Get Mystery Box with random crypto!

Free Education Ethiopia ✔️︎

የቴሌግራም ቻናል አርማ free_education_ethiopia — Free Education Ethiopia ✔️︎ F
የቴሌግራም ቻናል አርማ free_education_ethiopia — Free Education Ethiopia ✔️︎
የሰርጥ አድራሻ: @free_education_ethiopia
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 38.83K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Student’s Center
Our groups different grades
@EthioGrade6
@EthioGrade7
@EthioGrade8
@EthioGrade9
@EthioGrade10
@EthioGrade11
@EthioGrade12
Online school bot
@Education_Ethiopia_Bot
📮For paid promotion @Free_Education_Ethiopia_Bot

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2022-08-20 13:34:52
የትምህርት ጥራት #ፈተና_በመስጠት ብቻ ይረጋገጣል ?

ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ የመውጫ ፈተና መሰጠት እንደሚጀመር ይታወቃል።

ለመሆኑ ፈተና በመፈተን ብቻ የትምህርት ጥራት ማምጣት ይቻላል ? ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ጉዳይ ምላሽ አለው።

ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ (ኢቲቪ) የተናገሩት ፦

" የትምህርት ጥራት ፈተና ብቻ በመስጠት የሚሳካ ፤ የሚረጋገጥ ነገር አይደለም።

በአጠቃላይ ግን በትምህርት እና ስልጠና ዘርፉ በተለይም በትምህርቱ ዋና ችግር አለ ተብሎ የተለየው ዋና የትምህርት ሴክተሩ ስብራት ነው ተብሎ የተለየው ትምህርታችን ጥራትም ተገቢነትም ጎሎታል።

ስለዚህ አስመርቀን የምናስወጣው በሙሉ ባይባልም የጥራት ፣ የብቃት ችግር አለበት ይሄንን መፍታት ያስፈልጋል።

ለዚህ የሚሆን በሁሉም ደረጃ ከግብዓትም ጋር ከሂደቱም ጋር የሚያያዝ እንደዚሁም ውጤቱን ከማረጋገጥ ጋር የሚያያዝ ስራዎች መሰራት አለባቸው ተብሎ በመንግስት ቁልፍ የሪፎርሞች ተጀምረዋል አንደኛው ከመውጫ ፈተና ጋር የሚያያዝ ነው።

ይሄ የመውጫ ፈተና በዋናነት የሚመለከተው የመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቃንን ነው ሁለተኛ ዲግሪ እና ሌሎችን አይመለከትም የሚጀምረው በ2015 ሰፋ ብሎ ነው እንጂ ከዚህ በፊትም የተጀማመሩ ስራዎች አሉ የተጀመሩ ፕሮግራሞች አሉ።

ዋናው ቁም ነገሩ በግብአት ደረጃ ጥራቱን ማረጋገጥ ያስፈልጋል የምሩቁን ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባውን የመማር ማስተማር ሂደቱ ጥራትን በሚያረጋግጥ መልኩ መምራት እና መስጠት ያስፈልጋል።

በጥሩ ግብዓት ከተደገፈ እና ጥሩ ሂደት ካለው በውጤቱ ማረጋገጥ ይገባል ከሚል መነሻ የተጀመረ የሪፎርም ስራ ነው "
Via Tikvah

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
10.4K viewsπ, 10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 21:24:55
ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እንዲያደርጉ የትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል፡፡

የዩኒቨርሲቲዎች የ2015 ዓ.ም የትምህርት ካላንደር ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ታሳቢ ያደረገ መሆን እንደሚገባው ተገልጿል።

ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 17/2015 ዓ.ም በሁሉም የዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ምንም አይነት መደበኛ ተማሪ እንዳይገኝ እና ለፈተና ማቆያ ቦታ እና የምግብ አቅርቦት ዝግጅት እንዲደረግም ትእዛዝ ተላልፏል።

ከፈተና ደህንነት እና አቅርቦት ጋር በተያያዘ የፈተናውን አሰጣጥና ደህንነት የሚቆጣጠር በዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የሚመራ ዋና ግብረ ኃይል እንዲሁም በካምፓስ ኃላፊ የሚመራ ንዑስ ግብረ ኃይል እንዲደራጅም ሚኒስቴሩ መመሪያ አስተላልፏል፡፡

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
15.1K viewsπ, 18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 23:04:44
ፈተናው በ 42 ዩኒቨርስቲዎች ይሰጣል

ከላይ ባሉት ደብዳቤ ነበር ዩኒቨርስቲዎች እንዲዘጋጁ መልዕክት የተላከላችሁ። ስለዚህ በቅርቡ የ 1ኛ ዙር እና 2ኛ ዙር ተፈታኞች ስም ዝርዝርም በቅርቡ ይለካል ተብሏል።

እስካሁን ባለን መረጃ ተማሪዎች አቅራቢያቸው ባለው ዩኒቨርስቲ እንደሚፈተኑ ነው። ከክልላቸው ውጪ የሚለው መረጃ የተረጋገጠ አይደለም።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
15.5K viewsπ, 20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 16:04:17
#MoE

" የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 /2015 ዓ/ም ጀምሮ በ2 ዙር እንዲሰጥ ታቅዷል " - ትምህርት ሚኒስቴር

የ2ዐ14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች እንዲሰጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡

ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ #በሁለት_ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈርሞ ለ42 ዩኒቨርሲቲዎች በተላከውን እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትክክለኛነቱን ባረጋገጠው ደብዳቤ መመልከት ችለናል።

በዚሁ መሠረት ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ዩኒቨርስቲዎች ፦

1. ምንም አይነት የመደበኛ ተማሪ በግቢ እንዳይኖር እንዲያደርጉ፤

2. በቀጣይ በሚገለጸው ተማሪ ቁጥር ልክ ምግብ እንዲቀርብ ዝግጅት እንዲያደርጉ፤

3. ለፈተናዎች ማቆያ ቦታ አንዲዘጋጅ እና

4. የፈተናውን አሰጣጥና ደህንነት የሚቆጣጠር በፕሬዚዳንት የሚመራ ዋና ግብረ-ኃይልና በየካምፓሶቹ በዲን /ካምፓስ ኃላፊ የሚመራ ንዑስ ግብረ-ኃይል እንዲያደራጁ መልዕክት ተላልፎላቸዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች የ2ዐ15 የአካዳሚክ ካላንደር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ወቅት (ከመስከረም 28 - ጥቅምት 17) ታሳቢ በማድረግ እንዲያዘጋጁ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አሳስበዋል።
Via Tikvah

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
13.6K viewsRBST, edited  13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 20:54:15
" አዲሱ ስርዓተ ትምህርት "

የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ተሞክሮ የተጠናቀቀ ሲሆን ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ስራ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።

ክልሎች አስፈላጊ መፅሀፍትና ቋንቋ የመተርጎም ስራ እየሰሩ ሲሆን በፍጥነት ወደ መፅሀፍ የማሳተም ስራ እንዲገባ እየተሰራ ነው ተብሏል።

በዚህም ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት (ኤለመንተሪ) ካሪኩለም ስራ ላይ ይውላል።

በተመሳሳይ በቀጣይ ዓመት የሁለተኛ ደረጃ ካሪኩለም የሙከራ ስራ በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ላይ የሚሞከር ሲሆን 2016 ዓ/ም ላይ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።

Via Tikvah

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
11.9K viewsπ, 17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 10:24:49 ማንኛውም የግል ትምህርት ቤት መፅሃፍም ሆነ ደብተር መሸጥ እንደማይችል ማሳሰቢያ ተሰጠ

አንድ የትምህርት ተቋም ፍቃድ የተሰጠው ለማስተማር እንጂ፤ መጽሐፍም ሆነ ደብተር ለመሸጥ አይደለም ሲል የ #አዲስአበባ ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል።

የባለስልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፍቅርተ አበራ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት ማንኛውም የግል ትምህርት ቤቶች ከመመሪያ ውጪ ያልተገባ ክፍያ አስከፍለው በተገኙ ተቋማት ላይ ርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል።።

በመመሪያ አተገባበሩ ላይ የተለያዩ ጥቆማዎች እየደረሱ እንደሚገኝም ኃላፊዋ አክለዋል። በመመሪያ አተገባበሩ ላይ ከመጡት ጥቆማዎች ውስጥ አንዳንድ ተቋማት የምዝገባ ክፍያ መጨመር፣ በዓይነት መቀበል ለአብነት እሽግ ወረቀት እና የመፀዳጃ ቤት የንፅህና እቃዎችን የሚጠይቁ እንዳሉበት ገልፀዋል።

በተጨማሪም ባልተፈቀደ ክፍያ ጭማሪ እያደረጉ ያሉ የትምህር ተቋማት እንደሚገኙ ጥቆማ ደርሶናል ወርደን እናስተካከልን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ማንኛውም የግል ትምህርት ቤቶች ከመደበኛ ክፍያ ውጪ በየትኛውም መልኩ ክፍያ ማስከፈል አይቻሉም፤ አንድ የትምህርት ተቋም ፍቃድ የተሰጠው ለማስተማር እንጂ መጽሐፍም ሆነ ደብተር ለመሸጥ አይደለም ብለዋል።ከተሰጠው ፍቃድ ውጪ ሲንቀሳቀስ በሚገኝ ተቋም ላይ ርምጃ ይወሰድበታል፤ የሰበሰበውን ገንዘብም ሆነ ማንኛውንም አይነት ቁሳቁስ እንዲመልስ ይደረጋል ሲሉ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፍቅርተ አበራ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
13.3K viewsπ, 07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 22:50:21 ማሳሰቢያ

ለሁሉም የትምህርት ተቋማት
አዲሱ ስርዓተ ትምህርት አተገባበር በተመለከተ አጭር ማብራሪያ


አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በ2015 ዓ.ም ጀምሮ ከ1ኛ_8ኛ ክፍል ተግባራዊ ይደረጋል።

አዲሱ የመፀሀፍት ህትመት እንዳለቀ ለትምህርት ቤቶች ይሠራጫል

በሳምንት የሚሠጠዉ የክ/ግዜ ብዛት 35 ነዉ።

የክፍለ ግዜ ስርጭት በቅርቡ ይላካል

7ኛ እና 8ኛ ክፍል ICT ትምህርት ስለሚሰጥ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይገባል።

ቅድመ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አዲሱ ስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች ይካሄዳል።

ነባሩን ስረዓተ ትምህርት መፀሀፍት በ2015 ዓ.ም ማስወገድ አይቻልም ።አወጋገዱን በተመለከተ ትምህርት ቢሮ አቅጣጫ ያስቀምጣል።

አዲሱ የስረዓተ ትምህርት መፀሀፍ ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ለመምህራን የማስተዋወቅ ስራ ይሠራል።ቀኑ ወደፊት ይገለጻል።
የግል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከነሀሴ 3 ጀምሮ ከአዲስ አበባ ትምሀርት ቢሮ መፀሀፍ መግዛት ይችላሉ።

Via የካ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት
@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
14.1K viewsπ, edited  19:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-08 22:28:41
#የትምህርት_እድል

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ8ኛ ወደ 9ኛ ክፍል ያለፉ ተማሪዎች አወዳድሮ ለማስተማር እንደሚፈልግ ገልጿል።

ከታች የተዘረዘሩት ሲሆኑ መስፈርቶቹን የምታሟሉ ተማሪዎች ተመዝግባችሁ መወዳደር ትችላላችሁ።

ሀ/ የውድድር መስፈርቶች

1ኛ. ክልላዊ የ8ኛ ክፍል አማካይ ውጤት (average) (ጥሬ ማርክ) ለወንድ 78 እና ከዛ በላይ ለሴት 75 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገበ / ያስመዘገበች

2ኛ. ለተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርቶች ከፍተኛ ፍላጎት ያለው/ያላት 10ኛ ክፍል ካጠናቀቀ በኋላ በተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ መቀጠል የሚፈልግ/የምትፈልግ

ለ. ዝርዝር መረጃ

• የምዝገባ ቀን ከ09/12/14 - 13/12/14
• የምዘገባ ቦታ-በሳይንስ ሼርድ ካምፓስ፡ በቀድሞው ቀዳማዊ ምኒልክ የመጀመሪያ ት/ቤት፡፡ ከአራዳ ክ/ከተማ ፊት ለፊት
• የምዝገባ ሰዓት ከረፋዱ 3፡00 - ቀኑ 10:00

ሐ/ ተወዳዳሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ

• ክልላዊ የ8ኛ ክፍል ውጤት የሚገልጽ ዋናውንና 1 ፎቶ ኮፒ
• የመመዝገቢያ ብር 400
• አንድ ክላሰር ይዛችሁ ተገኙ

መ. ተጨማሪ መረጃ

• የጽሑፍ ፈተና የሚሰጥበት ቀን 18/12/14 ከቀኑ 7፡30 - 10፡30
• ፈተና የሚሰጥበት ቦታ በካምፓሱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ነው ተብሏል።

ት/ቤቱ ጎበዝ ተማሪዎች በማፍራት በሀገሪቱ ውስጥ አሉ ከሚባሉና በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናዎችም እጅግ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ያፈራ ት/ቤት ነው።

ለአብነት በ2013 ዓ/ም ብሄራዊ ፈተና 78 ተማሪዎችን አስፈትኖ 42 ተማሪዎች ከ600 በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።

በኢትዮጵያ ትልቁ ውጤት የመጣውም 659 ከዚሁ ሲሆን በት/ቤቱ ዝቅተኛ ውጤት የነበረው 529 ነበር።

@Free_Education_Ethiopia
15.7K viewsπ, 19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 15:03:29
#Update: የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ከመስጠት ባለፈ የፈተና ኩረጀ እና ስርቆትን ለመከላከል በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀው ነበር።

ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ ሲሆን ለጎን ያሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ የሚፈተኑት ፈተና የጥያቄው ዝርዝር (order) በፍፁም የተገናኘ እንዳይሆን ለማድረግ የታሰበ ነው።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዛሬ ባወጣው ማስታወቂያ የፈተና ደንብ ጥሰቶች #በህግ ያስጠይቃሉም ብሏል።
Via Tikvah

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
14.8K viewsπ, 12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 10:58:42 ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ይጀምራል

ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ በሚጀምረው አዲሱ ስርአተ ትምህርት ( ካሪኩለም) መሰረት ለ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናቀቂያ ፈተና መውሰድ የሚጀምሩ ይሆናል።

ለሁሉም ክልሎች ትምህርት ቢሮዎች ከተላከ ፋይል እንደተረዳነው የ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ካላንደር የተገለጸ ሲሆን ከሰኔ 12 እስከ ሰኔ 16 /2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ውስጥ ሁሉም ተማሪዎች የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ሲወስዱ 6ኛ ክፍል ተማሪዎች ደግሞ በልዩ ሁኔታ የ6ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መውሰድ ይጀምራሉ።

በ2009 ዓ.ም የመጨረሻው የ10ኛ ልፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከተሰጠ እና የ10ኛ ክፍል መልቀቂይ ብሔራዊ ፈተና ( ማትሪክ) መሰጠት ካቆመና ተማሪዎች በክፍል ውጤታቸው ብቻ ማለፍ ከጀመሩ ወዲህ ጥቂት ጊዜያት በኋላ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መሰጠት እንደሚጀምር ሲገለጽ ቆይቶ ነበር።

@Free_Education_Ethiopia
Stay Safe!
14.2K viewsπ, 07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ