Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 25

2022-12-27 11:13:35
ከ 4 አመት ጀምሮ ላሉ ህጻናት ዲጂታል መታወቂያን ለመስጠት መታቀዱ ተገልጻል፡፡

የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት የዲጂታል መታወቂያ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ባደረገው ውይይት በአዲሱ ረቂቅ ውስጥ የህጻናትን መታወቂያ የማግኘት መብት የሚያረጋግጥ ክፍል መካተቱንም ገልጾ በዚህም ህጻናት በአንድ አካባቢ ተወልደው ወደ ሌላ አካባቢ በሚዘዋወሩበት ጊዜ ማንነታቸው እንዲታወቅ መብት እንዳላቸውም ነው የጠቆመው፡፡

የጽህፈት ቤቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዮዳሄ ዘሚካኤል እንዳሉት ‹‹ህጻን የሚባለው በየትኛው የእድሜ ክልል ያለ ነው›› የሚለው ጥያቄ በተደጋጋሚ እንደሚነሳ በመጥቀስ ከ4 አመት ጀምሮ ያሉና የጣት አሻራቸው የማይነበብ ህጻናትን የሚመለከት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ይህም ህጻናት ከወላጆቻቸው ጋርም ሆነ በተቋማት ውስጥ ሆነው ማንነታቸው እንዲታወቅ የሚደረግበት አሰራር መዘርጋቱ ለህጻናቱ አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን ጨምሮ መብቶቻቸው የሚከበሩበትን ሁኔታ ያመቻቻልም ነው ያሉት፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.0K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 11:10:04
የታላቁ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ ግንባታ 88 በመቶ መድረሱ ተገልጻል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ብሄራዊ ምክር ቤት ፅህፈት ቤት የሚዲያ ኮምኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሀይሉ አብረሃ ለአሀዱ እንደገለፁት ግንባታዉ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በፍፁም ተነሳሽነት ሲከናወን እንደነበር በማስታወስ አሁንም ካለምንም መዘናጋት የግንባታዉ ሂደት እየተፋጠነ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እየተከናወነ ነዉ ብለዋል፡፡
አሁን ባለዉ መረጃ መሰረትም አጠቃላይ የህዳሴ ግድብ የግንባታ ደረጃ 88 በመቶ መድረሱን ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

የግንባታ ሂደቱ በዚህ ደረጃ እንዲደርስ የሆነበት ዋና ምክንያት የመላዉ ኢትዮጲያዉያን አንድነትና የጋራ ጥረት እንዲሁም ድጋፍ ነዉ ያሉት አቶ ሀይሉ አሁንም ይህ ጥንካሬ ሊዘነጋ አይገባም ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.3K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 12:20:25
ዩክሬን በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት አዳዲስ ኤምባሲዎችን ለመክፈት መሰናዳቷ አስታውቃለች፡፡

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በሰጡት ማብራሪያ ዩክሬን አዳዲስ ኤምባሲዎቿ የምትከፍትባቸው አስሩ የአፍሪካ ሀገራት መለየታቸውን ገልጸዋል፡፡

ዩክሬን በአፍሪካ አስር ሀገራት አዲስ የምትከፍታቸው ኤምባሲዎቿ ከቀጣዩ የአውሮፓውያኑ 2023 አዲስ ዓመት ጀምሮ ስራ እንደሚጀምሩ ነው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ያስታወቁት፡፡

እንደ ዘለንስኪ ዝርዝር ማብራሪያ ዩክሬን በአፍሪካ አህጉር አዲስ ከምትከፍታቸው ኤምባሲዎቿ ውጪም በሰላሳ የአፍሪካ ሀገራት ቋሚ ተወካዮች ይኖሯታል ነው ያሉት፡፡

ፕሬዝዳንቱ አክለውም የዓለማቀፋዊ እድገትን ማምጣት የሚቻለው አንድኛው ሀገር ከሌሎቹ ሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነትን በማጠናከር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዘገባው፡ ኢንተር ፋክስ ዩክሬን ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.8K viewsedited  09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 12:19:32
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ለአሜሪካ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፡፡

የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋንግ ዩ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚንስተር አንቶኒ ብሊንከን ጋር በነበራቸው የስልክ ውይይት አሜሪካ በቻይና የውስጥ ጉዳይ ያላትን ጣልቃ ገብነት እንድታቆም አሳስበዋል፡፡

የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ዋንግ ዩ እንዳሉት አሜሪካ የቻይና እድገት ትጨቁናለች ዋሽንግተንም ከዚህ ግብሯ ቶሎ መሰብሰብ አለባት ነው ያሉት፡፡
ዋንግ በማብራሪያቸው አሜሪካ አሁን የቻይናን ቀይ መስመር እያለፈች ነው ሱሉ ገልጸዋል፡፡

የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺዢን ፒንግና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በባለፈው የባሊ የቡድን 20 አባል ሀገራት ጉባኤ ላይ ተገናኝተው መነጋገራቸው ይታወቃል፡፡
ዘገባው፡-የአልጄዚራ ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.5K viewsedited  09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 12:17:42
የፖለቲካ አመራሮች እና የሃይማኖት አስተማሪዎች የሃሰተኛ መረጃ እና የጥላቻ ንግግር ህጉን ሲጥሱ ያለው ተጠያቂነት ላይ ውስንነት እንዳለበት ተገለፀ፡፡
የሀሰተኛ መረጃ እና የጥላቻ ንግግርን ለመከላከል የወጣው አዋጅ ከጸደቀ 3 አመት ቢያስቆጥርም በሚፈለገው ልክ ተግባራዊ አልሆነም፡፡
በተለይም ደግሞ የህዝብ ተቀባይነት ያላቸው ሰዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች እንዲሁም የሀይማኖት መሪዎች በሀሰተኛ መረጃ እና የጥላቻ ንግግር በሚያደርጉበት ጊዜ ሊከሰት የሚችለው ጥፋት ከፍ ያለ እንደመሆኑ መጠን በህጉ መሰረት ከሌላው ከፍ ያለ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ቢታወቅም ተግባራዊ ሲሆን እንደማታይ የህግ ባለሙያው አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ለአሀዱ ገልጸዋል፡፡
አክለውም በህጉ መሰረትም ከሌሎች በተለየ እስከ 5 አመት እስር እና የገንዘብ ቅጣት እንደሚያስቀጣቸውም አመላክተዋል፡፡

ሌላኛው አሀዱ ያነጋገራቸው የህግ ባለሙያ አቶ ካሳሁን ሙላቱ ተጽእኖ ፈጣሪ አልያም ተደማጭነት ያላቸው ሰዎች የጥላቻ ንግግር አልያም ሀሰተኛ መረጃዎችን በሚያስተላልፉበት ጊዜ መልእክቱ ብዛት ላላቸው ሰዎች እንዲዳረስ ከማድረጉም ባለፈ መረጃውን እንዲሁም የጥላቻ ንግግሩን ተከትሎ የሚፈጠረውን ችግር የከፋ እንደሚያደርገው ያስረዳሉ፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.1K viewsedited  09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 12:10:37
ከ20 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን የዋግ ኽምራ ዞን ገለፀ።

የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ ከተፈናቀሉ 92 ሺህ ወገኖች ውስጥ 29 ሺህ የሚሆኑት አካባቢዎቻቸው በመረጋጋታቸው ወደ ቀድሞ የመኖሪያ ቀያቸው መመለሳቸውን የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞን የአደጋ መከላከልና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ቢሮ ኃላፊ ዝናሽ ወርቁ ለአሃዱ ተናግረዋል።

ነገር ግን ካለው የእርዳታ ውስንነት አኳያ የተፈናቃዮቹ ወደ ቀያቸው መመለስ መልካም ጅምር ቢሆንም ከሄዱ በኋላ የሚቋቋሙበት ሁኔታ አለመመቻቸቱን ገልፀዋል።

በመንግስት በኩል የሚደረገው የማቋቋሚያ ድጋፍ ካለው ውስንነት አንፃር እየቀነሰ መጥቷል ያሉት ኃላፊዋ በሌሎች ዓለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች የሚደረግበት ደግሞ ምግብ ነክና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎች ብቻ በመሆናቸው ከመሸኘት ባለፈ የምናደርግላቸው ነገር የለም ነው ያሉት።

የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ ከዞኑ በተለይም አበርገሌና ሌሎችም ወረዳዎች ከ90 ሺህ በላይ ወገኖች የተፈናቀሉ ሲሆን ከነዚህም መካከል ወደ 29 ሺህ የሚሆኑት ወደ ቀያቸው ተመልሰዋል ተብሏል።
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.0K viewsedited  09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 12:06:54
በኢትዮጵያ እየተበራከተ የመጣውን ግጭት ለመከላከል የሰብዓዊ ድፕሎማሲ አካዳሚ ከፍቶ ሥልጠና ለመስጠት ማሰቡን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አስታወቀ፡፡

ከቅርብ አመታት ወዲህ እየተበራከተ የመጣዉን ግጭት ለመከላከል የሰብዓዊ ዲፕሎማሲ አካዳሚ በመከፈት ስልጠናዎችን ለመስጠት መታቀዱን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሰብአዊ ዲፕሎማሲ እና የኮምንኬሽን አገልግሎት ሀላፊ አቶ መስፍን ደረጄ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

ከራስ አልፎ ለሌሎች መኖር፣መተሳሰብና ሰብዓዊነት የሀገራችን ባህል እንዲሆን የአካዳሚው መቋቋም ወሳኝ መሆኑን ገልፀዉ ግጭቶች ሲፈጠሩ ከሚደረገዉ የሰብአዊ እርዳታ ባሻገር የአስተሳሰብ ለዉጥ ላይ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አስታዉቀዋል፡፡
አካዳሚዉ ምን አይነት ትምህርቶችን መስጠት እንዳለበት የሚረዱ ጥናቶች እየተሰደረጉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚከሰቱ ችግሮች እየተበራከቱ መምጣት አንዱ ምክንያት የግንዛቤ እጥረት በመሆኑ መልካም ልቦችን ለማብዛት በበጎ ፈቃድ ላይ ትኩረቱን ያደረገ አካዳሚ መመስረቱ ችግሩን ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

የሰብዓዊነት ትምህርት ቤት ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ችግር ለማዉጣት እንደሚጠቕም አቶ መስፍን አክለዉ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.3K viewsedited  09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-24 13:23:10
የሩዋንዳ ጦር ሀይል የዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎን ድንበር አልፎ መግባቱ ተነግሯል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገለልተኛ አካላት በሰጡት ማብራሪያ የርዋንዳ ጦር የኮንጎን ድንበር አልፎ መግባቱን ተከትሎ በኮንጎ ዴሞክራሲዊ ሪፐብሊክ መንግስት ዘንድ ግራ መጋባት ተፈጥሯል ነው የሚባለው፡፡

እንደ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገለልተኛ አጣሪዎች ማብራሪያ የርዋንዳ መንግስት በትክክል ለኮንጎ አማፅያን ሀይሎች ማርች 23 ወይም ኤም 23 ድጋፍ ያደርጋል ነው የተባለው፡፡

የርዋንዳ መንግስት ለኤም 23 አማፅያን ከሚሰጠው ድጋፍ በዋናነት የጦር መሳሪያና ጥይት እንዲሁም የአልባሳትና ስንቅ ተጠቃሾቹ መሆናቸዉን ዘገባዉ ያስረዳል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ይህንን ሪፖርት ያወጣው ደግሞ የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት የኤም 23 አማፅያን ሀይሎች በርዋንዳ መንግስት ድጋፍ ያገኛሉ እያለ ተደጋጋሚ ክስ በሚያቀርብበት ወቅት ነው፡፡
ዘገባው፡-የፍራንስ 24 ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24 #Ahadu #News
1.8K views10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-24 13:17:14
በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት የተከሰተው አስከፊ ድርቅና ያስከተለው ረሃብ ለሚሊዮኖች የሞት አደጋ መጋረጡ ታዉቋል፡፡

በመንግስታቱ ድርጅት የህፃናት መረጃ ተቋም ዩኒሴፍ ባወጣው መግለጫ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ባሉ ሀገራት በተለይም በሶማሊያ፤ በኢትዮጵያ፤ በኬንያ ከሁለት ሚሊየን በላይ ህፃናት ከባለፉት አምስት ወራት ወዲህ በከፋ ሰቆቃ ውስጥ መግባታቸውን አስታውቋል፡፡
በመላው የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በዚህ ወቅት ከ20 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ህጻናት ደግሞ በከፋ የረሃብ የውሃ ጥምና የህመም ሰቆቃ ውስጥ መሆናቸውንም ነው ዩኒሴፍ የገለፀው፡፡

ባለፈው ሀምሌ ወር ባወጣው መረጃ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ሀገራት ከአየር ንብረት ለውጡ ጫና ከጦርነትና ከዓለማቀፉ የሰላም ምስቅልቅል በተለይም በሩሲያና በዩክሬን መካከል በተከሰተው ጦርነት የጥራጥሬ ምርት መቋረጡን ተከትሎ በአፍሪካ ቀንድ ባለዉ ሁኔታ ችግር ውስጥ የገቡት ሰዎች ቁጥር አስር ሚሊየን እንደነበረ ይታወቃል ሲል የዘገበው ኦል አፍሪካ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24 #Ahadu #News
1.6K views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-24 13:03:48
ሀገራዊ የምክክር ኮምሽኑ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ማድረጉ የገለልተኝነቱ ጥያቄ እንደማያስነሳበት ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እና የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሥምምነት ስለመፈራረማቸው ተገልጿል፡፡

ሀገራዊ የምክክር ኮምሽኑ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ስምምነት ማድረጉ ገለልተኝነቱን ጥያቄ ውስጥ አይከተውም ወይ ሲል አሀዱ ጠይቋል፡፡

ምላሽ የሰጡት የኮምሽኑ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ምክትል ኮሚሽነር ዶክተር ዬናስ አዳዬ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የተለያየ አመለካካት፤ ሀይማኖት እና ባህል ያላቸው ዜጎች የሚገኙበት መሆኑ ከወገንተኝነት ይልቅ ገለልተኝነትን የሚያመላክት ነው ብለዋል፡፡

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሀገር በቀል እውቀቶች፤ የምርምር ስራዎች የሚገኝባቸው እንደ መሆኑ ማንኛውም የፖለቲካ አመለካከት አይኖርም ሲሉም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከእውቀት ማዕከልነታቸው ጋር ተያይዞ አስፈላጊ እገዛዎችን እንዲያደርጉ ለማስቻል እና በትምህርት ተቋማቱ ያሉትን ቁሳቁሶች ለሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ለመጠቀም እድልን መፍጠርም አንዱ እቅድ መሆኑን አንስተዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24 #Ahadu #News
1.6K views10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ