Get Mystery Box with random crypto!

AfandishaHarar 🇪🇷🇪🇹🇯🇴🇸🇩🇪🇭🇸🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ afandishaharar — AfandishaHarar 🇪🇷🇪🇹🇯🇴🇸🇩🇪🇭🇸🇴 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ afandishaharar — AfandishaHarar 🇪🇷🇪🇹🇯🇴🇸🇩🇪🇭🇸🇴
የሰርጥ አድራሻ: @afandishaharar
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.31K
የሰርጥ መግለጫ

Spreading Ethnographic and Historical Truth.

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 22:53:19
ራጂሽ ኻና ይኸውና።
538 views19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 22:52:28 ራጂሽ ኻናን በጨረፍታ
-------
አፈንዲ ሙተቂ
--------
አሁን በሕይወት የለም። በሕይወት ሳለ የህንድ ሲኒማን በዓለም ዙሪያ ካስተዋወቁት ዓለም አቀፍ አክተሮች አንዱ ነበረ። በተለይም በ70ዎቹ እና በ80ዎቹ ኮከብ የህንድ አክተር የነበረው እርሱ ነው። ታዋቂዎቹ አክተሮች አሚታብ ባችቻን እና ሚቱን ቻክራቦርቲ እንደ እርሱ የሚያደንቁት የሲኒማ ጥበበኛ አልነበረም። በመሆኑም ተመልካች ለመሳብ ሲሉ በፊልሞቻቸው ጣልቃ ተጋባዥ ተዋናይ (guest star) አድርገው ያስገቡታል።

ራጂሽ ኻና የታዋቂዋ አክትረስ እና ሞዴሊስት የዲምፕል ካፓዲያ ባለቤት ነበር። ከባለቤቱ ጋር ለአስር ዓመት ከኖረ በኋላ ትዳራቸው በ1984 በፍቺ ተጠናቅቋል። ሁለቱ አክተሮች ሁለት ሴት ልጆችን ያፈሩ ሲሆን ልጆቹም እንደ ወላጆቻቸው አክተሮች ናቸው።
------
ራጂሽ ኻና በዘመኑ በኢትዮጵያ እና በኤርትራም ዝነኛ ሆኖ ነበር። የኛ ታላላቆች እርሱን የሚያስታውሱት "Haathi Meri Saathi" በተሰኘ ፊልሙ ነው (ብዙዎች ርእሱን በአማርኛ ተርጉመው "ዝሆን ጓደኛዬ" ይሉታል)። የኔ ትውልድ አባላት ራጂሽ ኻናን በደንብ የምናስታውሰው ግን "Disco Dancer" በተሰኘው ፊልም ውስጥ የጂሚ አጎትና አሰልጣኝ ሆኖ በታየባቸው ሁለት ትዕይንቶች ሳቢያ ነው።

ታዲያ በOnline በነበረኝ ቆይታ እንደታዘብኩት ከኤርትራዊያንና ከኢትዮጵያዊያን መካከል ራጂሽ ኻናን በደንብ የሚወዱትና የሚያደንቁት የአስመራ እና የድሬ ዳዋ ልጆች ናቸው። በፌስቡክ ገጼ ላይ ስለሚቱን እና አሚታብ ስጽፍ በውስጥ መስመር እየመጡ "እስቲ ስለ ራጂሽ ኻና አንድ ነገር በል" ይሉኛል።
------
ራጂሽ ኻና እንደ አሚታብ፣ ዳርሜንድራ፣ ጄንተንድራ እና ሚቱን ቻክራቦርቲ የአክሽን ፊልሞችን ብዙም አይነካካም። ፊልሞቹ በአብዛኛው "drama" ናቸው። ደግሞም እስከ መጨረሻው ድረስ ስሜትን የመቆጣጠር ሀይል አላቸው። ይህንን ጽሑፍ የጻፍኩት "Swarg" የሚባል ፊልሙን በማየት ላይ ሳለሁ ስሜቴ ፍንቅል ብሎ በመውጣቱ ነው። ከእርሱ ፊልሞች መካከል ብዙዎቹ በጅምሩ ላይ ትራጀዲ ሆነው ሰውን ካስለቀሱ በኋላ በአፈጻጸም ላይ postive ትዕይንት ያስከትሉና የደስታ ስሜትን በመላው የሰውነት አካል ይረጫሉ።

Anand የተሰኘው ፊልሙ ግን ከጅምሩ እስከ መጨረሻው በትራጄዲ ነው የሚያልቀው። ራጂሽ ኻና በዚያ ፊልም የዓመቱ ኮከብ አክተር ተብሎ ተሸልሞበታል። ፊልሙ የካንሰር በሽተኛ ሆኖ ዕለተ ሞቱን በደስታ ስለሚጠባበቅ ወጣት ነው የሚተርከው። በፊልሙ ውስጥ ሁለት ተጻራሪ ስሜቶች ይንጸባረቃሉ። በአንድ በኩል እርሱን የሚከታተለው ዶክተር፣ መምህሩ፣ ዘመዶቹ፣ ጎረቤቶቹ፣ የስራ ባልደረቦቹ ወዘተ.. ወጣቱ Anand በቅርቡ የሚሞት መሆኑ አሳዝኖአቸው ይተክዛሉ። ያለቅሳሉ። በሌላ በኩል ግን Anand "በቅርቡ መሞቴ የማይቀር እንደሆነ ተረጋግጧል። እርሱን የማስቆምበት ሃይል የለኝም። ቢሆንም እስክሞት ድረስ ለምን በሃሳብና በሰቀቀን ራሴን አሰቃያለሁ? በቀረችኝ ጊዜ በደንብ ተደስቼ መሞት አለብኝ" እያለ ከማንም ጋር ሲቃለድና ሲጫወት ይውላል (BBC የዛሬ አስር ዓመት ገደማ "እስከ ዛሬ የተሰሩት ምርጥ 100 የህንድ ፊልሞች" በማለት ባካሄደው ምርጫ ራጂሽ ኻና የተወነበትን Anand በአምስተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጦታል)።
------
ራጂሽ ኻና በአጭሩ እንዲህ ነበር። እስቲ Wi-Fi ካላችሁ በእረፍት ጊዜያችሁ እነዚህን ፊልሞች በYouTube ተመልከቷቸው። እነዚህን ፊልሞች ካያችኋቸው በኋላ "የህንድ ፊልሞች ዕድገት ወደ ኋላ እየሄደ ነው" የምትሉ ይመስለኛል።

Anand
Avtaar
Amrit
Nazrana
Swarg
------
ሰላም እንሁን!
ሰላም ለሀገራችንና ለህዝባችን!
ሰላም በመላው ዓለም ይስፈን!!
------
አፈንዲ ሙተቂ
ነሐሴ 24/2014
557 views19:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 19:43:26
September 1/1961
------
One of the landmark dates in History of Eritrea.
-----
እንቋዕ አብጽሓኩም። እንቋዕ አብጽሓና።
1.0K views16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 23:08:13 "አሚር ሆይ! አንተ "ኸይሩን" ብቻ አስብ፤ “ለሸሩ” ባለቤት አለውና!!"
-----
ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
----
እነሆ የሀረር ተረት ልናካፍላችሁ ነው፡፡ ተረቱን ያጫወቱን የረጅም ጊዜ ጎረቤታችን የነበሩት አቶ ዑመሬ አብዱልቃዲር ናቸው፡፡ እኚህ ሰው ዛሬ በህይወት የሉም፡፡ አላህ ጀንነት እንዲወፍቃቸው እየተመኘን ተረቱን እንደወረደ እንጽፍላችኋለን (“እኛ” እንዲህ የምንላችሁ “እኛ” መሆናችንን እያስታወሳችሁ)፡፡
------
በጥንት ዘመን አንድ ቅን ሰውዬ በሀረር ከተማ ይኖር ነበር፡፡ ይህ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት፡፡ የመጀመሪያው ልጁ ርህሩህና የዋህ የነበረ ሲሆን ሁለተኛው ልጁ ግን ተንኮል እየፈጠረ ሰዎችን ማሞኘትና መሳቅ ይወድ ነበረ፡፡ አባትዬው ትንሹን ልጅ ቢመክረው አልሰማ እያለ አስቸገረው፡፡ ስለዚህ በትንሹ ልጅ ተስፋ የቆረጠው አባት ዘወትር ትልቁን ልጅ እየጠራው “ልጄ ሆይ! አንተ ደጉን ብቻ አስብ፡፡ ለተንኮል ባለቤት አለውና” የሚል ምክር ይሰጠው ነበር፡፡ አባት በዚህም ሳያበቃ ለትልቁ ልጅ “ዓሊ ኸይሮ” (ቅን አሳቢው ዓሊ) የሚል ቅጽል አወጣለት፡፡ ትንሽየውን ግን “ዓሊ ሸርሮ” (ተንኮለኛው ዓሊ) በማለት ሰየመው፡፡

ከጊዜ በኋላ አባት የአዱኛውን ዓለም ተሰናበተ፡፡ በዚህም የተነሳ ልጆቹ ተቸገሩ፡፡ ኑሮ በጣም ከበዳቸው፡፡ በመሆኑም ወደ ሀረሩ አሚር ሄደው በችግር መቆራመዳቸውን ነገሩት፡፡ አሚሩ በአጋጣሚ የቤተ መንግሥት ከብቶችን የሚጠብቅ ሰው ይፈልግ ነበርና ወንድማማቾቹ ለእረኝነት እንዲቀጠሩ ጠየቃቸው፡፡ ወንድማማቾቹ ለስራው የሚሰጣቸውን ምንዳ ሲጠይቁት ከሚበሉት ምግብና ከሚለብሱት ልብስ በተጨማሪ በዓመቱ መጨረሻ ላይ አንዲት ጊደር እንደሚያገኙ አሳወቃቸው፡፡ ወንድማማቾቹም ከአሚሩ የቀረበላቸውን ጥያቄ በደስታ ተቀበሉትና ስራቸውን ጀመሩ፡፡

ወንድማማቾቹ በመቶዎች የሚቆጠሩትን የአሚሩን ከብቶች “አው-ሓኪም”፣ “አቦከር” እና “ሸድዳ ዋ መድዳ” ወደሚባሉት ተራሮች እያሰማሩ በትጋት ማገዱን ተያያዙት፡፡ ስራቸውን በደህና ሁኔታ እያከናወኑ ዓመቱን አገባደዱት፡፡ የዓመቱ መጨረሻ እየተቃረበ ሲመጣ ግን የ“አሊ ሸርሮ” ልብ በግለኝነት መመታት ጀመረች፡፡ ለምንዳ የምትሰጣቸውን ጊደር ጉዳይ ሲያስብ አዕምሮው በስስት ተወጠረ፡፡ በመሆኑም “ወንድሜን ገድዬው ጊደሪቱን የግሌ ማድረግ አለብኝ” በማለት ወሰነ፡፡ እቅዱንም በአው ሓኪም ተራራ ላይ ለመፈጸም ቆረጠ፡፡

ወንድማማቾቹ ከብቶቹን ወደ “ሓኪም” ተራራ በወሰዱበት በአንደኛው ቀን “አሊ ሸርሮ” ለወንድሙ “አንተ ከዚህ ሆነህ ከብቶቹን ጠብቅ፤ እኔ ተራራው ላይ ወጥቼ ለምለም ሳር እንዳለ ልይና ልመስ” አለው፡፡ “አሊ ኸይሮ”ም በቀረበለት ሃሳብ ተስማምቶ ከብቶቹን ለብቻው መጠበቅ ጀመረ፡፡ “አሊ ሸርሮ” ከተራራው ላይ እንደ ወጣ ትልቅ ድንጋይ አንቀሳቅሶ ወንድሙ ወዳለበት አቅጣጫ ቁልቁል ለቀቀው፡፡ ድንጋዩ ከተራራው ላይ እየተንከባለለ ወረደ፡፡ ከ“አሊ ኸይሮ” አጠገብ ሲደርስ ግን ወደ ወርቅነት ተቀየረ፡፡ “አሊ ኸይሮ” በዚህ ተአምር ተገረመ፡፡ “ወደ ወርቅነት የተቀየረው ድንጋይ እኔና ወንድሜ ሀብታም እንድንሆን ዘንድ ከአላህ የተሰጠን ነው” በማለት በደስታ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ የተፈጠረውንም ተአምር ለወንድሙ ለመንገር በጉጉት ይጠባበቅ ጀመር፡፡
“አሊ ሸርሮ” በበኩሉ “አሊ ኸይሮ በድንጋይ በመገደሉ “ጊደሪቱ የኔ ብቸኛ ሀብት ትሆናለች” እያለ በደስታ ከተራራው ወረደ፡፡ ወንድሙ ወደነበረበት ቦታ ሲደርስ ግን ያልጠበቀውን ነገር አየ፡፡ “ይህ ወርቅ ከየት ነው የመጣው?” በማለትም ወንድሙን ጠየቀው፡፡ አሊ ኸይሮም “አንድ ትልቅ ድንጋይ ከተራራው ላይ እየተንከባለለ መጥቶ እኔ ጋ ሲደርስ ይህንን ወርቅ ሆነ” በማለት መለሰለት፡፡ “አሊ ሸርሮም “ድንጋዩ የተንከባለለው ከስሩ የነበረውን ለምለም ሳር ለማየት ብዬ ስላንቀሳቀስኩት ነው፤ እዚህ ደርሶ ወደ ወርቅ ከተቀየረ እኔም የራሴ ወርቅ ሊኖረኝ ይገባል፡፡ ስለዚህ አንተም በተራህ ወደ ተራራው ውጣና ሌላ ድንጋይ አንከባልልኝ” አለው፡፡

“አሊ ኸይሮ”ም ከወንድሙ የሰማውን ሳይጠራጠር ወደ ተራራው ወጥቶ ትልቅ ድንጋይ አነሳና “አሊ ሸርሮ” ወደነበረበት አቅጣጫ አንከባለለው፡፡ ይሁንና ድንጋዩ ወደ ወርቅነት ሳይቀየር “አሊ ሸርሮ”ን ጭፍልቅ አድርጎ ገደለው፡፡ “አሊ ኸይሮ” ከተራራው ወርዶ ወንድሙ ወደነበረበት ስፍራ ሲሄድ ወንድሙ ሞቶ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም ደነገጠ፡፡ ወደ ሀረሩ አሚር ሄዶም የተከሰተውን ሁሉ አንድ በአንድ ነገረው፡፡ ሆኖም አሚሩ ሊያምነው አልቻለም፡፡ “ወንድምህን ራስህ ነህ የገደልከው” በማለትም ከሰሰው፡፡ በመሆኑም “ነፍስ ያጠፋ ሰው ይገደል” በሚለው የሀረር ከተማ ጥንታዊ ህግ መሰረት በድንጋይ ተጨፍልቆ እንዲሞት ተፈረደበት፡፡

“አሊ ኸይሮ”ም ፍርዱ ሊፈጸምበት ወደ “ሐኪም” ተራራ ግርጌ ተወሰደ፡፡ ከተራራው ላይ ትልቅ ድንጋይ ተንዶ ቁልቁል ተወረወረበት፡፡ ይሁንና ድንጋዩ “አሊ ኸይሮ” አጠገብ ሲደርስ እንደገና ወርቅ ሆኖ ቁጭ አለ፡፡ የቅጣቱን አፈጻጻም ለማየት በስፍራው ተሰብስቦ የነበረው የሀረር ህዝብም በተፈጠረው ነገር በጣም ተገረመ፡፡ “ይህ ተአምር ልጁ ወንድሙን እንዳልገደለ በሐቅ ይመሰክራል” በማለትም ደመደመ፡፡ የሀረሩ አሚር በበኩሉ “የዓሊ ኸይሮ”ን ተአምር ሲያይ “በህይወቴ ስፈልገው የነበረውን ሐቀኛ ሰው ዛሬ አገኘሁት” የሚል ቃል ተናገረ፡፡ “አሊ ኸይሮ”ንም የዙፋኑ ወራሽ በማድረግ ሾመው፡፡
-----
ወደ ሀረርጌ ከመጣችሁ “Amiroo! Kheyruma yaadi, Sharriin abbuma eeydii” የሚል አባባል ትሰማላችሁ፡፡ “አሚር ሆይ! አንተ ኸይሩን ብቻ አስብ፤ ለሸርሩ ባለቤት አለውና” እንደማለት ነው፡፡ ከአባባሉ ጀርባ ብዙ ታሪኮች ይነገራሉ፡፡ ከነዚያ ታሪኮች መካከል አንዱ ከላይ የቀረበው ተረት ነው፡፡

በተረቱ እንደተገለጸው ተንኮለኛ ሰው በለስ የቀናው መስሎት ብዙ የሸር ትብታቦችን ሊተበትብ ይችላል፡፡ ይሁንና እንደዚህ ዓይነቱ ሰው አጓጉል ሆኖ ነው የሚቀረው፡፡ የማታ ማታ ራሱ በሸረበው የተንኮል ድር መታሰሩ የማይቀር ነው፡፡ ስለዚህ በህይወት እያለ ደግ ደጉን ብቻ አስብ!! ለተንኮሉ ባለቤት አለውና!!
በድጋሚ Amiroo kheyruma yaadi, Sharriin abuma eeydi ብለናል፡፡
----
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 11/2007
በሀረር ከተማ ተጻፈ።
1.8K views20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 22:58:09 "ብሄር" እና "ብሄረሰብ" እና ፖለቲካችን
---
አፈንዲ ሙተቂ
---
ብሄር ( Nation)

ብሄር ማለት ተለይቶ በሚታወቅ የጂኦግራፊ ክልል የሚኖር፣ የራሱ ቋንቋ ያለው፣ ተወላጆቹ በዘር ሀረግ (geneology) የሚገናኙ፣ የተለየ ባህልና ማህበራዊ አወቃቀር ያለው፣ ተወላጆቹ በኢኮኖሚ ስምሪታቸው የሚመሳሰሉ፣ የተወላጆቹ ስነ ልቦናዊ ባህሪ የሚመሳሰል፣ የራሱ መነሻው እና ታሪካዊ ጉዞ ያለው የሰዎች ስብስብ ማለት ነው። አንድ ብሄር በተለያየ ነገድና ጎሳ ሊከፋፈል ይችላል (ኦሮሞ፣ ሶማሊ፣ ዙሉ፣ ሃውሳ ወዘተ)። የጎሳና የነገድ ክፍፍል የሌለውም ሊሆን ይችላል (አማራ፣ ትግራይ፣ ፋርሲ፣ ካታላን)።
--
ብሄረሰብ (Nationality)

ብሄረሰብ በብዛቱ ከብሄር የሚያንስ እና በተለያዩ ክልሎች በሚኖሩት ቡድኖቹ መካከል በቋንቋ እና በባህል ብዙ የመለያየት ባህሪ የማይታይበት የሰዎች ስብስብ ማለት ነው (ለምሳሌ የአንድ ብሄር አባላት ቋንቋቸውን በተለያየ dialect ሊናገሩት ይችላሉ። የሀረር ኦሮምኛ ዘይቤ፣ የወለጋ ኦሮምኛ ዘይቤ፣ የሸዋ ኦሮምኛ ዘይቤ ወዘተ። የአንድ ብሄረሰብ አባላት ግን ቋንቋቸውን በተመሳሳይ dialect ነው የሚናገሩት። ለምሳሌ ሀረሪ፣ ሀላባ፣ ስልጢ)

ሁለቱ የእንግሊዝኛ ቃላትን በትክክለኛ መልኩ የሚገልፁ የአማርኛ ቃላት የሉም። "ብሄር" እና "ብሄረሰብ" በ1966 በፈነዳው አብዮት ማግስት ነው የተፈጠሩት (ልክ እንደ አብዮት፣ ህረተሰብአዊነት፣ ተራማጅ፣ አድሃሪ፣ ወዘተ ማለት ነው)። ሌሎች ቋንቋዎች ግን እነርሱን የሚተኩ ቃላት አሏቸው (ኦሮምኛ፣ አረብኛ፣ ሀረሪ፣ ሶማሊ ወዘተ)።
-----
ይህንን ፍቺ ያገኘሁት ከAmerican Heritage Dictionary ነው።
----
ጎሳ በእንግሊዝኛ Clan ነው የሚባለው። ነገድ ደግሞ tribe ነው የሚባለው።

ደግሞ "ዘውግ" እና "ዘውገኝነት" የሚሉ አባባሎች በቅርቡ ተፈጥረዋል። ይህንን አጠራር ያመጣው አንዳርጋቸው ጽጌ ነው (በ1997 ባሳተመው "ነፃነትን የማያውቅ ነፃ አውጪ" በተሰኘ መጽሐፉ)። ይህም የብሄር ፖለቲካን እያጥላላ የአሃዳዊነትን ቅቡልነት ለማስረፅ የዘየደበት መላ ነው።
----
በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የብሄርና የብሄረሰብ ፖለቲካ ነው እንጂ የጎሳ ፖለቲካ አይደለም። ፖለቲካው በዚህ መንፈስ የተቃኘው በኢትዮጵያ ከባድ የሆነ የብሄር ጭቆና ይካሄድ ስለነበረ ነው። አሁን ያለው ፌዴራሊዝምም የብሄርና ብሄረሰብ ፌዴራሊዝም ነው።

"የብሄር ፖለቲካ እና የብሄር ፌዴራሊዝም ለኢትዮጵያ ያስፈልጋታል ወይስ አያስፈልግም?" ብሎ መከራከር አንድ ነገር ነው። በኢትዮጵያ የሚኖሩ ህዝቦችን ህልውና እየካደ ወደ ጎሳ ደረጃ ዝቅ ከሚያደርግና "የጎሳ ፖለቲካ ይቁም" ከሚል ሰው ጋር ግን የሚካሄድ ክርክር የለም።
3.6K views19:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 23:32:35 ስለ ጦርነቱ- በጥቂቱ
-------
አፈንዲ ሙተቂ
-------
"ስለሙዚቃ መጻፍ አበዛህ። ስለጦርነቱ ተናገር እንጂ?!" የሚሉ ድምጾች በዝተውብኛል። በመጀመሪያ እንዲህ ዓይነት መመሪያ መሰል ጥያቄ እንደማልቀበል የገለጽኩትን መድገም እፈልጋለሁ። የምጽፍበትን አጀንዳ የምወስነው እኔ ብቻ ነኝ። ይህንን ያዙልኝ።
------
ጦርነቱን በተመለከተ ያለኝ አቋም አልተቀየረም። አይቀየርምም።

ጦርነት ለምንም ነገር መፍትሔ ሆኖ አያውቅም። ጦርነት አለመግባባቶችን ያባብሳል እንጂ የመፍትሔ ሐሳብ አያመነጭም። ከጦርነት የሚገኝ ትርፍ የለም። ጦርነት በብዙ ዓመታት ልፋት የተሰራውንና የተገነባውን የሀገር ሀብትና የግለሰቦች ይዞታ ከማጥፋት በቀር ምንም ፋይዳ የለውም።

አዎን! ይህንን አስረግጬ እናገራለሁ። ጦርነት መሰረተ ልማቶችን የሚያወድም፣ ሱቆችንና የገበያ አዳራሾችን የሚፈነቃቅል፣ አዝመራን የሚያቃጥል፣ የብዙዎችን ነፍስ የሚቀጥፍ፣ ብዙዎችን የሚያፈናቅል፣ ቤተሰብን የሚበትን፣ ህጻናትን፣ ሴቶችንና አረጋዊያንን ለዋይታና ለሰቆቃ የሚዳርግ፣ ለአጠቃላይ የኢኮኖሚ ቀውስ መንስኤ የሚሆን፣ ሀገሮችንና ከተሞችን የሚያፈራርስ የጥፋት መንገድ ነው።

ጦርነትን ተገደው ይገቡበት ይሆናል። ፍትሐዊነት ሲጠፋ ጦርነት ማወጅ ያለ ነው። ለምሳሌ ሀገር በውጪ ሃይል ብትወረር ጦርነትን ማወጅ ግዴታ ሊሆን ይችላል። ታዲያ በእንዲያ ዓይነት ጊዜም ቢሆን ቅድሚያ የሚሰጠው ለሰላማዊ አማራጮች ነው። ሁሉም የሰላም በር ዝግ ሲሆን ወደ ጦርነት መግባቱ ነው ፍትሓዊ መፍትሔ የሚያስገኘው። ሰላማዊ አማራጮች ሳይሞከሩ ወደ ጦርነት መግባት ራስን እንደማጥፋት ይቆጠራል።

እጅግ አስቀያሚው ጦርነት ደግሞ በአንድ ሀገር ዜጎች መካከል የሚካሄደው ነው። እንዲህ ዓይነቱ ጦርነት ከቁሳዊና ሰብዓዊ ውድመቱ ባሻገር በረጅም ታሪካዊ ሂደት የተገነባውን የህዝቦችን ብሄራዊ መስተጋብር የሚያናጋ እና ሀገር እንድትበተን መንስኤ ሊሆን የሚችል ክፉ ደዌ ነው።
------
አምና እንደዚህ እያልኩ ስጽፍ ነበር። አሁንም አቋሜ ይኸው ነው። ዛሬም ሁለቱም ወገኖች ጦርነቱን አቁመው ችግራቸውን በውይይትና በድርድር ብቻ ይፍቱት እላለሁ። ሰላም!!
-----
አፈንዲ ሙተቂ
ነሐሴ 22/2014
2.3K views20:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 22:14:20 የወጋየሁ ደግነቱ “አርኬ ሁማ” እና “ወረት”
-----
ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
-----
በድፍን ኢትዮጵያ ከሚታወቁት የአፋን ኦሮሞ ዘፈኖች አንዱ “አርኬ ሁማ” ይሰኛል። ዘፋኙ ሟቹ ድምጻዊ ሻለቃ ወጋየሁ ደግነቱ ነው። ይህ ዘፈን በዜማና ግጥም አሰካኩም ሆነ በሚያስተላልፈው መልዕክት “ዘመን አይሽሬ” ከሚባሉት አንዱ ነው። የዚህ ዘፈን አዝማች የህዝብ ነው። የሀረርጌ ኦሮሞ ወጣቶች ከጥንት ጀምሮ ሲቀባበሉት ነው የኖሩት። ዜማውን ከህዝቡ ወደ መድረክ አምጥቶ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሰማው ያደረገው ሰው ደግሞ “አቡበከር ሙሳ” ይባላል። አቡበከር “አርኬ ሁማ”ን እንደ አዝማች በማድረግ የዘፈኑን ግጥም ውብ በሆነ የቃላት ቅንብር ጽፎታል። በመሆኑም በአዝማቹ ግጥም በመሀል መንገድ ላይ ተንጠልጥሎ የቀረው የዘፈኑ መልዕክት በአቡበከር ሙሳ ውብ ብዕር የተሟላ ሆኗል።

“አርኬ ሁማ ሁማ አርኬ ሁማ (Arke humaa humaa arkee humaa)
ኤጋ ሆሪ ታቴ ጃለልቲ ነማ (Eega horii taate jaalalti namaa)
ረብቢ መሌ ነምኒ ኒጂጂረማ” (Rabbi malee namni nijijjirama)

ይህ የግጥሙ አዝማች ነው። በአማርኛ እንደሚከተለው ሊተረጎም ይችላል።

“አየሁት ግድየለም አየሁት ግድየለም”
“የሰው ልጅ መውደድ ከሆነ ለገንዘብ
“ፈጣሪ እንጂ ሰውስ ይቀየራል ግድየለም”

አቡበከር በዚህ ላይ ነው የሚከተሉትን መስመሮች የጨመረው።

“አርኬ ሁንዳ ሁንዳ አርኬ ሁንዳ (Arke hunda hunda arge hunda)
አርኬ ሁማ ሁማ አርኬ ሁማ (Arke humaa humaa arge humaa)
አምማ ሆሪ ዸብናን ከን ነ ዴይሱ ማሉማ (Amma horii dhabnaan kan nadheeysu maaluma)
አርኬ ሁማ (Arke humaa)
----------
አዱኛፍ ጂርተኒ አኺራፍ ቴይሳኒ (Adunyaaf jirtanii akhiraaf teysanii
ዋን ኢሲን ኤግገተን ኢሲን ዋ ሂንቤይተኒ (Waan issin eeggatan isin wa hinbeetanii)
አርኬ ሁማ (Arke humaa)
----------
ሀማሬሲ ሂንጨቡ ኑመ ሚጪረማ (Hammarreessi hincabu numa micciiramaa
ገራን ኢልማ ነማ ቶርባ ጂጂረማ (Garaan ilma namaa torba jijjiramaa)
አርኬ ሁማ (Arke humaa)
------------
ግጥሙ ወደ አማርኛ ሲተረጎም እንደሚከተለው ይሆናል (ተርጓሚው መኮንን ታደሰ መኮንን ነው)።

ሁሉን አየሁታ… ሁሉን አየሁታ…
ንዋይ ብቻ ሲሆን የሰው ልጅ ውለታ፣
ሁሉም ይቀየራል ያለርሱ ያለጌታ።
--------
አየሁት ሁሉንም አየሁት ሁሉንም፣
አየሁት ግድየለም አየሁት ግድየለም
አሁን ሀብት ባጣ…
መሸሽን ምን አመጣ?
------
ለአዱኛ ስትሮጡ ለንዋይ ስትኖሩ
ምን እንደሚገጥማችሁ…
ምን እንደምትሆኑ…
አይታወቅ ዳሩ!!
--------
ዝግባ አይሰበር ይጠማዘዝ እንጅ
አስሬ ይቀየራል አመሉ የሰው ልጅ።
------
ግጥሙ ስለ"ወረት" ነው የሚያወሳው።
አዎን! የሰው ልጅ ወረተኛ ነው። “አይደለሁም” ቢል እንኳ ወረተኛነት ሁልጊዜም ይፈታተነዋል። ማግኘትና ማጣት የዚህች ዓለም ነጸብራቅ በመሆናቸው ማንንም ሊያጠቁ ይችላሉ። ወረተኛነት ግን ሁሉም ዘንድ ላይደርስ ይችላል። ሰዎች ሽንጣቸውን ገትረው ከታገሉት “ወረት”ን በሩቁ ማስቀረት ይችላሉ። አለመታደል ሆኖ አብዛኛው ሰው ለወረት ይንበረከካል። “ፈረንካ” ሲቋጥር መቶ ሰማኒያ ዲግሪ ያህል ይቀየራል። ትላንት አብሯቸው ኳስ ሲጫወትና ማዕድ ሲቋደስ የነበሩትን ሰዎች በቆረጣ እያየ “እእ…ማን ነህ አንተ?..ስምህ ጠፋብኝ.. ወዘተ…” ማለት ይጀምራል። ዘመዶቹ ሊግጡት ያቆበቆቡ በቅሎዎች ይመስሉትና በሩቁ ይሸሻቸዋል። የባሰበት ደግሞ አፍ የፈታበትን ቋንቋ፣ የተወለደበትን ቀዬ እና ሀገሩን ጭምር እስከ መካድ ይደርሳል።

ታዲያ የሚያሳዝነው ነገር በ“ፈረንካ” ልቡን እያማለለ የቀየረው የ“ወረት” ልክፍት ነገን ጭምር የሚያስረሳው መሆኑ ነው። ነገ ሞት እስትንፋሱን ቀጥ አድርጎ ሊያቆመው ቢመጣበት “ወረት” ሊያድነው ነውን? ከሞት በኋላ ባለው ህይወት ከሚመጣበት ቅጣትስ “ወረት”ን አስጥለኝ ብሎ ሊማጸነው ነውን? አረ ምናለ.. በፈረንካ ባንታወር!… አረ ምናለ በወረት ባንታለል!…… (የራሴን ፍልስፍና ጨማመርኩበት አይደል? በርግጥ በግጥሙ ውስጥ ይህ ሁሉ የለም። መልዕክቱ ግን ከዚህም በላይ ነው… ብዙ ብዙ ያስጽፋል….)
------
እንግዲህ “ወረት”ን አላህ ይያዝልን። ወረተኞችም አደብ ግዙልን። ጌታችን የሰጠን ይበቃናልና በፍቅር አብረን እንኑር። ለሁሉም ይህንን የዩ-ቲዩብ ቪዲዮ ክፈቱና ወጋየሁ ደግነቱን ስሙት። የልጅነታችንን ዘመን እያስታወስን “ወረት”ን በጋራ ወግድ እንበለው።

አርኬ ሁማ አርኬ ሁማ…
ኤጋ ሆሪ ታቴ ጃለልቲ ነማ…
ረብቢ መሌ ነምኒ ኒጂጂረማ
አርኬ ሁማ!...




------
አፈንዲ ሙተቂ
ነሐሴ 28/2014
2.1K views19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 23:32:29
ይህንን ምርጥ የኦሮምኛ ዜማ ተጋበዙ!!
-----
አርቲስት ከዲር ሰዒድ እና ጎሓ ምሥራቅ ባንድ በዚህ ውብ ዘፈን የፈጠሩትን ተአምራዊ ጥምረት ያድምጡ።
-----
ድምጻዊውና የባንዱ አባላት በ1981 ድሬ ዳዋ ከተማ ተገናኝተው "ሙዚቃ የዓለም ቋንቋ ነው፣ የሙዚቃ ውስጣዊ ሃይል ደግሞ ዜማ ነው" የሚለውን አባባል እውነተኛነት የሚመሰክር ስራ ነበር የሰሩት። በተለይም የጎሓ ምሥራቅ ባንድ አባላት በዚህ ዘፈን ላይ በጣም ነው የተራቀቁበት።
2.5K views20:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 22:08:38
ሶማሊያ እያንሰራራች ነው!
-----
ይህቺ ከተማ "በለድወይን" ናት። በከተማዋ መሃል የሚያልፈው የዋቤ (ሸበሌ) ወንዝ ነው። በለድወይን ከኢትዮጵያዋ የፌርፌር (ቀላፎ) ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ትገኛለች።
2.4K views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 18:39:38
ኤርትራ ኤርትራ ኤርትራ፡
በዓል ደማ እናልቀሰ ተደምሲሱ፡
መስዋእታ ብሓርነት ተደቢሱ።

መዋእል ነኺሳ ኣብ ዕላማ፡
ትእምርቲ ጽንዓት ኰይኑ ስማ፡
ኤርትራ'ዛ ሓበን ዉጹዓት፡
ኣመስኪራ ሓቂ ክምትዕወት።

ኤርትራ ኤርትራ፡
ኣብ ዓለም ጨቢጣቶ ግቡእ ክብራ።

ናጽነት ዘምጸኣ ልዑል ኒሕ፡
ንህንጻ ንልምዓት ክንሰርሕ፡
ስልጣነ ከነልብሳ ግርማ፡
ሕድሪ'ለና ግምጃ ክንስልማ።

ኤርትራ ኤርትራ፡
ኣብ ዓለም ጨቢጣቶ ግቡእ ክብራ።
2.5K views15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ