Get Mystery Box with random crypto!

Natnael Mekonnen

የሰርጥ አድራሻ: @natnaelmekonnen21
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 173.42K
የሰርጥ መግለጫ

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 396

2022-05-19 17:39:20
የዚምባብዌው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው ኮ/ል መንግስቱ ሀይለማርያምን ለኢትዮጵያ አሳልፋ ልትሰጥ እንደምትችል ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ ላይ ገልጸዋል:: "የኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት የዚምባብዌ መንግስትን ቀርቦ ጥያቄ ካቀረበ አስፈላጊው እርምጃ ተወስዶ ተገቢው ጥያቄ መልስ ያገኛል" ነው ያሉት የዚምባብዌው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

ኮረኔል መንግስቱ ሆይ የዚምባቤ መንግስት ለኢትዮጵያ አሳልፋ እስኪሰጥህ አትጠብቅ በገዛ ፍቃድህ ወደ ምትወዳት ሀገርህ ከነቤተሰብህ በመግባት ቀሪ እድሜህን በሀገርህ ላይ አሳልፍ
35.0K views14:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 15:07:13 ‘’አዳዲስ አስተሳሰብና አሰራሮችን በመተግበር መከላከያ ሰራዊቱን በሁለገብ መልኩ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡’’ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር አብርሀም በላይ

#Ethiopia : የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ለሰራዊቱና ለሲቭል ሰራተኞቹ ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንት የዕጣ ማውጣትና የርክክብ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የመከላከያ ሚንስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ የመከላከያ ሰራዊታችንን ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ አዳዲስ አሰራሮችን በመዘርጋት ወደተግባር መገባቱን አረጋግጠዋል፡፡

ሀገርን በመስዋዕትነቱ እያስከበረ የሚገኘው ጀግናው መከላከያ ሰራዊታችንን ተጠቃሚ ለማድረግ አዳዲስ አሰራሮችን በመዘርጋት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ሚንስትሩ በጦርነት ውስጥ ሆነን ገንብተን ያጠናቀቅነውን የመኖሪያ ቤት ተቋሙን ላገለገሉ አባላት መተላለፉ አንዱ የለውጥ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ሜ/ጄ ኩምሳ ሻንቆ ፋውንዴሽኑ በኢንዱስትሪና በእርሻ ከመሰማራቱ በተጨማሪ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች ውስጥ በስምንት ሳይቶች የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በመገንባት የሰራዊቱን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡

በሰሚት ሁለት የጋራ መኖሪያ አፓርታማ ስለደረሳቸው መደሰታቸውን የገለጹት ሌ/ኮ ዘላለም ማሞ በቀሪ ዘመናቸው ሀገራቸውን ለማገልገል የበለጠ ተነሳሽነት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል፡፡

ሌላው ያነጋገርናቸው በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ ለረጅም አመት አገልግገለው በጡረታ ላይ በመሆን በቤት ክራይ ይኖሩ የነበሩትና የእድሉ ተካፋይ የሆኑት ሻምበል መክብብ መኮንን ለረጅም ዘመን ያገለገልኩት ተቋም የቤት ባለቤት ስላደረገኝ ደስ ብሎኛል ብለዋል፡፡

በዕለቱ ሙሉ እድሳታቸው የተጠናቀቁ 529 ከባለአንድ እስከ ባለኣራት መኝታ ቤቶች ዕጣ ለወጣላቸው የሰራዊት አባላትና የሲቭል ሰራተኞች ተላልፏል፡፡
37.3K views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 15:07:03
ናሽ የጥርስ እና የዓይን ህክምና ክሊኒክ
        Nash Dental and Optometry Clinic
 
ናሽ የጥርስ እና የዓይን ህክምና ክሊኒክ ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎ ች በመታገዝ ሙሉ የጥርስና የአይን ህክምናን በመስጠት ላይ ይገኛል::  ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በከፊል
➢  
➢ መጥፎ የአፍ ጠረንን ማከም
➢ የቆሸሹ ጥርሶችን በማሽን እናፀዳለን
➢ በህክምና መዳን የማይችሉትን ጥርሶች መንቀል
➢ ወጣ ገባ ያሉ ጥርሶችን በ ኦርቶዶንቲክ አፕላይንስ እና በብሬስ ማስተካከል
➢ የጥርስ ስር ህክምናን መስጠት
➢ የተቦረቦሩ ጥርሶችን እንሞላለን
➢ የተነቀሉ ጥርሶችን በሰው ሰራሽ አርተፊሻል መተካት
➢ የጥርስ ራጅ አገልግሎት መስጠት
 
➢ የረዥም እርቀት፤ የአጭር እርቀት እና ከእድሜ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የቅርብ እይታ መቀነስ ምርመራ እና ህክምና
➢ ሁለት ዓይኖች ተቀናጅተው ያለመስራት ችግር ምርመራ እና ህክምና
➢ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰት የእይታ መቀነስ ችግርን ምርመራና ህክምና
➢ የህፃናት የአይን ምርመራና ህክምና
➢ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የአይን መነጽሮች የሎው ቪዥን ድጋፍ መስጫ የቪዥን ቴራፒ መሳሪያዎች መለካት ማስተካከል እና ማዘዝ
 
 
በሁሉም የህክምና አይነቶች ቅናሽ አድርገናል
      አድራሻ: ቁጥር 1 ሜክሲኮ ገነት ሆቴል ፊት ለፊት ካሳ ግራንድ ሞል 4ኛ ፎቅ
                       ቁጥር 2 ሰሚት ሳፋሪ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት ገሊላ ፕላዛ
                       Tel: 0905262626, 0913858561
32.3K views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 13:50:12

31.7K views10:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 13:32:37
መልክት ከአዲስ አበባ ሞተረኞች

ናቲ በመጀመሪያ አመሰግናለሁ አዲስ አበባ መንገድ ትራንስፓርት ከሁለት አመት በፊት ሙሉ ለሙሉ እንዳንቀሳቀስ ክልክሎን ነበር ግን እነሱ ያወጡት ህግ ትክክል እናደልሆነና እኞን የሚጎዳ በዚህ የስራ ዘርፍ አብዛኞቻችን ቤተሰብ አስተዳዳሪ እንደሁንን ቅሬታ አቅርበን ወደ ስራ እንድንገባ ህግ አውጥተው አርገውን ነበር

ለምሳሌ ከህጎች ውስጥ

1 ሞተሮቹ ጂፒኤስ እንዲገጥሙ
2 ኮድ 2 የሆንቱ ሞተረች ኮድ 3 እንዲሆኑ
3 ለቁጥጥር እንዱያመች በማህበር እንዲሆኑ ሌሎችም ህጉ አሉ እነዚህን መስፈርቶች አሟልተን ወደስ ስራ ገባን ግን በተደጋጋሚ ያስቆሙናል አህን ደግሞ ጭራሽ ሰው ጭነን እንዳንሰራ አርገውናል ናቲ ቤተሰብ አለን ግብር እንክፍላለን ለጂፒኤስ በአመት 3000-4000ብር ለቁጥጥር እንክፍላክለን ትናንት ፋና ሄደን ነበር የሄድነውም ቅሬታችንን ለሚመለክተው አካል እንዲያደርሱልን መፍቴሄ እንዲሰጠን ነውና መፍትሄ እንድሰጡን ድምጻችንን አሰማልን::
31.9K views10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 12:56:41 የአያት መንደር ነዋሪዎች ያለሙት የሕዝብ መናፈሻ እየፈረሰ ነው!

በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍል ከተማ አያት መንደር የዞን 8 ነዋሪዎች ሕጋዊ ካርታ አውጥተው ያለሙት የሕዝብ መናፈሻ ያለ ምንም ማስጠንቀቂና ሕጋዊ ማስረጃ በትራክተር እየታረሰ መሆኑን ፓርኩን ያለሙት የመንደሩ ነዋሪዎች ገልጸዋል ሲል አዲስ ማለዳ ዘግቧል፡፡

እንደነዋሪዎቹ ገለጻ ከሆነ ከ15 ዓመት በላይ ያለሙት የሕዝብ መናፈሻ ወይም ፓርክ ከነዋሪዎች በተዋጣ ገንዘብ በአረንጓዴ ልማት የተሸፈነ ነው፡፡

ይሁን እንጅ ዛሬ ማለዳ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይዘን ነው የመጣነው ያሉ ፖሊሶች ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ሰራተኞችና አንድ ትራክተር አሰማርተው ፓርኩን እያፈረሱ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ሕጋዊ ካርታ አውጥተው ከ15 በላይ በመናፈሻነት የተጠቀሙት ፓርክ እንደሚፈርስ ምን አይነት ማስጠንቀቂያም ይሁን መረጃ እንዳልተሰጣቸውም ጭምር ነው የተናገሩት፡፡

የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይዘን ነው የምናፈርሰው ያሉት የመንግሥት አካላት ማዘዣውን ለፓርኩ ባለቤት ለሆኑት ነዋሪዎች እንዲሳዩ ቢጠየቁም የፍርድ ቤት ማዘዣ ማሳየት አልቻሉም ተብሏል፡፡

Via Addis Maleda
31.0K views09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 12:55:26
29.3K views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 12:55:18 በህወሓት ቀንበር ስር ያለው የትግራይ ህዝብ በከፋ ባርነት ውስጥ እንደሚገኝ በቅርቡ አምልጠው የመጡት የቀድሞ የስራ ሀላፊ ተናገሩ

#Ethiopia : አሸባሪው ህወሓት የትግራይ ህዝብን በማፈን ክልሉ በከፋ ባርነት ውስጥ እንዲኖር አድርጓል ሲሉ በቅርቡ ከትግራይ ክልል አምልጠው ወደ አማራ ክልል የገቡት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አባል እና የቀድሞ የሰሜን ምዕራብ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር የማነ ሃይለ ገለጹ፡፡

ኢንጂነር የማነ የፌደራል መንግስት ባለፈው ሰኔ ወር 2013 ዓ.ም ለትግራይ ህዝብ የጥሞና ጊዜ በመስጠት ከመቀሌ ለቆ መውጣቱን ተከትሎ ክልሉን የተቆጣጠረው አሸባሪው ህወሓት የጊዜያዊ አስተዳደር በነበሩ አባላት ላይ በርካታ ግፎች መፈጸሙን አስታውሰዋል፡፡

አሸባሪው ህወሓት የትግራይ ህዝብ ፈርቶት እንዲኖር፣ ሞራል እንዲያጣ እና የክልሉ ወጣቶች ባላቸው እውቀት ህዝብን እንዳያገለግሉ ከማሰብ የሚመነጭ የማፈን እና ሌሎች ዘግናኝ ግፎችን እየፈጸመ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አባላት በነበሩት አመራሮች እና ግለሰቦች ላይ የተጠና ግድያ መፈጸማቸውን ነው የገለጹት፡፡

ለዚህ ዕኩይ ተግባሩም ሲቪል መስለው የሚንቀሳቀሱ ገዳይ ቡድኖችን ማሰማራቱን ጠቁመው፥ እሳቸውም ከዚህ ቡድኑ ግድያ ማምለጣቸውን ተናግረዋል፡፡

የትግራይ ህዝብ ከተቀረው ወንድም የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲነጠል መደረጉን የገለጹት ኢንጂነር የማነ፥ አሸባሪው ህወሓት “አራት ኪሎ እገባለሁ” በሚል አይኑን ጨፍኖ በአማራ እና አፋር ክልሎች በለኮሰው ጦርነት የትግራይ ከተሞች በጦርነቱ ምክንያት አካላቸው የጎደሉ ወጣቶች መኖሪያ ማዕከል ሆነዋል ብለዋል፡፡

በዚህ ሳቢያም አዲግራት፣ ሽረ እና አክሱም ከተሞች በቁስለኛ እና አካላ ጉዳተኛ ወጣቶች የተሞሉ ከተሞች መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡

በጦርነቱ ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወጣቶችም መቀሌ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና ሆስፒታሎች እንደሚገኙ ነው ያብራሩት፡፡

በጦርነቱ ወጣቶች ላይ የደረሰው የአካል ጉዳት እጅግ የሚዘገንን መሆኑን በመግለጽ፥ የተጎጂ ቤተሰቦች ከፍተኛ ስቃይ እና ሀዘን ውስጥ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡

ስለሆነም በአሸባሪ ህወሓት አገዛዝ የተማረረው ህዝብ ህይወቱን ለማዳን ሲል ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ወደ አጎራባች ክልሎች እያመለጠ እንደሚገኝ ነው ኢንጂነር የማነ የተናገሩት፡፡

ይሁን እንጂ ከክልሉ ወጥተው ወደ አጎራባች ክልሎች የሚፈናቀሉ ዜጎችን የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች መንገድ ላይ በማገት ችግር እየፈጠሩባቸው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በዚህም የተፈናቃዮችን ንብረት እና ገንዘብ ከመዝረፍ ባለፈ ሴቶችን በመድፈር፣ ገንዘብ ከሌላቸውም ወደ መጡበት መልሰው በማሰር እንግልት እያደረሱባቸው መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በአንጻሩ ከአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች እገታ አልፈው ወደ አማራ ክልል ለመግባት እድሉን ያገኙ ተፈናቃዮች በክልሉ በሚገኙ የጸጥታ አካላት መልካም አቀባበል እየተደረገላቸው መሆኑን አውስተዋል ።

አሁን ላይም በአሸባሪው ህወሓት ቡድን ቁጥጥር ስር የሚገኘው የትግራይ ክልል ህዝብ በከፍተኛ ባርነት ውስጥ ይገኛል ሲሉ ነው ኢንጂነር የማነ ያስገነዘቡት፡፡
28.2K views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 12:48:39 ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚዎችን ተጠያቂ ማድረግ እንድትጀምር የአውሮፓ ህብረት አሳሰበ

ተወካዩ የኢሰመኮ እና የተመድን የጋራ የምርመራ ሪፖርት የአውሮፓ ህብረት እንደሚቀበለው ተናግረዋል

የአውሮፓ ህብረት ልዩ የሰብዓዊ መብት ተወካይ ኢሞን ጊልሞር በኢትዮጵያ የሶስት ቀናት ጉብኝት አድርገዋል

ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚዎችን ተጠያቂ ማድረግ እንድትጀምር የአውሮፓ ህብረት አሳሰበ፡፡

በኢትዮጵያ የሶስት ቀናት ጉብኝት አድርገው ወደ ብራስልስ የተመለሱት የህብረቱ ልዩ የሰብዓዊ መብት ልዩ ተወካይ ኢሞን ጊልሞር ጉብኝታቸውን የተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ኢሞን ጊልሞር የህብረቱ የኮሎምቢያ ልዩ የሰላም ተወካይም ነበሩ፡፡

በመግለጫው በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ዳይሬክተር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) እና ሌሎች የፌደራል ተቋማት መሪዎች ጋር ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

የተመድ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በጋራ ሆነው ያጠኑት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምርመራ ጉዳይ፣ የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን እና የሰብዓዊ መብት ድጋፎች፤ በሶስት ቀናት የአዲስ አበባ ቆይታቸው ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የመከሩባቸው ዋነኛ አጀንዳዎች ናቸው እንደ ጊልሞር ገለጻ፡፡

ተወካዩ ኢሰመኮ እና የተመድ ሰብዓዊ መብት ባሳለፍነው ዓመት ይፋ ያደረጉት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የጋራ ምርመራ ሪፖርትን የአውሮፓ ህብረት እንደሚቀበለው ተናግረዋል፡፡

ይሁንና የጋራ ምርመራ ሪፖርቱ ግኝቶች ወደ ተግባር አልተቀየሩም፣ አጥፊዎችም ወደ ተጠያቂነት አልመጡም የሚሉት ልዩ ተወካዩ በዚህ ምርመራ መሰረት ዜጎችን በግፍ የገደሉ፣ አስገድደው የደፈሩ፣ የህግ ስልጣን ካለው አካል ውጪ ሰዎችን የሰወሩ እና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የፈጸሙ ሁሉ ሊጠየቁ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ በግጭቶች እና በድርቅ ምክንያት 13 ሚሊዮን ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የአውሮፓ ህብረት መረጃ አለው ያሉት ጊልሞር ህብረቱ በተለይም በአማራ፣ በትግራይ፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በሶማሊያ ክልሎች የሰብዓዊ ድጋፍ እንደሚያደርግም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ወደ ትግራይ ክልል ግጭቶችን በማቆም ለተጎጂዎች የሰብዓዊ መብት ድጋፍ ያለምንም ገደብ እንዲደርስ እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉም አክለዋል ልዩ ተወካዩ፡፡

ኢሰመኮ ባሳለፍነው ሳምንት በፌደራል መንግስት እና በህወሓት መካከል ያለው መካረር እየጨመረ መምጣቱን ገልጾ በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይነሳ የኢትዮጵያ የልማት አጋሮች ተጽዕኖ እንዲያደርጉ አሳስቦ ነበር፡፡

ጊልሞር በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይነሳ ህብረቱ ምን ሊያበረክት ይችላል? በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄም "በጦርነት የሚፈታ ችግር የለም፣ ተጨማሪ ዜጎች ለሞት እና ጉስቁልና ሊዳረጉ አይገባም ሁሉም አካላት ችግሮቻቸውን በውይይት ሊፈቱ ይገባል" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል በኮሎምቢያ ከፋርክ አማጽያን ጋር የተደረሰውን ስምምነት እንደማሳያ በማንሳት፡፡

በሂደት ላይ ያለው ሃገራዊ የምክክር መድረክ 27ቱም የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በበጎ እንደሚያዩት የተናገሩት ልዩ ተወካዩ በዚህ መድረክ ላይ ሴቶች እና ወጣቶችን ማሳተፍ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ጊልሞር በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከህወሓት ባለስልጣናት ወይ ተወካዮቻቸው ጋር ተገናኝተው እንደሆነ ለቀረበላቸው ጥያቄ የፌዴራል መንግስቱን እንጂ የህወሓት ባለስልጣናትን ሊያገኙ እንዳልመጡ በመጠቆም አላገኘሁም ሲሉ መልሰዋል፡፡
26.4K views09:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 12:45:07
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት 10 ወራት 282 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን ገለጸ፡፡

የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት አስር ወራት 360 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 282 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተነገረ፡፡

ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥም 168 ነጥብ 7 ቢሊየን ብሩ ከአገር ውስጥ ገቢ ታክስ የተገኘ ሲሆን፥ 113 ነጥብ 8 ቢሊየን ብሩ ደግሞ ከወጪ ንግድ ቀረጥና ታክስ የተገኘ ገቢ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው ጠቁመዋል፡፡

በዚህም የእቅዱን 93 ነጥብ 1 በመቶ ማሳካት መቻሉን ነው አቶ ላቀ በሪፖርታቸው ያመላከቱት፡፡

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት እያካሄደ በሚገኘው 8ኛ መደበኛ ጉባዔ የገቢዎች ሚኒስቴርን እና የተጠሪ ተቋማቱን የ2014 በጀት ዓመት የ10 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እያዳመጠ ነው፡፡
25.9K views09:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ