Get Mystery Box with random crypto!

ሰላም ሰላም ውድ ቤተሰቦች ለተለያዩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለወሰዱ ጥያቄዎች መልስ ስልክ | Free Education Ethiopia ✔️︎

ሰላም ሰላም ውድ ቤተሰቦች ለተለያዩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለወሰዱ ጥያቄዎች መልስ


ስልክ ይፈቀዳል ወይ

በጭራሽ ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክ አይፈቀድም ።
በመሆኑም ስልክ ቀርቶ በመፈተኛ ክላስ እስክርቢቶ አይፈቀድ  የሚፈቀደው እርሳስ ብቻ ነው ምክንያቱም አንሰር ሽቱ ላይ የ እስክርቢቶ ሰረዝ ከተገኘ ማሽኑ ላያርመው ስለሚችል

በተመሳሳይ ሌሎች ህጎችን ተላልፎ ህግ ከጣሰ ቀላል እና ከባድ በሚባል የቅጣት መስፈርት የሚቀጣ ይሆናል።

የጥፋት አይነቱ ከ አንሰር ሽታችሁ ጋር በ ዲሲፕሊን ፎርም ተያይዞ የሚላክ ይሆናል።

ቀላል   ሲያጠፋ የተገኘበትን ሳብጀክት ብቻ የሚያሰርዝ ሲሆን
ከባድ ሁሉነም እስከ ማሰረዝ ይደርሳል

ካልኩሌተር ይያዛል ወይ

ከ አእምሮ እገዛ ውጪ የምንም መሳሪያ እገዛ ማግኘት አይፈቀድም በጣም ክልክል ነው ።
በመሆኑም ማንኛውም አጋዥ ማሽን ነገር አይፈቀድም

ሰአት መያዝ ይቻላል ወይ

ለሰአት መቁጠሪያ ብቻ የሚያገለግል ሰአት ብቻ ከሆነ እንጂ ማንኛውም ዘመናዊ ሰአት ( ፎቶ የሚያነሳ ስልክ የሚደውል ወዘተ....) አይፈቀድም

ቻሉት እንግዲህ በተመሳሳይ ከ 30 ደቂቃ በላይ አርፍዶ መፈተን አይቻልም።

የስም፣ የፆታ ፣የስትሪም ስህተት ቢኖርስ

id card በምትቀበሉበት ሰአት የተሳሳተ የመሙያ ፎርም በ ርዕሰ መምህር እና ሱፐርቫይዘር አማካኝነት በመሙላት
ማስተካከያ ደብዳቤ ማፃፍ ይገባቸዋል ችላ አይባልም ።

የ 2013 ተፈታኞች ድጋሚ የሚፈተኑት ውጤቱ አንደ አማራጭ ነወይ የሚያዘው

እስካሁን ከ ት/ሚ የመጣ ነገር ባይኖርም የሚያዘው የ ዘንድሮ ፈተናቸው መሆኑን እና አንዳንድ አሳሳች መልክት የሚያስተላልፉትን ከመስማት በመቆጠብ የአሁኑን ጥሩ እንዲሰሩ ምክንያቱም የበለጠው ይያዝ ቢባል እንኳ የአሁኑ ስለሚያዝ የ አሁኑን ጥሩ ለመስራት ሞክሩ።

ከገቡ ቡኋላ መውጣት አይቻልም የ ሀይማኖት ተቋም መሄድ የምንፈልግስ

እንደ ኢትዮጵያ የመጣውን በጋራ መቀበል ነው ።
አንድም ተማሪ ወደ ግቢ ከገባ ቡሃላ በምንም ምክንያት ያለግቢው ፍቃድ አይወጣ፣ አይገባም። ለምሳሌ ህመም ምንምን እንደ ድንገት ብያጋጥማችሁ እዛው ውስጥ ባለው ክሊኒክ #በነፃ መታከም ነው።

በራስ ወጪ ቀድሞ መጓጓዝ የሚፈልግ ይፈቀዳል ወይ

አይቻልም ከ ት/ቤት ለ ዩንቨርስቲ ማስረከብ ያለበት የወረዳው አመራር ስለሆነ የተማሪውን ብዛት ከ ትራንስፖርት ተቋም ጋር በመነጋገር ያዘጋጃሉ

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe