Get Mystery Box with random crypto!

FastMereja.com

የሰርጥ አድራሻ: @fastmereja
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.93K
የሰርጥ መግለጫ

FastMereja.net

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2024-05-21 16:02:53
5.7K views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-21 16:02:53 በወላይታ ዞን 75 አመራሮች ላይ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተገኘ
#FastMereja
በወላይታ ዞን ፎርጅድ የትምህርት ማስረጃ የተገኙባቸው 75 አመራሮች ላይ ፖለቲካዊ ፣ህጋዊና አስተዳዳራዊ እርምጃ መወሰዱን የዞኑ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት መምሪያ አስታውቋል።

በወላይታ ዞን 1079 አመራሮች የትምህርት ማስረጃ ተፈትሾ75 አመራሮች የትምህርት ማስረጃቸው ፎርጅድ ስለ መሆኑ መረጋገጡን ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን የተናገሩት የዞኑ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ፀጋ ፋንታ ናቸዉ፡፡120 የሚሆኑ አመራሮች የትምህርት ማስረጃ ያገኙባቸው ተቋማት በአሁኑ ሰዓት ሥራ ያቆሙ በመሆናቸው ማስረጃቸውን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራትና አግባብነት ኤጀንሲ እንዲጣራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀሪ አመራሮች የትምህርት ማስረጃ ማጣራቱ ተጠናቆ በሚገኙ ግኝቶች መነሻ ተመሳሳይ የእርምት እርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በማጣራት፥ ህጋዊ እርምጃ በመወሰድ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ማዳን ላይ ዞኑ በትኩረት እየሰራ ነው ተብሏል።

በየተቋማት ሥር ከሰደዱ ችግሮች ውስጥ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ዋናው መሆኑን የተናገሩት ወይዘሮ ፀጋ ይህንንም በማጣራት፥ ህጋዊ እርምጃ በመወሰድ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ማዳን በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል። ባልተፈቀደና ባልተቀረጸ መደብ ላይ የተፈጸሙ ቅጥሮች የተሰጡ ምደባዎችና የደረጃ ዕድገቶች በአስቸኳይ ሊታረሙና እነዚህን ብልሽቶች የፈጸሙ እንዲሁም በህገወጥ ተግባራት ላይ የተሳተፉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰድ እንደሚገባም ተመላክቷል።

ዘገባው የብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ነው።
****
ትክክለኛው የቴሌግራም ገጻችን ይህ ነው
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja
5.7K views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-21 13:22:17
የአስፓልት መንገድን በአፈርና በጠጠር አንዲሁም በጭቃ ያበላሹ 91 የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ተቀጡ
#FastMereja
በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አምስት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የጫኑትን ጭነት ሳይሸፍኑ እንዲሁም የተሸከርካሪ ጎማ ሳያጸዱ በማሽከርከር በመንገድ ላይ ጠጠርና አፈር ያንጠባጠቡና በጭቃ አስፓልት ያበላሹ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን በልዩ ኦፕሬሽን እንዲቀጡ አድርገዋል፡፡

በተለይም በ90 ቀናት የተግባር ክንውን ወቅት የጭነት አገልግሎት የሚሰጡ አሽከርካሪዎች በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ አፈርና ጭቃ ከጎማ ላይ ሳያፀዱ ወደ መንገድ እንዳይወጡ እንዲሁም ከመጠን በላይ ትርፍ አፈርና ቆሻሻ እንዳይጭኑ ተገቢውን ቁጥጥር እዲደረግ በተሰጠ አቅጣጫ መሰረት በየቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከ ግንቦት 1 እስከ 10 ባሉት ቀናት በለሚ ኩራ 38 በቦሌ 36 በአዲስ ከተማ 7 በልደታ 4፣ በቂርቆስ 4 በየካ 2 በድምሩ 91 አሽከርካሪዎች ተቀጥተዋል፡፡

በአጫጫን ጥንቃቄ ጉድለት ጭነትን ሳይሸፍኑ ያንጠባጠቡ እና ከተሸከርካሪዎች ጎማ ላይ ጭቃ ሳያጸዱ አስፓልት መንገድን ያበላሹ እነዚሁ አሽከርካሪዎች የተቀጡት በደንብ 395/2009 በእርከን 1/14 መሰረት ሲሆን ቁጥጥሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የትራፊክ ማኔጅመንት አስታውቋል።
****
ትክክለኛው የቴሌግራም ገጻችን ይህ ነው
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja
5.9K views10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-21 08:43:59
#Tecno #Camon30Pro5G

Tech – art leather ቴክኖሎጂ በመጠቀም እጅግ ዘመናዊ ዲዛይን የተላበሰው አዲሱ Tecno Camon 30 pro 5G ምርጫዎ ያድረጉ!

#Camon30Et #Camon30pro5GEt  #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
5.8K views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-20 22:11:21
"ፖሊሱ ተይዞ ምርመራ እየተደረገበት ነው" የአፋር ፖሊስ
#FastMereja
በማህበራዊ ሚዲያዎች የከባድ መኪና ሹፌር በማስቆም ሲያስፈራራ እና ሲያንገላታ የሚታየው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ምርምራ እየተጣራ እንደሚገኝ የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ቢልኤ አህመድ ገልጸዋል።

ይህ አሽከርካሪ ላይ በግድ መንገደኛ የመጫን ተግባር ከፖሊስ ዲሲፕሊን ውጭ የሆነ ተግባር በመሆኑ የአፋር ክልል ፖሊስ ጉዳዩን በማጣራት ተመጣጣኝ የሆነ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ማረጋገጣቸውን ፋስት መረጃ ከአፋር ፖሊስ ያገኘው ሰምቷል።

ኮሚሽነር ጄነራሉ ይህ ተግባር የህዝብ ልጅ እና በህዝባዊ ወገንተኝነቱ የሚታወቀው የአፋር ፖሊስ እንደማይወክል አሰረድተዋል።
****
ትክክለኛው የቴሌግራም ገጻችን ይህ ነው
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja
6.4K views19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-20 22:01:14 በዲላ ዙሪያ ወረዳ የጅብ መንጋ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ መጠጥ ቤቶች እስከ 12 ሰዓት ብቻ እንዲሰሩ ፖሊስ አስጠነቀቀ።
#FastMereja
ከዚህ በፊት ባልተለመደው መልኩ በዲላ ዙሪያ ወረዳ አንዳንድ አከባቢዎች የጅብ መንጋ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን የገለጹት የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ም/ኢ/ር መሰለ ወንዱ ጀጎ ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ም/እ/ር ይህንን ያሉት በሽጋዶ ቀበሌ ልዮ ቦታ ባፋኖ ተብለው በሚጠራበት አከባቢ ነዋር የሆኑት አቶ አለማዬሁ ጎበና የተባሉ ግለሰብ ግንቦት 11/2016 ዓ/ም አምሽተው ወደ ቤታቸው ስመለሱ በጅብ መንጋ መበላታቸውን በገለጹበት ወቅት ነው፡፡

አቶ አለማየሁ ወደ ቤት ሳይመለሱ በመቅረቱ ቤተሰቦች ፍለጋ በወጡበት ወቅት በመንገድ ላይ ልብስ ጫማና የተለያዩ የሰውነት ክፍል የቀሩ ስጋና አጥንት በማግኘታቸው ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ መሠረት ፖሊስ ባደረጉት ምርመራ ባገኙት ምልክቶች ግለሰቡ በጅብ መበላታቸውን ማረጋገጣቸው የገለጹት አዛዡ በአከባቢው ከፍተኛ የጅብ ጩሄት እንደነበረው ከአከባቢው ማህበረሰብ ማረጋገጥ መቻሉን አስታውቋል፡፡

ህብረተሰቡ የትኛውን ማህበራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ከገበያ በሚመለሱበት ወቅት በጊዜ ወደ የቤታቸው መመለስ እንዳለበት በመግለጽ በም/ቤቱ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ማነኛውም መጠጥ ቤቶች እስከ ምሽቱ 12:00 ስዓት ብቻ መሆኑን ገልጸው ከዚህ ውጭ በሆኑ ግለሰቦች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተናግሯል፡፡

የጅብ መንጋ እንቅስቃሴ ስጋት በመጨመሩ የአካባቢው ነዋሪዎች በጊዜ ወደየ ቤታቸው መግባት እንደለበትና ልጆች የቤት እንስሳትን ስጠብቅ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና ወደ ጫካ ውስጥ እንዳይሄዱ አሳስቧል።

በመጨረሻ በአካባቢው ለረዥም ጊዜያት ጅብ እንደነበሩ የገልጹት ም/እ/ር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በአጎራባች ቀበሌያት መሠል ጥቃት መድረሱን በማንሳት ማህበረሰቡ በጊዜ በመግባት የሚሰጠዉን የጥንቃቄ መልእክት በአግባቡ እንዲተገብርም ጠይቀዋል።

ዲላ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳይ ጽ/ቤት
****
ትክክለኛው የቴሌግራም ገጻችን ይህ ነው
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja
6.3K views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-20 22:01:13
5.6K views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-20 21:48:13
በዚፕ ቁልፍ ሚመጣ የብልት አደጋ
-------
የውንድ ልጅ ብልት አካባቢ ከሚደርሱ አደጋዎች ዋነኛው በሱሪ መዝጊያ ዚፕ የሚመጣ ነው። ይህ ደሞ በብዛት ህፃናት ወንዶች ላይ ተደጋግሞ ይታያል። ለዚህም የህፃናት ልጆች ሃሳብ ወደጨዋታ በመሳብ ላይ ሆኖ ዚፕ ለመክፈት ወይም ለመዝጋት በሚያደርጉት ሙከራ ተደጋግሞ ይከሰታል።

በዚህም ምክንያት ህመም፣ ማበጥ፣ መድማት ከፍ ካለም ቆዳ ውስጥ ገብቶ መቀርቀርን ያመጣል። ቶሎ ካልታከመ ደግሞ ብዙ ጥሩ ያልሆኑ እና ከፍተኛ አደጋ ላይ የሚጥሉ መዘዞችን ያመጣል።

በዚህ ዙሪያ የተሰሩ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ደሞ ቤተሰብ ወይም አሳዳጊ ይህን ሁኔታ ለማስተካከል ሆስፒታል ከመምጣቱ በፊት እዛው ይታገላል። ይህም ለተጨማሪ ስቃይ፣ ጉዳት እና ቶሎ ወደ ሃኪም ቤት ከመሄድ መዘግየትን ይዳርጋል።

ስለዚህ ቤተሰብ ለህፃናት ወንድ ልጆቻችሁ ዚፕ የመክፈትን እና የመዝጋትን ነገር ብትከታተሉና ብታግዙ ሁኔታው ከተፈጠረ ደግሞ ቶሎ ወደጤና ተቋማት ብታመጧቸው ይመከራል።

ዶክተር መላኩ አባይ (Pathologist)
****
ትክክለኛው የቴሌግራም ገጻችን ይህ ነው
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja
6.0K views18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-20 21:04:56
«በስቃይ እና መከራ ነው ያደኩት፣ ጓደኞቼ ሲዝናኑ እኔ እንጀራ እሸጥ ነበር፣ ዘመዶቼ እናቴ እና ልጆቼ ናቸው!» አቶ ከድር ጁሃር
#FastMereja
ከደሃ ቤተሰብ ነው የወጣውት ይለሉ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ከሰይፉ ጋር በነበራቸው ቆይታ "እንጀራ እሸጥ ነበር አባቴ ሌላ ሚስት ሲያገባ ኑሮ አስቸጋሪ ሆኖብን ነበር ጓደኞቼ ሲጫወቱ ሲዝናኑ እኔ እናቴን ለማገዝ ብዬ ቤት ውስጥ ቀርቼ ነበር ብለዋል።

ከእንጀራ ውጪ ሴቶች የሚሰሩትን ጠቅላላ ነገር ሰርቻለሁ የሚሉት አቶ ከድር ጁሃር ይህ ሁሉ የተከሰተው አንድ ቀን እናቴ የኛ ያልሆነ ልብስ ስታጥብ አገኘዋት ይህ ልብስ የማነው ስላት ጎረቤቶቼን ላግዝ ብዬ ነው አለችኝ ግን 20 ብር ሲሰጧት አየሁ ከዛ ቀን በኋላ እናቴ መስራት የለባትም የሚል አቋም ይዤ እኔ መስራት ጀመርኩ ይላሉ። የመጨረሻ እህቴ ስትወለድ እኔ ነኝ ገንፎ እየሰራው ያረስኳት ብለዋል።

«ትናንት እናቴን ብዙ ችግር ስታሳልፍ አንድም ዘመድ ዞር ብሎ አላየንም፣ አሁን ስልጣን ስይዝ ብዙ ሰው መጥቷል እኔ አይገባኝም፣ አሁንም ዘመዶቼ እናቴ እና ልጆቼ ናቸው፣ ነገ ከስልጣን ብወርድ ፊታቸውን ስለሚያዞሩብኝ የሚያዋጡኝ ቤተሰቦቼ ናቸው» ብሏል።
5.9K views18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-20 14:02:56
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በዛሬው እለት ሹመቶች ሰጥተዋል

1. ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣

2. አብረሃም በላይ (ዶ/ር) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣

3. መሀመድ እንድሪስ (ዶ/ር) በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ከግንቦት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተሹመዋል::
    
#PMOEthiopia
6.5K views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ