይሎች ከመቼውም ጊዜ በላይ አሁን ህዝቡን ማድመጥ የሚጠበቅባቸዉ ጊዜ ላይ መሆናቸዉን አረጋጠዋል፡፡
የሰላም ስምምነቱ ያመጣውን ውጤት መሰረት በማድረግ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ወደ ክልሉ በማምራት ህዝቡ የሚገኝበትን ሁኔታ መረዳት አለባቸው ሲሉ ነው የፖለቲካ ኃይሎች የገለጹት፡፡
አሁን ህዝቡ እኛን ያድምጠን የምንልበት ጊዜ አለመሆኑን መገንዘብ ይኖርብናል ያሉት የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳዮች ም/ል ኃላፊው ተስፋዬ አለማየሁ ናቸው፡፡
ከዚህ ቀደም ባሉት ጊዚያት ለህዝቡ እኛ የፖለቲካ ኃይሎች ብዙ ተናግረን የፈታንለት ብዙም ችግር የለም ስለሆነም ከአሁን ወዲህ የህዝቡን እውነተኛ ስሜት ብቻ በማድመጥና ጦርነቱ ካስከተለው ጉዳት እንዲወጣ በማገዝ ጊዚያችንን ማሳለፍ ይጠበቅብናል ነዉ ያሉት፡፡
ይህንን ከማድረግ ውጭ በዚህ ስዓት እኔ እሻልሃለሁ የምንልበት ሞራል የለንም ሲሉም ገልጸዋል
በተጨማሪ የባይቶና ፓርቲ ም/ል ሊቀመንበር ክንፈ ገ/ዮሐንስ እንዳሉት የተጀመረው የሰላም ሂደት ዘላቂ እንዲሆን ሂደቱን ወደኋላ የሚጎትቱ ነገሮችን በማስወገድ መስራት እንደሚገባ ነው ያነሱት፡፡
በተጨማሪም በሁለቱም ወገኖች በደል ያደረሱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ ለማድረግ እንሰራለን ነዉ ያሉት፡፡
ይህን ማድረግ እስካልተቻለ ድረስ በዘላቂነት የህዝቡን ሰላም ማረጋገጥ አይቻልም ይህ እንዲሆን ደግሞ በሚገባን ልክ እንሰራለን ሲሉ አስታዉቀዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
1.8K views13:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 15:12:41
ሁለት ሚሊየን ኩንታል ስኳር ግዢው ተጠናቆ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተከሰተውን የስኳር እጥረት ለመቅረፍ እና ገበያውን ለማረጋጋት ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን በማስታወስ በዋነኝነት ያሉንን አማራጮች በመጠቅም ከውጭ ሃገራት ስኳርን ለማስገባት የተያዘዉን እቅድ በመተግበር ላይ መሆኑን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒቴር የህዝብ ግንኙነት ዳሬክተር ወ/ሮ ቁመነገር እውነት ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡
በተያዘው እቅድ መሰረት ሁለት ሚሊየን ኩንታል ስኳር ግዢው ተፈጽሞ የማጓጓዝ ሂደቱን ለማስጀመር በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኙ ለአሃዱ የገለጹት ዳሬክተሯ በቅርብ ጊዚያት ዉስጥ የተገዛዉ ስኳር ሙሉ ለሙሉ ወደ ሀገር ቤት እንደሚገባ አስታዉቀዋል፡፡
ከዚህ ቀደም የስኳር እጥረት በከፍተኛ ደረጃ እንዲከሰት ያደረገው የአምራች ፋብሪካዎች ብልሽት እና የጥሬ እቃ አቅርቦት ችግር መሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ቁምነገር ይሄን እና መሰል ችግሮችን በዘላቂነት አንዲቀረፍ እየተደረገ መሆኑን ተከትሎ ከውጭ ከምናስገባው ስኳር በተጨማሪ በቀጣይ በሃገር ውስጥም በከፍተኛ ሁኔታ ምርት ስለሚኖር ችግሩ ይቀንሳል ነዉ ያሉት፡፡
የስኳር እጥረት እና ውድነት በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደጋጋሚ ጊዜ ቅሬታ ከሚነሳባቸው መሰረታዊ ፍጆታዎች መካከል ዋነኛው እንደሆነ ይታወቃል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
1.2K views12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 15:10:11
የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ በሸቀጦች ላይ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለፀ፡፡

ከሰሞኑን በነዳጅ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉ ተከትሎም በሸቀጦች መሸጫ ዋጋ ላይ ተገቢ ያልሆነ ጭማሪ እያደረጉ የሚገኙ ነጋዴዎች እንዳሉ ተገልጻል።
በዚህ ላይ ምን እየሠራችሁ ነው ሲል አሐዱ ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ወይዘሮ ቁምነገር እውነት ጥያቄውን ያቀረበ ሲሆን በምላሻቸውም የነዳጅ ጭማሪውን ሰበብ በማደረግ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ዙሪያ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተካሄደ እንደሚገኝ አስታዉቀዋል፡፡
በነዳጅ ላይ የተደረገው ጭማሪ ምክንያት አድርጎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ ተቀባይነት እንደሌለው ገልፀው የንግዱ ማበረሰብም ከመሰል ተግባራት ሊቆጠብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዚህ ተግባር ላይ ተሰማርቶ የሚገኝ ማንኛውም አካል ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ የሚገኝ ሲሆን ህብረተሰቡም መሠል ተግባራትን በሚያስተውልበት ጊዜ ከማማረር ባለፈ ጥቆማዎችን በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
አክለውም ከቁጥጥር ስራው በተጨማሪ ከነዳጅ ጭማሪው በኋላ የገበያው ሁኔታ ምን እንደሚመስል የዳሰሳ ጥናት እየተካሄደ እንደሚገኝ ገልፀው በቀጣይ የጥናቱን ውጤት ተከትሎ በቁጥጥር ስራው ላይ ማሻሻያ እንደሚኖር አመላክተዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
1.1K views12:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 15:05:07
ያለባቸውን እዳ ለመክፈል ፍቃደኛ ያልሆኑ ከመቶ በላይ የጤና ተቋማት ጉዳያቸው በህግ መያዙን የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አስታወቀ፡፡

ከፍተኛ እዳ ያለባቸውን እና ለመክፍል ፍቃደኛ ያልሆኑ የጤና ተቋማት ቁጥራቸው ከመቶ በላይ እንደሆነ ጉዳያቸው በህግ መያዙን የተናገሩት የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ ናቸው፡፡
የጤና ተቋማት እዳቸውን በወቅቱ አለመክፈላቸው ተግዳሮት ቢሆንም የመድሀኒት አቅርቦት ላይ የውጪ ምንዛሬ እጥረት እንደማያጋጥማቸዉ አንስተዋል፡፡
የዉጭ ምንዛሬ የመድሀኒት አቅርቦት ላይ ጫና እንደሚያሳድር ስለሚታወቅ ቅድሚያ እንዲሰጠን ተደርጎ በአቅርቦቱ ላይ በውጪ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ምንም አይነት መስተጓጎል እንዳላጋጠመም አንስተዋል፡፡
ከብሄራዊ ባንክ ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ሆስፒታሎች በወቅቱ ክፍያቸውን ባለመክፈላቸው ምክንያት ከሌሎች ሀገራት በቢሊየን የሚቆጠር ገንዘብ የሚያወጣ የመድሀኒት ብድር ተወስዶ እንዳልተከፈለም ገልጸዋል፡፡
የውጪ ምንዛሬ እጥረት እንደ ሀገር የሚያሳድረው ጫና እንዳለ ሆኖ የአሰራር ክፍተቶችን በማሻሻል ለውጥ እንዲመጣ ለማድረግ በአቅርቦቱ ላይ ያለውን ችግር ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
995 views12:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ