Get Mystery Box with random crypto!

Free Education Ethiopia ✔️︎

የቴሌግራም ቻናል አርማ free_education_ethiopia — Free Education Ethiopia ✔️︎ F
የቴሌግራም ቻናል አርማ free_education_ethiopia — Free Education Ethiopia ✔️︎
የሰርጥ አድራሻ: @free_education_ethiopia
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 39.06K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Student’s Center
Our groups different grades
@EthioGrade6
@EthioGrade7
@EthioGrade8
@EthioGrade9
@EthioGrade10
@EthioGrade11
@EthioGrade12
Online school bot
@Education_Ethiopia_Bot
📮For paid promotion @Free_Education_Ethiopia_Bot

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-09-22 21:37:05
ለ12ተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ተፈታኞች መልካም ዜና

ባሎት አጭር ግዜ የተሳካ ጥናት
በፈተናው ከፍተኛ ዉጤት ለማስመዝገብ
ሁሉም የት/ት አይነቶች ከበቂ ማብራሪያ በ አንድ የያዘ
የረጅም ግዜ ልምድ ባላቸዉ ብቁ መምህራን የተዘጋጀ
መተግበሪያውን በስልኮ በቀላሉ ከ playstore ያዉርዱ
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.exam_time.exam

ቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀላሉ https://t.me/+gHu0kXxt6MIwN2Vk

መተግበሪያውን ለመጠቀም የሚያስችል መመርያ ዩትዩብ ቻናላችን ላይ ያገኛሉ



Recommend by free education Ethiopia
5.6K viewsRBST, 18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 07:35:52 የአዲስአበባ ከተማ መስተዳድር ለተማሪዎች በነፃ የሚያከፋፍላቸዉ ደብተሮች በህገወጥ መንገድ በሱቆች በመሸጥ ላይ ናቸዉ

የአዲስአበባ ትምህርት ቢሮ በበኩሉ ወላጆች ለህግ አካላት ጥቆማ ያድርሱ ብሏል

የአዲስአበባ ከተማ መስተዳድር የሚያሳትማቸዉ ደብተሮች በሱቆች በመሸጥ ላይ መሆናቸዉን ብስራት ራዲዮ ተመልክቷል። ደብተሮቹ በመንግስት ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ተማሪዎች በነፃ የሚከፋፈሉ ቢሆንም ፤ በአሁኑ ሰዓት እስከ 50 ብር ድረስ በሱቆች በመሸጥ ላይ ናቸዉ።

ብስራት ራዲዮ ጉዳዩን በሚመለከት የአዲስአበባ ከተማ መስተዳድር የትምህርት ቢሮን ያነጋገረ ሲሆን ድርጊቱ ህገወጥ ከመሆኑ በተጨማሪ ይህን በሚያደርጉ የንግድ መደብሮች ላይ ወላጆች ጥቆማ ይስጡኝ ብሏል።

የከተማ መስተዳደሩ ምገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አንቺነሽ ተስፋዬ ለጣቢያችን እንደተናገሩት ፤ መስተዳድሩ በከፍተኛ በጀት የሚያሳትማቸዉ እኚህ ደብተሮች ለተማሪዎች በነፃ የሚከፋፈሉ እንጂ ለንግድ የሚዉሉ ባለመሆናቸዉ በድርጊቱ የሚሳተፉ አካላትን አስጠንቅቀዋል። እንደ ኃላፊዋ ገለፃ እያንዳንዱ ደብተር ከበስተጀርባው የራሱ የሆነ መለያ ቁጥር ያለዉ በመሆኑ በየትኛው አምራች የተመረቱት ደብተሮች በገበያዉ ላይ አሉ የሚለዉን እናጣራለን ብለዋል።

አሁን በገበያዉ ላይ ያሉ ደብተሮች፤ ከዚህ ቀደም ለከተማ መስተዳድሩ ደብተሮቹን ለማቅረብ ተስማምተው ከጥራት በታች ናቸዉ ተብለዉ ከጨረታዉ የታገዱ እና ህጋዊ እርምጃ የተወሰደባቸዉ ሊሆኑ እንደሚችሉም ጠቁመዋል።

ኃላፊዋ አክለዉም ትምህርት ቢሮዉ ፤ ለተማሪዎች ተብለዉ የሚመጡ ደብተሮችን የሚሸጥም ሆነ የሚያዘዋዉር እንዲሁም የሚገዛ አካል በህግ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተዋል።

በተያዘዉ ዓመት ደብተር እስካሁን ያልደረሳቸዉ ተማሪዎች እንዳሉ ለኃላፊዋ ጥያቄ ያነሳን ሲሆን ፤ አቅርቦቱ ከዉጭ ሀገር በመሆኑ እና የዘንድሮው የትምህርት ዘመን ጅማሮ ከተያዘው የግዜ ሰሌዳ የፈጠነ በመሆኑ መጓተቱ ከዚህ የመነጨ ነው ብለዋል። በቀጣይ አንድ ሳምንት ዉስጥ ችግሩ እንፈሚቀረፍ እና ለሁሉም ተማሪዎች ደብተር እንደሚከፋፈል ወ/ሮ አንቺነሽ ተስፋዬ ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
7.0K viewsπ, 04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 21:15:48
ለ12ተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ተፈታኞች መልካም ዜና

ባሎት አጭር ግዜ የተሳካ ጥናት
በፈተናው ከፍተኛ ዉጤት ለማስመዝገብ
ሁሉም የት/ት አይነቶች ከበቂ ማብራሪያ በ አንድ የያዘ
የረጅም ግዜ ልምድ ባላቸዉ ብቁ መምህራን የተዘጋጀ
መተግበሪያውን በስልኮ በቀላሉ ከ playstore ያዉርዱ
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.exam_time.exam

ቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀላሉ https://t.me/+gHu0kXxt6MIwN2Vk

መተግበሪያውን ለመጠቀም የሚያስችል መመርያ ዩትዩብ ቻናላችን ላይ ያገኛሉ



Recommend by free education Ethiopia
7.7K viewsRBST, edited  18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 20:44:59 ለተፈታኞች የተፈቀዱ ነገሮች

ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ ይዘው እንዲመጡ እና ግቢ ውስጥ እንዲጠቀሙ የተፈቀዱ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው፡፡

¤ አዲስ ወይም ቀድሞ ለመማርና ለማጥናት ሲጠቀሙበት የነበረ ማስተወሻ ደብተር፣ የትምህርት መጽሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መጽሐፍት፣ ባዶ ወረቀት

¤ ደረቅ ምግቦች ወይም ሰንባች ምግቦች (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቦ ቆሎ፣ ቆሎ….)

¤ ገንዘብ (ብር)፣

¤ የልብስ ወይም የእጅ ቦርሳ፣ የግል ልብስ፣ ጫማ

¤ የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ (ሳሙና፣ ሞዴስ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጥርስ ሳሙና፣ የገላ ማድረቂያ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሽነር፣ ሎሽን፣ ቻፕስቲክ፣ የጸጉር ቅባት፣ የፊት ቅባት)

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
7.7K viewsπ, 17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 10:02:11
Anyone interested in paid promotion.
We got different packages
◇daily
◇weekly
◇monthly
Contact : @Pluviophilegirl116 or @Free_Education_Ethiopia_Bot

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe

Details of the promotion
https://t.me/Free_Education_Ethiopia/2106
8.1K viewsRBST, edited  07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 09:55:11 ሰላም ሰላም ውድ ቤተሰቦች ለተለያዩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለወሰዱ ጥያቄዎች መልስ


ስልክ ይፈቀዳል ወይ

በጭራሽ ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክ አይፈቀድም ።
በመሆኑም ስልክ ቀርቶ በመፈተኛ ክላስ እስክርቢቶ አይፈቀድ  የሚፈቀደው እርሳስ ብቻ ነው ምክንያቱም አንሰር ሽቱ ላይ የ እስክርቢቶ ሰረዝ ከተገኘ ማሽኑ ላያርመው ስለሚችል

በተመሳሳይ ሌሎች ህጎችን ተላልፎ ህግ ከጣሰ ቀላል እና ከባድ በሚባል የቅጣት መስፈርት የሚቀጣ ይሆናል።

የጥፋት አይነቱ ከ አንሰር ሽታችሁ ጋር በ ዲሲፕሊን ፎርም ተያይዞ የሚላክ ይሆናል።

ቀላል   ሲያጠፋ የተገኘበትን ሳብጀክት ብቻ የሚያሰርዝ ሲሆን
ከባድ ሁሉነም እስከ ማሰረዝ ይደርሳል

ካልኩሌተር ይያዛል ወይ

ከ አእምሮ እገዛ ውጪ የምንም መሳሪያ እገዛ ማግኘት አይፈቀድም በጣም ክልክል ነው ።
በመሆኑም ማንኛውም አጋዥ ማሽን ነገር አይፈቀድም

ሰአት መያዝ ይቻላል ወይ

ለሰአት መቁጠሪያ ብቻ የሚያገለግል ሰአት ብቻ ከሆነ እንጂ ማንኛውም ዘመናዊ ሰአት ( ፎቶ የሚያነሳ ስልክ የሚደውል ወዘተ....) አይፈቀድም

ቻሉት እንግዲህ በተመሳሳይ ከ 30 ደቂቃ በላይ አርፍዶ መፈተን አይቻልም።

የስም፣ የፆታ ፣የስትሪም ስህተት ቢኖርስ

id card በምትቀበሉበት ሰአት የተሳሳተ የመሙያ ፎርም በ ርዕሰ መምህር እና ሱፐርቫይዘር አማካኝነት በመሙላት
ማስተካከያ ደብዳቤ ማፃፍ ይገባቸዋል ችላ አይባልም ።

የ 2013 ተፈታኞች ድጋሚ የሚፈተኑት ውጤቱ አንደ አማራጭ ነወይ የሚያዘው

እስካሁን ከ ት/ሚ የመጣ ነገር ባይኖርም የሚያዘው የ ዘንድሮ ፈተናቸው መሆኑን እና አንዳንድ አሳሳች መልክት የሚያስተላልፉትን ከመስማት በመቆጠብ የአሁኑን ጥሩ እንዲሰሩ ምክንያቱም የበለጠው ይያዝ ቢባል እንኳ የአሁኑ ስለሚያዝ የ አሁኑን ጥሩ ለመስራት ሞክሩ።

ከገቡ ቡኋላ መውጣት አይቻልም የ ሀይማኖት ተቋም መሄድ የምንፈልግስ

እንደ ኢትዮጵያ የመጣውን በጋራ መቀበል ነው ።
አንድም ተማሪ ወደ ግቢ ከገባ ቡሃላ በምንም ምክንያት ያለግቢው ፍቃድ አይወጣ፣ አይገባም። ለምሳሌ ህመም ምንምን እንደ ድንገት ብያጋጥማችሁ እዛው ውስጥ ባለው ክሊኒክ #በነፃ መታከም ነው።

በራስ ወጪ ቀድሞ መጓጓዝ የሚፈልግ ይፈቀዳል ወይ

አይቻልም ከ ት/ቤት ለ ዩንቨርስቲ ማስረከብ ያለበት የወረዳው አመራር ስለሆነ የተማሪውን ብዛት ከ ትራንስፖርት ተቋም ጋር በመነጋገር ያዘጋጃሉ

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe
8.2K viewsRBST, 06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 20:27:51 የ ዘንድሮ የ 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ምኑ ለየት ያረገዋል ?


የግል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ፈተናውን ሊያሰሩ አይችልም!

የግል ትምህርት ቤቶች የትምህርት ቤታቸውን ስም ለማስጠራት ሲሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ እንዲሰሩ ተጨማሪ መልስም እንዲሰጣቸው ሲደረግ ሰንብቷል! እስካሁን ድረስ ግቢ ላይ የተዋወኳቸው የግል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ያረጋገጡልኝ ያንን ነው!  ዘንድሮ ማን ሰርቶ ይሰጣቸው ይሆን ማንም! በደምብ ያላጠና የሃብታም ልጅ ከሰረ

ተማሪዎች ስልክ ይዘው አይገቡ ፤ ከግቢ መውጣት አይችሉ ፣ ጉዳዩ ተዘጋ!

የአምናውን ፈተና ብቻ ለማስታወስ ስንሞክር ፈተናውን ከመፈተናቸው በፊት የፈተናው ሙሉ ጥያቄ በ Pdf ፋይል ለግቢ ተማሪዎች ሲላክ እንደነበር አይዘነጋም! የግቢ ተማሪዎች ጥያቄውን  ለዘመድ አዝማድ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እየሰሩ ሲልኩም ነበር!ዘንድሮ ማንም ለማንም አይልክም ፣ ስልክ የለማ! ፤ ውጪ እንኳን ሲወጡ ይሰጣቸዋል እንዳይባል ፤ ማንም ተማሪ ከግቢ ውጪ ዝር ማለት አይችልም! ሰው ይሰራልኛል ፤ የግቢ ተማሪ ሰርቶ ይልክልኛል ብሎ ሲያስብ የነበረ ተማሪ ከሰረ !

ፈተኞችን በሬ እያረዱ የሚያበሉ ፣ የገጠር ትምህርት ቤቶች ከሰሩ!

ከዚህ በፊት በነበሩ ፈተናዎች ላይ selfie እየተነሱ የሚልኩ ተማሪዎች ነበሩ! ኸረ ፈተናው ላይ የሚሳሳሙ ጥንዶች እራሱ ሳይኖሩ አይቀሩም!ምንንም ቁጥጥር የለም እኮ በቃ ገበያ ነው!ይህ ለምንድነው ብለን ስንጠይቅ ለካ ፈታኞቹ በሬ እየታረደላቸው ፤ ጠጅ እያጠጧቸው ነው! የትምህርት ቤት ዳይሬክተር እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ልጆቻቸው እንዲያልፉላቸው ስለሚፈልጉ ፤ ደግሰው ፈተኞቹን ያበሏቸዋል! ፈታኞቹ ጮማቸውን ወጥቀው ወጥቀው ሲደክማቸው እንቅልፋቸውን ሊተኙ ሁላ ይችላሉ ፣ መፈተኛ ክፍል ውስጥ! ኸረ እንደውም አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ሰልፍ ላይ ለፈታኛችሁ ድግስ ስለምንደግስ ሁለት መቶ ሁለት መቶ አዋታችሁ በአለቆቻችሁ በኩል ቢሮ እንድትልኩ ፤ በደምብ ተክራርጃችሁ እንድትሰሩ የሚባሉ እራሱ አሉ በድግስ ለማለፍ ያቀደ የገጠር ተማሪ ጉዱ ፈላ!


ፈተናው ከ በፊቱ ኮድ ነው የበለጠ ነው የሚሆነው ፣ ጎበዝ ተማሪዎች አረፉ!

ከዚህ በፊት በነበሩ ፈተናዎች ላይ ጎበዝ ተማሪ እየተደበደበ መልስ እንዲሰጥ ይደረግ ነበር ፤ ኸረ ሽት የሚነጥቁ ተማሪዎች እራሱ ተማሩ! ዘንድሮ ግን በ 12/8 ኮድ ሲሆን ፣ ሰነፍ ተማሪ ምን ይዋጠው! ፈተናው ሊቀራረብበት የሚችልበት እድል የሞተ ነው! በጉልበቱ የሚመካ ሰነፍ ተማሪ ከዛ አይኑ ፋጥጥ ጥርሱ ግጥጥ ....ቀለም ተማሪዎች መልሱን ግልብጥ

የዘንድሮ ፈተና እጅግ ልዩ ከመሆኑም በላይ ፤ ጎበዝ ተማሪዎች ብቻ የሚያልፉበት ነው! አይኑን እያቃጠለ ያነበበ የደሃ ልጅ ፤ እምባው በውጤቱ ይታበሳል ፤ አቅሙን በሙሉ አሟጦ የተጠቀመ የሃብታም ልጅ እንዲሁ በውጤቱ ይኮራል ፤ የሰራ እና የሰራ ብቻ መልካሙን ፍሬ የሚበላበት ፈተና ይሆናል! ዘንድሮ ውጤት የሚቀርበት ተማሪ በምንም ምክንያት ሊያማሃኝ አይችልም ፣ ሙሉ ሃላፊነቱን እራሱ ይወስዳል! የእናቴ ቀሚስ አደናቀፈኝ ማለት አይሰራም
Via QesemAcademy

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
9.9K viewsπ, 17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 20:03:53
የ 12ኛ ክፍል የመፈተኛ ምደባ

በሁሉም ዩኒቨርስቲ ምደባ የተካሄደ ስሆን በየ አቅራቢያችሁ የሚገኙትን ዩኒቨርስቲ ስር ተመደቧል።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
14.0K viewsπ, 17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 09:31:43 በነገው ዕለት የ2015 የትምህርት ዘመን ይጀምራል።

በዚሁ ዕለት ትምህርት ሚኒስቴር 5 ዓመታት ሲያዘጋጅ የቆየው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መተግበር ይጀምራል፡፡

በሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባው የአዲሱ የትምህርት ስርዓት ከነገ ጀምሮ በኢትዮጵያ በሚገኙ 80 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በሙከራ ደረጃ ይሰጣል።

#ለማስታወሻ - የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ፦

- ከኢንተርናሽናል እና የማህበረሰብ  ትምህርት ቤቶች ውጭ ስርዓተ ትምህርቱ በሁሉም የአገሪቱ ክፍል ባሉ የግል እና  የመንግስት ትምህርት ቤቶች ይተገበራል።

- ግብረ ገብ ፣ አገር በቀል ዕውቀት ፣ ሙያና የቀለም ትምህርት፣ ቴክኖሎጂ፣ ምርትና ተግባር፣ ጥናት እና ምርምር ትኩረት ተደርጎባቸው ይሰጣሉ።

- ከ1ኛ - 6ኛ ክፍል የግብረ ገብ ትምህርት ይሰጣል።

- ለ7ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ራሳቸውን የቻሉ የትምህርት ዓይነቶች ሆነው ይሰጡ የነበሩት ኬሚስትሪ ፣ ባዮሎጂ እና ፊዚክስ " ጄኔራል ሳይንስ " ተብለው ይሰጣሉ። ጆግራፊና ሂስትሪም ተቀናጅተው የሚሰጡ ይሆናል።

- ከ1ኛ - 6ኛ ክፍል ላሉ የክፍል ደረጃዎች ትምህርት በአፍ መፍቻ ቋንቋ ይሰጣል፤ ከ7ኛ ክፍል -12ኛ ክፍል ያሉት ደግሞ ሁሉም ተማሪ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ይማራል።

- ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ያሉት ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ቋንቋን እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ይወስዳሉ።

- 3ኛ ክፍል ላይ ተጨማሪ ቋንቋዎችን መስጠት ይጀመራል፤ በክልሎቹ ውስጥ በስፋት የሚነገረውን #ተጨማሪ_ቋንቋ በመምረጥ ተማሪዎቹ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲወስዱት ይደረጋል።

-  አጠቃላይ ፈተና በክልል ደረጃ 6ኛ ክፍል ላይ እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ላይ ይሰጣል።

- የ7ኛና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች " ኬሪየር ኤንድ ቴክኒካል ኤጁኬሽን " የተባለ ትምህርት ይሰጣቸዋል። የእርሻ ትምህርት፣ አካውንቲንግ፣ ቢዝነስና ጀነራል የሆነውን የሥራና ክህሎት ትምህርት በሙያ ትምህርት ተካቶላቸው ይሰጣቸዋል።

- 11ኛ እና 12ኛ ክፍሎች ላይ ጤና ፣ ግብርና፣ የእርሻ ትምህርት፣ ማኒፋክቸሪንግ፣ ኮንስትራክሽን ፣ ቢዝነስ ፣ አካውንቲንግ የመሳሰሉት የሙያ ትምህርትነቶችን እንዲማሩ ይደረጋል። 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከእነዚህ የሙያ ትምህርቶች ውስጥ የመረጡትን ይወስዳሉ።

- የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍልን እንዲሁም ከ1ኛ - 8ኛ ክፍል ያሉ የተመረጡ 5 የትምህርት አይነቶችን መጸሐፍት ዝግጅት ትምህርት ሚኒስቴር ያከናውነዋል ፤ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ያለውን የትምህርት መፀሐፍት ክልሎች በራሳቸው ባህልና አካባቢያዊ ሁኔታ ቃኝተው ያዘጋጁታል።
Via. Tikvah
መረጃው ከትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ / ኢፕድ የተወሰደ ነው።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
14.1K viewsπ, edited  06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 22:07:37 በአማራ ክልል በቅርቡ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች የተላለፈ አስቸኳይ መልዕክት

የ2014 /2015 ዓ.ም በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ፈተናው እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወሳል፡፡

በመሆኑም ተፈታኝ ተማሪዎች ቀድመው ሊዘጋጁባቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡

1. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ማዕከልም ይሁን በመፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ መገኘት ግዴታ በመሆኑ አድሚሽን ካርድ ፎርም ከሞሉበት ትምህርት ቤት እና ወረዳ በአካል በመገኘት እስከ መስከረም 10/2015 ዓ.ም እንዲረከቡ፡፡

2. በአድሚሽን ካርዱ ላይ የስም፣ የስትሪም እና የጾታ ወዘተ..ስህተት ካለ በአስቸኳይ ለትምህርት ቤቱ እና ለወረዳው ሪፖርት እንድታደርጉ በጥብቅ እያሳሰብን ይህንን የማያደርጉ ተማሪዎች ካሉ ፈተና ለመውሰድ እንደሚቸገሩ፤

3. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ የትምህርት ቤት ወይም የኗሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት የሚገባ መሆኑ፤

4. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ጊዜ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዘው መገኘት ያለባቸው መሆኑ ከዚህ ዉጭ ሌሎች ቁሳቁሶችን በዩኒቨርሲቲ ግቢ እና በመፈተኛ ክፍል መያዝ የተከለከለ መሆኑ፤

5. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ፣ ወረዳው እና ዞኑ በሚያዘጋጀው የጉዞ ፕሮግራም መሰረት ወደ መፈተኛ ዩኒቨርሲቲ የሚጓዙ መሆኑን በመረዳት ዝግጅት ማድረግ ያለባቸው መሆኑን፤

6. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲሄድ አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ልብስ ይዞ የመምጣት ይኖርባቸዋል፡፡

ይህን መረጃ ሸር በማድረግ ለተማሪዎችና ተማሪ ወላጆች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት እንዲደርስ ትብብራችሁን እንድታደርጉ በተፈታኝ ተማሪዎች ስም ቢሮው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
ባህርዳር

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
13.9K viewsπ, edited  19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ