Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 24

2022-12-29 11:39:15
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚገኙ ቅርሶች የሚገኙበትን ሁኔታ እንዲያጠና የተዋቀረው ቡድን ወደ ስራ ሊገባ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ያሉ ቅርሶች ያሉበትን ሁኔታ አጣርቶ ወደ ስራ መግባት የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር አጣሪ ቡድን ከዚህ ቀደም መዋቅሩን ያስታወሱት በቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ወይዘሮ ነዳች ጀማል፡፡
ቡድኑ ስፍራው ድረስ ሄዶ ሁኔታውን ለማየት የሚያስችለው ምቹ የጸጥታ ሁኔታ ባለመኖሩ ወደ ስራ መግባት ሳይችል መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡

የሰሜኑ ጦርነት በሰላም ስምምነቱ መሰረት መቆሙን ተከትሎ የጸጥታ ሁኔታው በጊዜ ሂደት በመሻሳሉ ለዚህ ተግባር የተዋቀረው ቡድን በአካባቢዎቹ ያሉ ቅርሶች ምን ያክል ጉዳት እንደደረሰባቸው እና አሁን ላይ ያሉበት ሁኔታን የማጣራት ስራውን እንደሚጀምር ገልጸዋል፡፡

ቅርሶቹ ያሉበትን ሁኔታ በመገምገም ወደ ስራ እንዲገቡ ለማስቻል ከተለያዩ ባለደርሻ አካላት ጋር እንደሚሰራም አክለዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.4K views08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 14:10:09
የታይዋን ደሴት ከቻይና የተቃጣባትን ወረራና ጥቃት ለመመከት የጦር ሀይሏን ለማጠናከር መወሰኗን አስታውቃለች፡፡

የታይዋን ደሴት ለዜጎቿ የአስገዳጅ የወትድርና አገልግሎት አዋጅ ማስነገሯ ነው የተሰማው፡፡
በዚያም መሰረት ከዚህ ቀደም ማንኛውም የታይዋን ዜጋ አስፈላጊውን የውትድርና ትምህርት ወስዶ ለአራት ወራት ወታደራዊ ግዳጅ ላይ መሰማራት እንዳለበት የሚደነግግ ህግ እንደነበረ ይታወሳል፡፡

አሁን ግን በታይዋን ደሴት ማንኛውም ዜጋ የወትድርና ስልጠና ተቀብሎ ለአንድ አመት በግዳጅ ላይ እንደሚሰማራ ህጉ ይገልጻል፡፡
የታይዋኗ ፕሬዝዳንት ፃይ ኢንግ ዌን ትናንት ከደሴቲቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወታደራዊ አዛዦች ጋር ከተወያዩ በኃላ በሰጡት ማብራሪያ ከእንግዲህ በኃላ በታይዋን ደሴት ዜጎች ዘንድ የአንድ ዓመት የወትድርና አገልግሎት ግዳጅ አሉ ብለዋል ሲል ዘገበው ዋሽንግተን ፖስት ነው፡፡


አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.2K views11:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 14:06:29
የናይጄሪያ ጦር ሀይል በቅርቡ በካሄደው አሰሳ ህይወታቸውን ስላጡት ንጹሃን ማጣራቱን ገልጿል፡፡

የናይጄሪያ ጦር ሀይል ባለፈው እሁድ በፈጸመው ከባድና የተቀናጀ የተባለለት የአየር ጥቃት ከ62 በላይ የናይጄሪያ ንጹሃን ዜጎች መገድላቸውን የናይጄሪያ ጦር ሀይል በካሄደው ምርመራ ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡
የናይጄሪያ አየር ሀይል ባለፈው የአውሮፓውያኑ ታህሳስ 18/2022 በሙቱምጂ ማህበረሰብ ላይ በፈጸመው ከባድ ድብደባ የንጹሃን ዜጎች እልቂት ማጋጠሙንም ነው ያስታ ወቀው፡፡

የናይጄሪያ አየር ሀይል በዚያ የዛምፋራ ግዛት ከህዝቡ ጋር መሳ ለመሳ በሆኑት ሺፍቶችና አሸባሪዎችን ለመምታት በወሰደው እርምጃ የንጹሃን ሞት እንዳሳዘነው የሀገሪቱ ጦር ሀይል አስታውቋል፡፡

ዘገባው፡-የኢስት አፍሪካን ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.8K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 13:58:10
በኮሌራ በሽታ ሳቢያ የሚከሰተው ሞት ምጣኔ 3 ነጥብ 4 በመቶ መድረሱ ተገለጸ፡፡

ወረርሽኙ ከነሐሴ 21 ቀን 2014ዓ.ም ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ባሌ፤ ጉጂ እና ምዕራብ አርሲ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ 9 ወረዳዎች እንዲሁም በሶማሌ ክልል ሊበን ዞን በሚገኙ 2 ወረዳዎች መከሰቱን የገለጹት በኢትዮጲያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ መስፍን ወሰን ናቸው፡፡

በሁለቱ ክልሎች እስካሁን በአጠቃላይ ለ 25 ሰዎች ህልፈት ምክንያት ሆኗል ያሉት ዳይሬክተሩ በወረርሽኙ 3 ነጥብ 4 በመቶ የሞት ምጣኔ ተመዝግቧልም ብለዋል፡፡

ወረርሽኙን ለማከም የሚያስችሉ 13 ጊዜያዊ የኮሌራ ህክምና መስጫ ማእከላት መዘጋጀታቸውን የገለጹት አቶ መስፍን ከዚህም በተጨማሪ ስር ነቀል ስራ ለመስራት የሚያስችል የተለያዩ አጋር ድርጅቶችን ያካተተ የ8 አመት የኮሌራ መቆጣጠሪያ ሰነድ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል፡፡


እቅዱ በኮሌራ ምክንያት የሚከሰተውን የሞት ምጣኔ 90 በመቶ ለመቀነስ ያለመ ሲሆን በሃገር አቀፍ ደረጃ 118 ወረዳዎች በዕቅዱ ውስጥ ተካተዋል ነው ያሉት፡፡

በዚህ ሂደት ውስጥ በእነዚህ ወረዳዎች ውስጥ የሚኖሩ ከ15 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉም አክለዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.4K views10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 13:57:16
በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከህዳር ወር አጋማሽ ጀምሮ በ7 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ተገለጸ፡፡
በዓለማቀፍ ደረጃ ዳግም ስጋትነቱ እየጨመረ የመጣው የኮሮና ባይረስ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ ውስጥም በዚህ ወረርሽኝ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን በጤና ሚኒስቴር የብሄራዊ ኮቪድ ግብረሀይል አስተባባሪ ዶክተር መብራቱ ማሴቦ ለአሀዱ ገልጸዋል፡፡
እንደ አስተባባሪው ገላጻ ከሆነ ላለፉት ሰባት ወራት በወረርሽኙ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከ1 በመቶ በላይ ያልገፋ እንደነበር እና ከህዳር ወር አጋማሽ ጀምሮ በወረርሽኙ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተናገረዋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥም የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ዳግም እያንሰራራ እናዳለ የሚሳዩ ሁኔታዎች መኖራቸውን ገለጸው ለዚህም እንደማሳያ የሚጠቅሱት በዚህ ምክንያት የሚታመሙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑና ወረርሽኙም እያገረሸ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በዚህ ሰአት ጭማሪ ያሳየው የኮቪድ ወረርሽኝ ብቻ ሳይሆን ኢንፍሉዌንዛ እና ሌላ ከጉንፋንገራ ተመሳሳይ የሆነ ቫይረስ አብረው ጭማሪ ማሳየታቸውን አክለዋል፡፡
እነዚህ ወረርሽኞች ኢትዮጵያ ውስጥ መኖራቸው እና እየጨመሩ እንደሚገኙ በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት መረጋገጡንም ዶክተር መብራቱ ገልጸዋል፡፡
ህብረተሰቡ እነዚህ ወረርሽኞች እየጨመሩ መምጣታችን ተገንዝቦየመከላከያ መንገዶቹን በአግባቡ በመጠቀም መከላከል እንዳለበት ገልጸዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
2.2K views10:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 13:48:27
ከሰላም ስምምነቱ በኋላ በሁለት ዙር 17 ሚሊዮን ብር የሚገመት የሰብአዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ ክልል መላኩን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አስታወቀ፡፡

በፌድራል መንግስቱ እና በህዉሀት መካከል የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ በሁለት ዙሮች ወደ 17 ሚሊዮን ብር የሚገመት የሰብአዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ የተላከ ሲሆን አንዱን በሽሬ በኩል አንዱ ደግሞ በመቀሌ በኩል መላኩን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሰብአዊ ዲፕሎማሲ እና የኮምንኬሽን አገልግሎት ሀላፊ አቶ መስፍን ደረጄ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

የሰብአዊ እርዳታዉ ቀጣይነት ያለዉ መሆኑን ገልፀዉ ህብረተሰቡን በማስተባበር እና ፕሮጀክቶችን በመንደፍ ቀጣይነት ያለዉ ድጋፍ ለማድረግ እየሰሩ መሆኑን አስታዉቀዋል፡፡
ሰብአዊነት የሚሰማዉ ድጋፍ ማድረግ የሚችል ማንኛዉም ዜጋ በ9400 አጭር የፅሁፍ መልዕክት እና በየአካባቢዉ ባሉ የቀይ መስቀል ቅርንጫፎች ድጋፍ ማድረግ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን "በበይነ መረብ" በሚሰሩ የተለያዩ አማራጮች መጠቀም እንደሚችሉ አስታዉቀዋል፡፡
አለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት እያሳዩ በመሆናቸዉ ድጋፉን እንዲያደርጉ በመነጋገር ላይ መሆናቸዉን ገልፀዋል፡፡
ሰብአዊ እርዳታዉን በማድረግ ህይወት የማዳን ስራዉ በተቻለ መጠን እንደሚቀጥል አቶ መስፍን አክለዉ ተናግረዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.2K viewsedited  10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 13:47:18
የህወሀት ቡድን አሸባሪነቱ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሳይፋቅለት በአፈ ጉባኤ የተመራ ሁነት መከናወኑ አግባብ እንዳልሆነ ተገልጿል፡፡

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ የተመራ ልኡክ ወደ በመቀሌ ተጉዞ እንደነበር ይታወቃል ይህም የሁለቱን ወገኖች ስምምነት መሰረት አድርጎ የተካሄደ ነዉ፡፡

ነገር ግን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የተለያዩ ምሁራን በተለያዩ አጋጣሚዎች ቀድሞ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግና ደንብን ባከበረ መልኩ አሸባሪነቱ እንዲነሳ መደረግ ነበረበት ሲሉ እንደነበረ የህግ ባለሙያዉ አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ገልፀዋል፡፡

ስለሆነም ስምምነቱ ከታመነበትና ወደ ስራ ከተገባ ሽብርተኝነቱ ሊፋቅለት ይገባል ይህም ሰላሙን ዘላቂ ያደርገዋል ነዉ የሚሉት፡፡

ሌላኛዉ ህግ ባለሙያ አቶ ይልቃል ሀሳቤ በበኩላቸዉ ከስነ ስርአት ህግ አንፃር ሲታይ መቅደም የነበረበት ይህ የተወካዮች ምክር ቤት ፈረጃን ማንሳት ነበር ያሉ ሲሆን ነገር ግን ላለመነሳቱ ምክንያት የጠራ ፖለቲካዊ አካሂድ ባለመኖሩ ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡

አሀዱ ያነጋገራቸዉ ህግ ባለሙያዎች እንዳጋሩን በየትኛዉም አቅጣጫ ሲታይ ለዘላቂ ሰላምና መሬት የወረደ እንዲሁም ስር የሰደደ መተማመን እንዲኖር ፍረጃዉ መነሳት እንዳለበት ነዉ ፤ ነገር ግን በሙስጥ ያሉ ፖለቲካዊ አካሂዶች ለዚህ እንደምክንያትነት ቢቀመጡም በህጉ በኩል ግን ቅድሚያ መነሳት እንዳለበት ያሳያል ብለዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
2.6K viewsedited  10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 11:29:18
በሱዳን በተፈጠረ ግጭት የበርካታ ሰዎች ህይወት መቀጠፉ ተነግሯል፡፡

በሱዳን ዳርፉር ግዛት በተፈጠረው ከባድ ግጭት 11 ሰዎች ሲሞቱ ከ20 በላይ ሌሎች ሰዎች ክፉኛ መቁሰላቸው ነው የተሰማው፡፡
ግጭቱ የተጀመረው በአረብ የከብት አርቢዎችና በአናሳዎቹ የዲጁ ማህበረሰብ እንዲሁም በሌሎች የአረብ ዝርያ ባልሆኑት ጉሳዎች መካከል ከረቡ ጀምሮ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የግጭቱ ስፍራ ደግሞ ከደቡብ ሱዳኗ ዳርፉር ግዛት ዋና ከተማ በ20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደሆነ የዓይን እማኞች አስታውቀዋል፡፡
ይሁንና የግጭቱ መንስኤ ምን እንደሆነ ገና በመጣራት ላይ መሆኑን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

በዳርፉር ግዛት የበጎ አድራጎት ተቋም የስደተኞችና የተፈናቃዮች ጉዳይ ቃል አቀባይ አዳም ሬጋል በሰጡት ማብራሪያ የሟቾቹ ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ ይችላል ሲሉ ለሱዳኑ የዜና ተቋም ሱና ተናግረዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.7K viewsedited  08:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 11:24:44
በአልሸባብ ሀይሎች ተይዘው የነበሩ በርካታ ኢራናዊያን መለቀቃቸው ተነግሯል፡፡

በአልሸባብ አሸባሪ ሀይሎች ተይዘው የነበሩ 14 ኢራናዊያን ዓሳ አጥማጆች መለቀቃቸውን ታዉቋል፡፡
ኢራናዊያኑ ዓሳ አጥማጆች በአልሸባብ አሸባሪ ሀይሎች እጅ የገቡት በሶማሊያ አቅራቢያ በሚገኘው ዓለማቀፉ የውሃ ክልል መሆኑንም ነው ዘገባው ያብራራው፡፡

ዓሳ አጥማጆች ከአልሸባብ አሸባሪዎች እጅ የተለቀቁት በኢራን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፤ በኬንያ የኢራን ተወካይና በሶማሊያ መንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም በሶማሊያ የጎሳ መሪዎችና ታላላቅ ሰዎች ጋር በተደረገ የረዥም ጊዜ ድርድር በኃላ መሆኑ ነው የተሰማው፡፡

ዓሳ አጥማጆች በሰላም ወደ እናት ምድራቸው ኢራን መመለስን አስመልክቶ በኢማም ኮሚኔይ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ልዩ የአቀባበል ዝግጅት በክብር መሰናዳቱን የዘገበው ኢየሩሳሌም ፖስት ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.4K views08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 11:18:04
በሙስና የተገኘን ሀብት ለህዝብ የሚጠቅሙ ስራዎች ላይ እንዲውል መባሉ ወንጀልን የሚያበረታታ እንደሆነ ተገለፀ፡፡

በሙስና እና በሌሎች ወንጀሎች የተገኙ ገንዘቦችን ለልማት ጉዳዮች እንዲውሉ መፍቀድ ህጋዊነት የሌለው እንዲሁም ወንጀለኞችን በተግባራቸው እንዲቀጥሉ የሚያበረታታ ከመሆኑም ባለፈ ህብረተሰቡ በህግ ላይ ያለውን መተማማን የሚሸረሽር ተግባር እንደሆነ የህግ ባለሙያው አቶ ነብዩ ምክሩ አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም በሀገሪቱ ህግ መሰረት በህገ ወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እንዲሁም ለሌሎች ማናቸውም ተግባራት ማዋል በወንጀል የሚያስጠይቅ እንደሆነ የተደነገገ ነዉ ያሉት አቶ ነብዩ አሁን ላይ በሙስና ገንዘብ የሰበሰቡ ሰዎች ገንዘባቸውን ልማታዊ በሆኑ ስራዎች ላይ እንዲያውሉት መጠየቁ የወንጀል ህጉን የሚፃረር እንደሆነም ገልፀዋል፡፡

ሌላኛው አሀዱ ያነጋገራቸው የህግ ባለሙያ አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ መልእክቱ ወንጀልን ህጋዊ እንደማድረግ የሚቆጠር እንደሆነ እና አስቀድሞ ለአገር እና ለህዝብ ጥቅም የሚሰጡ ስራዎችን የመስራት ፍላጎት እና ሀሳብ ያለው ሰው የሀገርን ሀብት የመዝረፍ ስራ ላይ አይሰማራም ነበር ያሉ ሲሆን አሁንም የዘረፉትን ሀብት ለበጎ አላማ ያውሉታል ተብሎ እንደማይጠበቅ አመላክተዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.2K views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ