Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 26

2022-12-24 12:54:08
በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ የወጣት ማእከላት ለወጣቶች ምቹ አይደሉም ተባለ፡፡
ለወጣቶች ተብለው የተገነቡ የወጣት ማእከላት መካከል አብዛኞቹ ከታለመላቸው አላማ ውጪ እየዋሉ እንደሚገኙ እና ለወጣቶቹ ምቹ አይደሉም የሚሉ ቅሬታዎች ይቀርባሉ፡፡
አዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ተቀዳሚ ፕሬዘዳንት አቶ ተከስተ አያሌው ችግሮቹ በአብዛኛዉ በወጣት ማእከላት የሚስተዋል እንደሆነ ገልጸው ለወጣቶች ምቹ ካለመሆናቸው በተጨማሪም በሚፈለገው ልክ ለታለመላቸው አላማ አለመዋላቸው ወጣቶች አልባሌ ቦታዎችን እንዲመርጡ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል እንደሆነ አስታዉቀዋል፡፡
አብዛኛዎቹ ማእከላት የተገነቡባቸው ቦታዎች ከመንገድ ገባ ያሉ ከመሆናቸው በተጨማሪም እየተዳደሩበት ያለዉ መንገድ ወጣቶቹ አገልግሎቱን ፈልገው እንዳይመጡ እየገፋቸው እንደሚገኝም አመላክተዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24 #Ahadu #News
1.5K views09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-24 12:35:58
የተመዘገበ የሀብት መጠንን ለህዝብ ይፋ ለማድረግ ህጉ እንደማይፈቅድ ተገለጸ፡፡

የፌደራል የስነ ምግባር እና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በባለስጣናት እና በመንግሥት ሠራተኞች ላይ እያከናወነ ያለው የሀብት ምዝገባ መረጃ ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ በርካታ ዜጎች እና ተቋማት ሲጠይቁ የነበረ ሲሆን አሀዱም የተመዘገበን ሀበት ለምን ለህዝብ ይፋ እንደማያደረግ የፌደራል የስነ ምግባር እና የፀረ ሙስና ኮሚሽንን ጠይቋል፡፡

የሀብት ምዝገባ እና ማሳወቅ አዋጅ 668 ህዝባር 2002 ላይ በተደነገገዉ መሰረት የተመዘገበን ሀብት ማየት ለሚፈልግ የትኛዉም ሰዉ መጥቶ የሚጠይቅ ከሆነ ህጉ በሚፈቅደዉ አሰራር መሰረት እንደሚያስተናግድ ሆኖም ግን የተመዘገበን ሀብት ለሁሉም ህዝብ ይፋ ማደረግን ህጉ እንደሚከለክል የፌድራል የስነ ምግባር እና የፀረ ሙስና ኮሚሽን የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋዬ ሻሜቦ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

ኮሚሽኑ የተመዘገበን ሀብት በህጋዊ መንገድ ለሚጠይቁ አካላት የማሳየት ስራን እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የተመዘገበን ሀብት ትክክል ነዉ አይደለም የሚለዉን ለመለየት የሚፈለጉ ዜጎች በህጋዊ መልኩ የሚጠይቁ ከሆነ እና ተመዘገበዉ ሀብት እዉነተኛ አለመሆኑን የሚጠቁሙበት አጋጣሚ ካለ የሀብቱን አንድ አራተኛ እንዲያገኙ እንደሚደረግ አስታዉቀዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
1.8K viewsedited  09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 14:03:30
ሩሲያ የወታደራዊ ቴክኖሎጂዎቿን ለኢራን ለማስተላለፍ አቅዳለች ስትል እንግሊዝ ከሳለች፡፡

የእንግሊዝ የመከላከያ ሚንስትር በሰጡት ማብራሪያ ሩሲያና ኢራን በከፍተኛ ደረጃ የጦር መሳሪያ ግዢና ስያጭ እንዲሁም ልውውጥ ይዘዋል ነው ያሉት፡፡
እንደ ብሪታንያ መንግስት ሩሲያ በዩክሬን በገባችበት ጦርነት ከአንድ መቶ ሺህ በላይ ወታደሮቿን ማጣቷ ይነገራል፡፡

የብሪታንያው የመከላከያ ሚንስትር ቤንዋላስ በሰጡት ዝርዝር ማብራሪያ ሩሲያ ለኢራን የተራቀቁ የጦር መሳሪያ ቴክኖሎጂዎቿን ለማስተላለፍ አልማ ሌት ተቀን እየሰራች ስለመሆኑ ጥርጥር የለንም ብለዋል፡፡

መላው ዓለም ማወቅ ያለበት ሩሲያና ኢራን ያሰሉት ቀመር ሁሌም ቢሆን የመከካለኛውን ምስራቅ ለማተራመስ ነው ሲሉ በጽኑ አስጠንቅቀዋል፡፡
ዋላስ በማጠቃለያቸውም ኢራን በዩክሬን ጦርነት ለሩሲያ የጦር መሳሪያ ድጋፍ በመስጠቷ ኃላፊነቱን ትወስዳለች ነው ያሉት፡፡

ዘገባውው፡- የዘ ታይምስ ኦፍ እስራኤል ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.8K views11:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 12:16:26
የርዋንዳ መንግስት በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ላይ ክስ መስርቷል፡፡
በቅርቡ የኮንጎ አማፅያን ማርች 23 ወይም ኤም 23 በመባል የሚታወቁት በፈፀሙት ጥቃት 131 ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም ሳይቀር ባደረገው ማጣሪያ ማረጋገጡ ይታወቃል፡፡

የኪንሻሳ መንግስም በዚያ ጥቃት ለተገደሉት በርካታ ንጹሃን እልቂት የጎረቤት ርዋንዳ መንግስት በዋናነት ለአማጽያኑ ድጋፍ እየሰጠ የከፋ ወንጀል ተፈጽሟል በሚል ክስ ማቅረቡም ይታወሳል፡፡
ይሁንና የርዋንዳ መንግስት የዚያን የኮንጎ መንግስት ክስ ከእውነት የራቀ በሚል አጣጥሎታል ተብሏል፡፡

የርዋንዳ መንግስት ለኮንጎ አማጽያን የኤም 23 ሀይሎች ብርቱ ድጋፍ ሰጥቷል የሚለውን ሀሳብ አሜሪካ፤ ፈረንሳይ፤ ቤልጂየምና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መርማሪ ሙያተኞች በትክክል ማረጋገጣቸውን የዘገበው ኔሽን ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.9K viewsedited  09:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 12:06:24
የሕፃናት መብትን ከማስጠበቅ አንፃር በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደነገገውን ሕግ የማስፈጸም ክፍተት መኖሩን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የሕፃናት መብትን ከማስጠበቅ አንፃር በዓለማቀፍ ደረጃ የተደነገገውን ሕግ የማስፈጸም ክፍተት በመኖሩ ሕጉን ለማስፈጸም ትምህርት የመስጠትና ሌሎች መሰል ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸዉን በሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት እና የኮምንኬሽን ቡድን መሪ አቶ መላኩ ባዩ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

የሕግ ማዕቀፉ የአፈጻጸም ችግር በመኖሩ አፈጻጸሙን ለማሻሻል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዉ ችግሩ በአንድ ተቋም ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ ከተለያዩ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
በተለይም በሰሜን ኢትዮጵያና በተለያዩ ክፍሎች በተካሄዱ ግጭቶች ሴቶች እና ሕፃናት ተጠቂ መሆናቸውን አስታዉቀዋል፡፡

በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ተገደው የተደፈሩ ሴቶች እና ሕፃናትን በተመለከተ ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ሰፊ ጥናት እያደረገ መሆኑን አቶ መላኩ አክለዉ ተናግረዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.6K viewsedited  09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 12:02:12
በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለመከሰስ መብት ያላቸው ሰዎች ላይ የተፈጸሙ እስሮች ህጋዊ መሰረት የሌላቸው እንደሆኑ ተገለጸ፡፡
ፍርድ ቤት ነጻ ያለውን ፖሊስ በድጋሚ የሚያስርበት ሁኔታ እየተስተዋለ እና በአጠቃላይ አሁን ለሚታዩ ችግሮች የሰሜኑ ክፍል ጦርነትን በምክንያትነት መጥቀስ ተገቢ ነው ወይ የሚል ጥያቄ በትላንተናዉ እለት በአሀዱ መድረክ ተነስቷል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የፍትህ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት እና የኮምንኬሽን ጉዳዮዎች ዳይሬክተር አቶ አወል ሱልጣ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የነበረው ጦርነት በሌሎች ስራዎች ላይ እንቅፋት ቢሆንም ሙሉ ለሙሉ ሌሎች ስራዎችን መስራት እንዳንችል አድርጎናል ማለት አያስደፍርም ብለዋል፡፡
2014ዓ.ም በሰሜኑ ክፍል ከነበረው ጦርነት ውጪ ከ24 ሺ በላይ የሚሆኑ ወንጀለኞችን ማስቀጣት እንደተቻለ እና ከ15ሺ በላይ መዛግብቶች በላይ ውሳኔ እንደተሰጠባቸውም ገልጸዋል፡፡
የፖሊስ ፤ፍርድ ቤቶች እንዲሁም የፍህት ሚኒስቴር ቅንጅታዊ ስራን በተመለከተ እርምት ለመውሰድ ስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል፡፡
የፓርላማ አባላት፤ዳኞች ሌሎችንም ጨምሮ ያለመከሰስ መብት ያላቸው ሰዎች እጅ ከፍንጅ ወንጀል ሲፈጽሙ ካልተያዙ በቀር በቁጥጥር ስር እንደማይውሉም ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.5K views09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 11:49:46
ከሰንደቅ አለማ ጋር በተያያዘ የተፈጠረው ችግር እርማት እንዲወሰድበት ለመንግስት ማሳሰቢያ መስጠቱን የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
በአሐዱ መድረክ ላይ ተገኝተው ምላሽ የሰጡት በህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የህግ እና የይግባኝ ምርመራ አማካሪ ዳይሬክተር አቶ ደነቀ ሻንቆ በየክልሎቹ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችን በመክፈት በአስፈጻሚ አካላት የሚፈጸሙ የአስተዳደር በደሎች እንዲታረሙ የማድረግ የማይተረሙ ከሆነ ደግሞ ለህዝብ ተወካዮዎች ምክር ቤት በማሳወቅ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የዲሞክራሲ ተቋማት ሲቋቋሙ ገለልተኛ እና ነጸ ናቸው ቢባልም አመራሮች ግን ከፖለቲካ ወገንተኛ ነጻ ናቸው ማለት እንደማይቻል የጠቀሱት ዳሬክተሩ አሁን ላይ ግን ተቋሙ ነጻ ሆኖ እየሰራ ነው ፤ የገለልተኝት ጉዳይ ከህሊና እና ከአመለካከት ጋር የሚያያዝ ነው ብለዋል፡፡
ከሰንደቅ አለማ ጋር በተያያዘም የግጭት መነሻ መሆን ስለሌለበት እና አስቀድሞ ግንዛቤ ለማህበረሰብ መፈጠር ስለሚያስፈልግ መንግስት እርማት እንዲወስድበት ስለጉዳዩ ዝርዝር ማብራሪያ የያዘ መግለጫ ማሳሰቢያ መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡
ማህበረሰቡ በመንግስት ተቋማት ፍትሀዊ የሆነ አገልግሎት እያገኘ ባለመሆኑ ማስተካከል እንደሚያስፈልግ የተናገሩት አቶ ደነቀ ጥናት በማድረግም ለመንግስት እንደቀረበም አስታዉቀዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.4K views08:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 11:20:08
ብሄራዊ የክፍያ ስርዓት ማሻሻያው የውጪ ባለሃብቶችን ተሳታፊ በማድረግ ረገድ ሚናው የጎላ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የብሄራዊ ክፍያ ስርአት ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን ያጸደቀ ሲሆን የረቂቅ ማሻሻያው በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳታፊ በማድረግ የተዳከመውን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ያለመ እንደሆነ የገለጹት የኢትዮጲያ ብሄራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ ናቸው፡፡
አዋጁ ሙሉ በሙሉ የባንክ ስራን ተክቶ የማይሰራ በመሆኑ ከባንክ ውጪ ያሉ የክፍያ ስርአቶች የውጪ ዜጎችና ባለሃብቶችን እንዲያሳትፉ ያግዛል ያሉት የባንኩ ገዢ የፋይናንስ ዘርፉ እንዲያንሰራራ በማድረግ ረገድ የጎላ አስተዋጽኦ እንዳለውም ገልጸዋል፡፡
የብሔራዊ የክፍያ ሥርዓት አዋጅ ከዘመኑ የክፍያ ሥርዓት ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ ባለመ መልኩ ማሻሻያ እንደተደረገበት የተገለጸ ሲሆን በረቂቅ አዋጁ የሰነድ መዋዕለ ንዋይ ግምጃ ቤትን የማቋቋም፣ የውጭ ሀገር ዜጎች በዘርፉ የኢትዮጵያን ገበያ የሚቀላቀሉበትን አግባብ እንዲሁም፣ ዓለማቀፍ መርሆዎች ተፈፃሚ የሚሆኑበትን አግባብ የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ አዳዲስ ድንጋጌዎች እና ማሻሻያዎች መካተታቸውም ተገልጿል፡፡
አዋጁ በስራ ላይ ከዋለ 10 አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን አሁን ላይም አዋጁ ማሻሻያ ተደርጎበት ወደ ስራ እንዲገባ ከውሳኔ ተደርሷል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.3K views08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 17:18:29
በአሐዱ ሬድዮ 94.3 ጋዜጠኞች የተዘጋጀው "ኢትዮጵያ የተቃርኖ ሙክራብ የመቀራመት ወይስ የማዳን ተልዕኮ" መፅሃፍ የፊታችን ታህሳስ 22/2015 ዓ.ም በብሔራዊ ትያትር አዳራሽ ይመረቃል።
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24 #Ahadu #News
1.3K viewsedited  14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 14:44:25
ሊቢያ በበርካታ ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ ውሳኔ አስተላልፋለች፡፡
አሁን የሞት ፍርድ ውሳኔ የተሰጠባቸው ሊቢያውያን ቁጥር 17 ሲሆን ሰዎቹ በዋናነት 55 ሰዎችን ገድለዋል በሚል በማስረጃ የተረጋገጠ ሰነድ ስለተገኘባቸው ነው ተብሏል፡፡
የትሪፖሊ የወንጀለኞች መቅጫ ከፍተኛው ፍርድ ቤት በበኩሉ በሰጠው ማብራሪያ የሞት ፍርድ ከተወሰነባቸው 17 ሰዎች በተጨማሪ 2 ደግሞ የእድሜ ልክ የእስራት ፍርድ እንደተወሰነባቸው ገልጿል፡፡
በሊቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸውና የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደባቸው ግለሰቦች ከአሸባሪው የአይ ኤስ ሀይሎች ጋር ግንባር ፈጥረው በሰሜናዊ የሊቢያ ከተማ ሳብራታ የተቀናጀ ጥቃት ፈፅመዋል በሚል ነው፡፡
ዘገባው፡-የዘ ናሽናል ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24 #Ahadu #News
2.3K views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ