🏡 The complete catalog of thousands of rent-to-own properties in USA Get Mystery Box with random crypto!

A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU

የቴሌግራም ቻናል አርማ aahdabofficial — A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU A
የቴሌግራም ቻናል አርማ aahdabofficial — A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU
የሰርጥ አድራሻ: @aahdabofficial
ምድቦች: መጠነሰፊ የቤት ግንባታ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 17.94K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-25 07:02:06 የህብረተሰቡን የቤት ልማት ፕሮግራም ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት መጠናከር እንዳለበት ተጠቆመ 

ግንባታቸው በመፋጠን ላይ የሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በማጠናቀቅና ነባር ፕሮጀክቶችን በመዝጋት የህብረተሰቡን የቤት ልማት ፕሮግራም ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረገው ርብርብ ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት ተጠቆመ፡፡ 

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እንዲሁም የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች ባለፉት 15 ቀናት በተከናወኑት ተግባራት ዙሪያ ባካሄዱት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ላይ በሰነዘሯቸው አስተያየቶች በተለያዩ ሳይቶች ግንባታቸው በመጠናቀቅ ላይ ያሉ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ቀሪ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ ለነዋሪዎች ለማስተላለፍና ፕሮጀክቶቹን በመዝጋት ሌሎች ቀጣይ የልማት ሥራዎችን ለማፋጠን እየተደረገ ያለው ጥረት ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

የቤቶቹን ግንባታ ከፍፃሜ በማድረስ ፕሮጀክቶቹን ዘግቶ ለመውጣት እየተደረገ ባለው ርብርብ በተለይ ለመሠረተ ልማት ግንባታ፣ ለወሰን ማስከበር እንዲሁም ለግብዓት አቅርቦትና ለሌሎችም ቁልፍ ተግባራት ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ያመለከቱት የሥራ ኃላፊዎቹ የከተማዋን ነዋሪዎች የቤት ባለቤት በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይበልጥ ተቀናጅቶ በጋራ መረባረብ ተገቢ ነው ብለዋል፡፡

የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራትና የኮርፖሬሽኑ የግንባታ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ቶማስ ደበሌ እንዲሁም ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች የከተማ አስተዳደሩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ነባር የቤት ልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለነዋሪዎች ማስተላለፍና  ህብረተሰቡ በየጊዜው ለሚያነሳቸው ቅሬታዎች ምላሽ መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

በየደረጃው የሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ከመደበኛ የሥራ ሠዓት በተጨማሪ ትርፍ ጊዜያቸውን በመጠቀምና አምሽቶ በመሥራት የተቀመጠውን ዕቅድ ለማሳካት ጠንክረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡

በሥራ አፈፃፀም ግምገማው ላይ የቢሮው ፣ የኮርፖሬሽኑ እንዲሁም የቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎችና የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመሰረተ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ  ልማት ቋሚ ኮሚቴ አባላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

http://www.aahdab.gov.et

https://t.me/aahdabofficial

https://www.facebook.com/aahdabofficial
2.3K views04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 19:50:41 "ስውር ስኬት" በሚል ርዕስ ስለ ስለ ጋራ መኖሪያ ቤቶች የተዘጋጀውን ዶክመንተሪ ፊልም ዛሬ ከምሽቱ 3:00 ሰዓት በዋልታ ቴሌቭዥን እንዲከታተሉ ተጋብዘዋል።

http://www.aahdab.gov.et

https://www.facebook.com/aahdabofficial
3.7K views16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 21:27:31
ማስታወቂያ

በ40/60 እና በ20/80 የቤት ልማት ፕሮግራም  ተመዝግባችሁ ሰትቆጥቡ የነበራችሁ እና በጋራ ህንፃ የመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበር በፈቃደኝነት ለመደራጀት በ54 በድን የተደለደላችሁ በሙሉ።

ከ16/08/2015 ዓ.ም እስከ 18/08/2015 ዓ.ም ባሉት ቀናት   ከታች ባለው ሰንጠረዥ መሰረት  በተደለደላችሁበት ክፋለ ከተማ እና ቀን በመገኘት:-

የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ ወይም
      ፓሰፖርት

ሁለት 3 በ 4 የሆነ ፎቶግራፍ 

በመያዝ የህጋዊ ማህበርነት መሰፈርቶችን እንድትፈፁሙ የአዲስ አበባ ህብረት ስራ ማህበር ኤጀንሲ  ጥሪውን አስተላልፏል ።
3.4K views18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 19:56:35
4.5K views16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 06:28:42
ለ3ኛው ዙር የ40/60 የንግድ ሱቅ ጨረታ አሸናፊዎች የወጣ ማስታወቂያ

ኮርፖሬሽኑ 3ኛውን ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ንግድ ቤቶች በጨረታ አወዳድሮ መሸጡ ይታወቃል ።

በመሆኑም 1ኛ የሆናችሁ አሸናፊዎች ከታች በተቀመጠው የውል ማዋዋያ  የጊዜ ሰሌዳ  መሰረት  ለ15 የስራ ቀናት ብቻ ቦሌ ክፍለ ከተማ ቅጥር ግቢ በሚገኘው አንድ ማእከል በአካል ቀርባችሁ እንድትዋዋሉ ኮርፖሬሽኑ ያሳስባል።

http://www.aahdab.gov.et

https://t.me/aahdabofficial

https://www.facebook.com/aahdabofficial
6.3K viewsedited  03:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 16:02:31 ማስታወቂያ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቤቶች ልማትና አስተደዳር ቢሮ የ2005 ዓ.ም በ20/80 እና 40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም ተመዝግባችሁ አሁን መንግስት ባመቻቸው የጋራ ህንፃ መ/ቤት/ህ/ሥራ/ማህበር በፍቃደኝነት ተደራጅታችሁ ቤት ለመገንባት የተመዝግባችሁና አሰፈላጊውን መረጃ አሟልታችሁ ስም ዝርዝራችሁ በግሩፕ ተደልድሎ ለህብረት ሥራ ማህበራት ኤጀንሲ የተላከ መሆኑ ይታወቃል።

ይሁንና ከየግሩፕ አስተባበሪዎች አድራሻቸውን ማግኘት ያልቻልን ተመዝጋቢዎች በሙሉ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ማስታወቂያዎች በአካል ቀርባችሁ መረጃ እንድትሰጡ ብትጠየቁ እና ቀርበው ሪፖርት እንድታደርጉ ብትባሉ  ሪፖርት ያላደረጋችሁ አባላትን እና በተለያየ መልኩ ቅድመ ክፍያውን መክፈል አንችልም ያላችሁ የመተካካት ስራ በቢሮው በኩል እንዲሰራ በሚል ውሣኔ መሰረት ተቋሙ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል:-

1. B+G+9 የህንፃ ከፍታ ላይ 42 የነበረው የቡድን ድልድል ቡድን 1፣2እና 3 የታጠፈ መሆኑንና በነዚህ ቡድን የነበራችሁ ተመዝጋቢዎች ድልድሉን በማየት ወደ ተመደባችሁበት ቡድን አስተባባሪዎች ሪፖርት እንድታደርጉ፤

2. የ2B+G+13 የነበረው 15 ቡድን ባላችሁበት ሲሆን ተጠባባቂዎችን ሙሉ ለሙሉ በክፍት ቦታዎች ላይ በመደልደል የተሟላ መሆኑን፤

3. ተጠባባቂ የነበራችሁ ተመዝጋቢዎች 2B+G+13 ላይ ሙሉ ለሙሉ የተመደባችሁ በመሆኑ ስም ዝርዝርራችሁን በማየት ለቡድን አስተባባሪዎች ሪፖርት እንድታደርጉ በB+G+9 በተጠባባቂነት የነበራችሁ ዝርዝራችሁን በቅደም ተከተላችሁ መሠረት ፖስት የምናደረግ በመሆኑ ያልተመደባችሁ በትዕግስት በተጠባባቂነት እንድትቆዩ እናስታውቃለን፤

በመጨረሻም ከቢሮው እና ከህብረት ሥራ ማህበራት ኤጀንሲ ውጪ የሚለጠፉ ማስታወቂያዎችን መከተል እንደሌለባችሁ እና ቢሮው በህጋዊ መንገድ ኃላፊነት ወስዶ ከሚለቃቸው መረጃዎች ውጪ በተዛባ መረጃ እንዳትሳሳቱ እናሳስባለን ፡፡

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
9.7K views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 20:28:07



ቢሮው እና ኮርፖሬሽኑ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ነዋሪዎች ያደረጉትን የኢፍጣር እና የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ በዚህ መልኩ ዘግቦታል
3.3K views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 18:27:34
ቢሮው እና ኮርፖሬሽኑ በአዲስ ቴክኖሎጂ የህፃናት ማቆያ ግንባታ አስጀመሩ

ቢሮው እና ኮርፖሬሽኑ ኪዩቢክ ማኑፋክቸሪንግ ከተባለ ኩባንያ ጋር በመተባበር ጥቅም ላይ የዋሉ የኘላስቲክ እቃዎችን ወደ ተገጣጣሚ የግንባታ ግብአትነት በመቀየር በተሰራ  አዲስ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የህፃናት ማቆያ ግንባታ በተቋሙ ቅጥር ግቢ ውስጥ አስጀምረዋል።

ግንባታው ጥቅም ላይ የዋሉ የኘላስቲክ እቃዎችን ለግንባታ በሚሆን መልኩ በማምረት ጥራት ጊዜን እና ወጪን በቆጠበ መልኩ እንደሚሰራ በግንባታ ማስጀመሪያ ስነስርአቱ ላይ በማኑፋክቸሪንጉ ስራ አስኪያጅ ተብራርቷል።

ቴክኖሎጂው ለግንባታ ዘርፉ አዲስ የቴክኖሎጂ ሽግግር ከማምጣቱም በላይ ጥቅም ላይ የዋሉ ኘላስቲኮች አካባቢን እንዳይበክሉ ጠቀሜታው የጎላ ነው ተብሏል።

ለተቋሙ ሰራተኛ ልጆች ጥቅም ላይ እንዲውል ማስገንባት የተጀመረው  ህፃናት ማቆያ  በቀጣይ ወደጋራ መኖሪያ መንደሮቸ አካባቢም እንደሚቀጥል በእለቱ ተገልጿል።

http://www.aahdab.gov.et

https://t.me/aahdabofficial

https://www.facebook.com/aahdabofficial
3.9K views15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 16:02:39
3.7K views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 07:10:20
ቢሮው እና ኮርፖሬሽኑ የትንሳኤ እና የኢድ ዓልፈጥር በአላትን ምክንያት በማድረግ ለሰራተኞች ማዕድ የማጋራት መርሀ ግብር አካሄዱ

በማዕድ ማጋራት መርሀግብሩ 163 የሚሆኑ ዝቅተኛ ደሞዝተኞችን ያካተተ ሲሆን ለሰራተኞቹ 5 ሊትር ዘይት ፣ 10 ኪሎ ፉርኖ ዱቄት እና 20 እንቁላል በስጦታ ተበርክቷል።

ክብርት ያስሚን ወሀብረቢ በም/ከ/ ማእረግ የቤ/ል/አስ/ቢ ኃላፊ በማእድ ማጋራት መርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት  የፋሲካ እና የረመዳን ወቅት በአል አስመልክቶ በተያዘው ሳምንት ብቻ 1470 አቅመ ደካማ ወገኖችን ማእድ የማጋራት ስራ መሰራቱን ገልፀው እንዲህ አይነቱ የመረዳዳት ባህል መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።

በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ ድጋፍ የተደረገላቸው ሰራተኞች በበኩላቸው ቢሮው እና ኮርፖሬሽኑ በአላቱን በደስታ እንዲያሳልፉ አስቦ ላበረከተው ስጦታ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

http://www.aahdab.gov.et

https://www.facebook.com/aahdabofficial
940 views04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ