Get Mystery Box with random crypto!

A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU

የቴሌግራም ቻናል አርማ aahdabofficial — A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU A
የቴሌግራም ቻናል አርማ aahdabofficial — A.A HOUSING DEVELOPMENT & ADMINISTRATION BUREAU
የሰርጥ አድራሻ: @aahdabofficial
ምድቦች: መጠነሰፊ የቤት ግንባታ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 17.94K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-05-16 20:29:30
በድጋሚ የወጣ ማስታወቂያ

የጋራ መኖሪያ ቤት ለመገንባት በ54  ማህበራት ለተደረጃችሁ በሙሉ ፦

ቀደም ሲል በ07/09/2015 ዓ.ም
በወጣ ማስታወቂያ መሠረት ሰባ ከመቶውን (70%) ለተከታታይ 5 የስራ ቀናት እንድታስገቡ ማሳወቃችን ይታወቃል።

ይሁንና የ54ቱ ማህበራት ተወካዮችና አባላት ባቀረቡት የማስገቢያ ጊዜው  ይራዘምልን ጥያቄ  መሰረት የማስገቢያው ግዜ ለተጨማሪ 10 የስራ ቀናት የተራዘመ መሆኑን እንገልፃለን።

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ

http://www.aahdab.gov.et

https://t.me/aahdabofficial

https://www.facebook.com/aahdabofficial
7.5K views17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 20:05:02
ማስታወቂያ

በ54 ማህበር ለተደራጃችሁ የማህበር ቤት ተመዝጋቢዎች በሙሉ ፦
8.9K views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 11:35:52
2.3K views08:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 11:34:52
2.4K views08:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 11:27:30 ከጋራ መኖሪያ ቤት እደለኞች ጋር በቅርበት በመስራት እና የተመረጡ ስራዎችን በማጠናቀቅ ነዋሪውን ወደ መኖሪያ ቤቱ የማስገባት ስራ እየተከናወነ ነው፡፡

የጋራ መኖሪያ ቤት ባለእድለኞችን ቤታቸው ለማስገባት ከራሳቸው ከነዋሪዎች ጋር በርካታ ቀሪ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ የመሰረተ ልማት ተቋማት ፣ የስራ ተቋራጭ እና የማህበራት እንዲሁም የነዋሪ ተወካዮች በተገኙበት ያለፈው አንድ ወር አፈጻፀም በተገመገመበት ወቅት ተገልጿል፡፡

ከመጋቢት 1 ጀምሮ ላለፈው አንድ ወር በቅርንጫፍ 1 ፣ 4 እና 7 የተሰሩ ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በተመረጡ ስራዎች በተለይም ከመሰረተ ልማት አንጻር የውሀ ፣ የፍሳሽ ፣ የመብራት ፣ የመንገድ እና የተረፈ ምርት ማንሳት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን እና ቀሪ ጥቃቅን ስራዎች በቀሪ ወራት ለማጠናቀቅ ከነዋሪው ጋር ከአሁንም ከምን ጊዜውም በላይ በመቀናጀት መስራት ይገባል ተብሏል፡፡ 

ስራዎች በተፈለገው ጊዜ ለማከናወን የዋጋ ንረት ፣ የመሰረተ ልማት አፈጻጸም መዘግየት ፣ የስርቆት ፣ የአልሙንየም ገጠማ መዘግየት ፣ የተቋራጮች አቅም ማነስ እና የወሰን ማስከበር ስራዎች እንደ ውስንነት የተነሱ ቢሆንም ያሉ ችግሮች ቢኖሩም አብሮ በመስራት ችግሩንም በጋራ መቅረፍ የገባል ተብሏል፡፡

በውይይቱም የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ፅጌወይን ካሳ እና የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽምልስ ታምራትን ጨምሮ ሌሎች የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የመሰረተ ልማት ተቋማት ተወካዮች ፣ የስራ ተቋራጭ እና የማህበራት ተወካዮች እንዲሁም የነዋሪ ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡

http://www.aahdab.gov.et

https://www.facebook.com/aahdabofficial
2.4K viewsedited  08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 07:54:31



የ14ኛው ዙር የ20/80 እና የ3ኛው ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ውል የማዋዋል ሂደት በማስመልከት በዋልታ ቴሌቭዥን የተናዳ ኘሮግራም
4.1K views04:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 07:54:08



"ስውር ስኬት" በሚል ርእስ የጋራመኖሪያ ቤቶችን በተመለከተ ከዋልታ ቴሌቪዥን ጋር በመተባበር የተዘጋጀ  ዶክመንተሪ
4.3K views04:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 21:56:20
ማስታወቂያ

ለ14ኛው ዙር የ20/80 እና ለ3ኛው ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለእድለኞች በሙሉ
5.4K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 10:55:50
በበጀት አመቱ ማጠናቀቂያ የተሻለ  ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ መደረግ እንዳለበት ተገለጸ

የቢሮው እና የኮርፖሬሽኑን የ9 ወር አፈጻፀም የሁለቱም ተቋማት አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በተገኙበት ተገመገመ፡፡

ወ/ሮ ፅጌወይን ካሳ የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ በግምገማው ላይ እንደገለጹት በዘጠኝ ወሩ ያልተከናወኑ ተግባራት ላይ ትኩረት በመስጠት በበጀት አመቱ ማጠናቀቂያ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ መደረግ አለበት ያሉ ሲሆን ስራን በጋራ አቀናጅቶ ለመስራት የአመለካከት ለውጥ ማምጣጥ ይገባልም ብለዋል፡፡

በግምገማው ለአመታት እጣ ወቶባቸው ርክክብ ባልተካሄደባቸው ቤቶች በተመረጡ ስራዎች ላይ በማተኮር ግንባታውን ለማጠናቀቅ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በጥንካሬ የተነሱ ሲሆኑ በተመሳሳይም በ13ኛው ዙር የ20/80 እና በ3ኛው ዙር የ40/60 ቤት ማስተላለፍ እና ከንግድ ቤት ጨረታ ጋር ሰፊ ስራ መሰራቱ እንዲሁም የመንግስት ቤት መረጃ አያያዝን ለማዘመን የተሰሩ ስራዎች በጥንካሬ ተነስተዋል፡፡

በቀጣይም በቦንድ ብድር አመላለስ ፣ በህገወጥ የተያዙ ቤቶችን ከማስለቀቅ እና የተቋሙን ሀብት አሰባሰብ ላይ በተለይም በየሳይቱ ስራ ላይ የማይውሉ እና የተካማቹ ንብረቶች መፍትሄ ከማሰጠጥ አንጻር በርካታ ስራዎች ይጠበቃሉ ተብሏል፡፡

የቢሮ ኃላፊዋ ወ/ሮ ፅጌወይን ካሳ ጨምሮ የቢሮው እና የኮርፖሬሽኑ አጠቃላይ ሰራተኞች እና አመራሮች በግምገማው ላይ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

http://www.aahdab.gov.et

https://www.facebook.com/aahdabofficial
5.1K views07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 11:38:01
በ54 ቡድን የተደለደሉ የማህበር ቤት ፈላጊዎችን የማደራጀት ስራ ተሰራ

የከተማው ህብረት ስራ ማህበር ኤጀንሲ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በማህበር ለመገንባት በ54 ቡድን የተደለደሉትን በማህበር በማደራጀት ወደ ስራ የማስገባት ስራ እየሰራ ነው።

በ2005  ዓ.ም  በ40/60  እና በ20/80  የቤቶች ልማት ፕሮግራም የጋራ መኖሪያ ቤቶችን  ለመገንባት ሲቆጥቡ የነበሩ እና አሁን ግን በፍላጎታቸው በህብረት ስራ ማህበራት ለመደራጀት  ከ70 በመቶ በላይ  ለመቆጠብ  ዝግጁ የሆኑ ማህበራትን  ወደ ስራ  ለማስገባት  የማደራጀት  ህጋዊ እውቅና የመስጠት ስራ ተሰርቷል።

በቀጣይም ሰላሳ በመቶ ብድር ተመቻችቶ 70 ከመቶውን በማህበሩ የዝግ አካውንት ማስገባታቸው ሲረጋገጥ ግንባታው ለሚካሄድባቸው ሳይቶች እጣ የማውጣት እና የማስረከብ እንዲሁም የማስጀመር ስራ የሚሰራ ይሆናል ተብሏል።


http://www.aahdab.gov.et

https://www.facebook.com/aahdabofficial70
7.0K views08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ