Get Mystery Box with random crypto!

Zaphnath-paaneah

የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah
የሰርጥ አድራሻ: @zaphnathpaaneah1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 648

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-02-25 22:29:52 የዓመፅ ምሥጢር አሁንም እንኳን ይሠራልና!!

2ኛ ተሰሎንቄ 2
⁶ በገዛ ራሱ ጊዜም ይገለጥ ዘንድ፥ የሚከለክለውን አሁን ታውቃላችሁ።
⁷ የዓመፅ ምሥጢር አሁን ይሠራልና፤ ብቻ ከመንገድ እስኪወገድ ድረስ አሁን የሚከለክል አለ።

የተሰሎንቄ መፅሃፍ በዋነኝነት የሚታወቀው ስለ መሲሁ ዳግም ምፅዐት ስለሚያወራና በተጨማሪም የመጨረሻ ዘመን ምልክቶችን ስለሚያነሣ ነው.....ስለዚህ አማኞች የሆኑ ሁሉ በምን አይነት ዝግጅት ምፅዐቱን መጠበቅ እንደሚገባቸው ያሳስባል....በዚህ መፅሃፍ ላይ ከምናገኘው የመጨረሻ ዘመን ምልክቶች አንደኛው የአመፅ ልጅ(የክህደት ልጅ) መገለጥን ይመለከታል......መሲሁ ከመምጣቱ አስቀድሞ የዐመፅ ልጅ(ሐሰተኛው ክርስቶስ) መገለጡ ግድ ይላል:-

“ማንም በማናቸውም መንገድ አያስታችሁ፤ ክህደቱ አስቀድሞ ሳይመጣና የዓመፅ ሰው እርሱም የጥፋት ልጅ ሳይገለጥ፥ አይደርስምና።”2ኛ ተሰሎንቄ 2፥3

ሐሰተኛው ክርስቶስ አሁን በግልፅ በምድር ላይ መሥራት የማይቻለው ከልካይ በመኖሩ ነው፤ መንፈስ ቅዱስ እና በክርስቶስ ደም የተዋጁ ሁሉ.....ይሄ ማለት ግን የዐመፅ ልጅ የተባለው የዲያቢሎስ መልዕክተኛ አሁን አይሰራም ማለት አይደለም......በአደባባይ አይሥራ እንጂ በምስጢር እየሰራ እንደሆነ መፅሃፍ ቅዱሳችንም ይነግረናል እኛም በግልፅ የምናውቀው ጉዳይ ነው....

አለማችን ላይ እየተደረገ ያለውን ኩነት ነቅተን ብንመለከት ምን ያህል ከሲስተሞች(ኢኮኖሚ፣ ፓለቲካ፣ ቴክኖሎጂ፣ ትምህርት...) ጀርባ የዓመፅ ልጅ በምስጢር እየተንቀሳቀሰና ለጥፋት እየተጋ እንዳለ እናስተውላለን......ጌታችን እነዚህን ልጆች በአለም ሳሉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከአለም እንድታወጣቸው አልለምንም ብሎ ያለው ለዚህ ይሆን??

ተወዳጆች ሆይ የጌታችን መምጣት ከመቼውም ግዜ ይልቅ ወደ እኛ እንደቀረበ እንረዳለን.....ሆኖም ግን ከእግዚአብሔር መንግስት በተቃራኒ ያለው የጨለማው አለም ስርዓት በምስጢር እየሰራ እንደሆነ ልብ ማለት ይገባል......አሁን በምስጢር እየሠራ ያለው የጨለማ መንግስት ወዶ ሳይሆን ከልካይ ስላለበት ነው...ሆኖም ግን አንድ ቀን ማለትም ከመሲሁ መምጣት አስቀድሞ በግልጥ መስራት ይጀምራል.....ይህንን ሁሉ ያልኩት በዘመናችን በድብቅ የሚሰራውን የጥልቁን አለም ምስጢር አውቀን እንድንኖርና ከዐመፅ ስራው ሁሉ በመለየት በፅድቅ እንድናበራ ለማሳሰብ ብዬ ነው....ፀጋ ይብዛልን!!

“ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።”1ኛ ዮሐንስ 5፥19

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
785 viewsYonatan Worku, edited  19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 11:20:40 እግዚአብሔርን አለመጠበቅ፤ የዘመኑ ሁነኛ ተግዳሮት!!

'መጠበቅ' የሚለው ፅንሰ ሃሳብ የሚሰበከውን ያህል ቀላል አይደለም ይልቁንም እልህ አስጨራሽና ትዕግስትን በእጅጉ ይፈታተናል......በተለይ ንፋስና ደመና በሌለበት ከባቢ ላይ ቆሞ ዝናብ ይዘንባል የሚል አይነት ትንቢትን መስማት ብሎም በፅናት መጠበቅ የእውነት ከባድ ነው......ሆኖም ግን መጠበቅ መፅሃፍ ቅዱሳዊ ብቻም ሳይሆን ተፈጥሮዓዊም እንደሆነ መረዳት ይገባል.....እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሲፈጥር በግዜ ዑደት ውስጥ ወደ ፍፅምና የሚያድጉበትን ሥርዓት በመዘርጋትም ጭምር ነው.....ቅዱስ ቃሉ እንደሚነግረን አብርሃም የተባለለት እስኪፈፀም 25 አመት፣ ዮሴፍ 13 አመት፣ ሙሴ ደግሞ 40 አመት መጠበቅ ነበረባቸው....እሱ ብቻ አይደለም ጌታችን ኢየሱስ በምድር በስጋ በነበረበት ግዜ ወደ አደባባይ ወጥቶ በግልጥ የመጣበትን አላማ መከወን የጀመረው ከ30 አመቱ በኃላ ነበር......የምትዘገይ ተስፋ በባህሪዋ ልብን ታሳዝናለች......የተባለልኝና የምኖረው ኑሮ የሰማይና የምድር ያህል ሲራራቅብኝ በጣም ከማዘኔ የተነሣ ወደ ተስፋ መቁረጥ መጥቼ አውቃለሁ....አባታችን አብርሃም ልጅን እንደሚወልድ የተነገረው ተስፋ ላም አለኝ በሰማይ ሲሆንበት እኮ አቋራጭ መንገድን መርጦ ወደ አጋር በመግባት የራዕዩ ወጊና ባላንጣ ለሆነውን ሰው እንዲወለድ ምክንያት እንደሆነ እናስታውሳለን......እግዚአብሔርን መጠበቅ አቅቶን አቋራጮችን ስንጠቀም ከበረከት ይልቅ እግማን፣ ከትርፍ ይልቅ ኪሣራ፣ ከደስታ ይልቅ ደግሞ የማይሽር የልብ ስብራትን ማጨዳችን ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው.......ተወዳጆች ሆይ በተለይ አሁን ባለንበት ማለትም በመጨረሻው ዘመን ትልቁ ተግዳሮታችን መጠበቅ ይመስለኛል.......በአለማችን ላይ የብዙ አመታት ፍርደኞች ሆነው በእስር ቤት እየማቀቁ ያሉት አብዛኞቹ ሰዎች ለደቂቃዎች መታገስና ራሳቸውን መግዛት ባለመቻላቸው በተፈጠረ ወንጀል የገቡበት ነው....ይህም የመታገስን ዋጋ ያመላክታል....ችኩልነት የመጨረሻው ዘመን ምልክት ነው(2ጢሞ 3:4)....እግዚአብሔርን መጠበቅ የለመዱ ሰዎች ግን ክብር፣ በረከት፣ ፍሬያማነት፣ ድል፣ ሞገስ የእነሱ ነው፤ ማንምም ሊወስድባቸው አይችልም....ፀጋ ይብዛልን!!!

“በለሱን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል፥ ጌታውንም የሚጠብቅ ይከብራል።”ምሳሌ 27፥18

“እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።”ኢሳይያስ 40፥31

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
922 viewsYonatan Worku, edited  08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 18:54:30 ለህይወታችን በጣም አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች በቀላሉና በብዛት የመገኘታቸው ጉዳይ...

ሁልግዜ ከሚገርመኝና እግዚአብሔርን ከማመሰግንበት ዋነኛ ጉዳዮች መካከል ለሰው ልጆችም ሆነ ለፍጥረታት በጣም አስፈላጊ የሆነ ነገሮች በቀላሉ የሚያልቁ አለመሆናቸው ነው....ይህ ጉዳይ እንደ አጋጣሚ የሚታይ ሳይሆን አለማችንን ብሎም ዩኒቨርስን በአጠቃላይ እያስተዳደረ ያለው ፍፁም የሆነው መለኮታዊው አርክቴክት መሆኑን በግልፅ ያሳያል.....ውሀንና አየርን እንደምሳሌ ብንወስድ እንኳ ያለ እነዚህ ነገሮች መቼስ በምድር ላይ መኖር እንደማይቻል ይታወቃል.....የአስፈላጊነታሸውን ያህል በቀላሉና በብዛት ይገኛሉ......አስባችሁታል ኦክስጅን እየከፈልን ብንጠቀም ኖሮ??? ....ይህንን እንደመነሻ ተጠቅሜ ዛሬ ለማንሣት የወደድኩት ስለመዳናችን ጉዳይ ይመለከታል....ሁላችንም እንደምናውቀው መዳናችን በግዢ ቢሆን ኖሮ ማናችንም ልንገዛው(afford) አንችልም ነበር.....እግዚአብሔር ይህን ስለሚያውቅ በነፃ ማለትም በእምነት ብቻ እንድናገኝ አደረገ....ይሄ ማለት ግን መዳናችን ርካሽ መሆኑን በጭራሽ አይናገርም.....ሃሌሉያ.....በፀጋው ያዳነንና የመንግስቱ ወራሽ ያደረገን ጌታ ይባረክ!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
885 viewsYonatan Worku, 15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 18:51:49 መፀለይ ስትጀምር ጠላትህ መጨነቅና መፍራት ብቻ ሳይሆን መልቀቅ ይጀምራል!!

የፃድቅ ሰው ጥንካሬ የሚያመልከው አምላኩ ራሱ ነው......ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት መልካምና የሰመረ እንደ ሆነለት ሰው በዚህ ምድር ላይ የተሳካለት ሰው የለም.....መዝሙረኛው ዳዊት በተደጋጋሚ 'አቤቱ ጉልበቴ ሆይ እውድድሃለሁ' እያለ የሚዘምረው በትክክል ጉልበቱና አቅሙ ያለው የት ጋር እንደሆነ ስለገባው ይመስለኛል...

ወደ እግዚአብሔር መገኘት ውስጥ ሮጦ ገብቶ ከፍ ከፍ ማለት እንጂ መዋረድ በፍፁም አይታሰብም.....ምክንያቱም የእግዚአብሔር ስም ማንም የማይቋቋመውና የማያልፈው የፀና ግንብ በመሆኑ ነው.....ሃሌሉያ......በሰማይም ሆነ በምድር እንዲሁም ከምድር በታች የእግዚአብሔርን ስም የበላይነት የሚገዳደር አንዳች ሌላ ስም የለም...

ወደ እግዚአብሔር የፀጋ ዙፋን ሥር በፀሎት በመቅረብ የሰማይን ኃይል መጠቀም ይቻላል.....የሚፀልዩ ሰዎች በዘመናት መካከል ለሰይጣን ራስ ምታትና በሽታ ናቸው.....የጨለማው አለም መንግስት በፀሎት በተጉ ቅዱሳን መካከል እንደፈለገና እንደወደደ መንቀሳቀስና ሃሳቡን ማስፈፀም አይቻለውም.....

ምናልባት በተለያየና መጨረሻ የሌለው በሚመስል መንፈሳዊ ጦርነት ውስጥ እንደገባችሁ የሚሰማችሁ ሰዎች ብትኖሩ መፀለያችሁን ቀጥሉ ስትፀልዩ የጨለማው ኔትወርክ ሁሉ መበጣጠስ ይጀምራል አልፎም ከተዓምራቶቻችሁ ጋር መገናኘት ትጀምራላችሁ፤ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር ከቶ የለምና!!

“እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤”ያዕቆብ 4፥7

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.0K viewsYonatan Worku, edited  15:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 11:02:42 እንባ ማስቀረት ወይስ እንባ ማስቀየር??

ያለ ክርስቶስ ኢየሱስ የሆነ ህይወት የለቅሶና የሰቆቃ መሆኑ ሳይታለም የተፈታና ሁላችንም በተግባር አልፈንበት የምናውቀው እውነት ነው......የሰው ልጅ በዘመኑ እረፍትንና እርካታን እንዲጎናፀፍ የእግዚአብሔር መገኘት ህይወቱን ሊቆጣጠረው ይገባል....መፅሃፍ ቅዱሳችንን በተለይም ዘፍጥረት ምዕራፍ 39ኝን ስናነብ የዮሴፍን የስኬቱ ምስጢር ቁሳቁስ ሳይሆን የአምላክ መገኘት እንደሆነ በግልፅ እንረዳለን..

ዛሬ ለማንሳት የወደድኩት ስለ እንባ ነው....በተለይ በዚህ ጉዳይ ላይ እህቶች አይታሙም፤ ወንዶች ግን ሲቸገሩ ይስተዋላል.......የሆነው ሆኖ ግን ኢየሱስን ከማግኘታችን በፊትም ሆነ በኃላ እንባ ከህይወታችን አይቋረጥም፤ የእንባው ምክንያት ግን በደንብ ይለያያል....

በጌታ ሳንሆን በፊት ወይም በጨለማው አለም አገዛዝ ሥር ባሪያ ሆነን በነበርንበት ግዜ የምናለቅሰው አዝነን፣ ተስፋ ቆርጠን፣ ተጨንቀን፣ ደንግጠን፣ ብቸኛ ሆነን፣ የሚረዳን አጥተን፣ ሰላምና እረፍት አጥተን፣ ግራ ተጋብተንና ተቅበዝብዘን,,,,ምናምን ሲሆን ኢየሱስ ካገኘን በኃላም ቢሆን ማልቀሳችንን አላቆምንም፤ የምናለቅስበት ምክንያት ግን ተለውጧል.....ክርስቶስን የህይወታችን ጌታ አድርገን ከሾምን በኃላ የምናለቅሰው በፍቅሩ ተነክተን፣ በክብሩ ተነክተን፣ ደስታችንን መቆጣጠር አቅቶን፣ ሰላማችንና እረፍታችን በዝቶ፣ የእግዚአብሔር መልካምነት መብዛትና የፍቅሩ ማየል አስደንቆን፣ ምህረት ማግኘታችን(ይቅር መባላችን) ከአዕምሮ በላይ ሆኖብን፣ ስማችንና ታሪካችን መቀየሩ አስገርሞን እንጂ...እንደዚህ አይነት ትኩስ እንባ እንዴት ደስ ይላል...ሃሌሉያ....

የእግዚአብሔር ፍቅር የነካው ሰው ብቻ አሜን ይበል!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
574 viewsYonatan Worku, edited  08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 10:22:14 የወዳጅ ማቍሰል የታመነ ነው፤ የጠላት መሳም ግን የበዛ ነው!!

“የወዳጅ ማቍሰል የታመነ ነው፤ የጠላት መሳም ግን የበዛ ነው።”ምሳሌ 27፥6

ጠቢቡ ሰሎሞን ከተናገራቸውና ለሁላችንም ትምህርት ከሚሆነን ነገር መካከል አንዱ ከላይ የለጠፍኩላችሁ ነው......እስቲ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ክፍሉን እንዴት እንደሚተረጉመው እንመልከት:-

“ከጠላት ደጋግሞ መሳም ይልቅ፣ የወዳጅ ማቊሰል ይታመናል።”ምሳሌ 27፥6 (አዲሱ መ.ት)

በዚህ ክፍል ጠቢቡ መታመንን በሚመለከት ሁለት ነገሮችን ያወዳድራል...ይህም የጠላትን ደጋግሞ መሳም እና የወዳጅን ማቁሰል!!.....ይቀጥልና የወዳጅ ማቁሰል ያለምንም ጥርጥር እንደሚታመን ያስቀምጣል....

ወገኖቼ ሆይ አንድ ማወቅ ያለብን እውነት ቢኖር የሳመን ሁሉ የወደደን ላይሆን ይችላል.....ልክ የሳቀ ሁሉ ከልቡ እየሳቀ እንዳልሆነ እንዲሁም እያለቀሰና እንባውን እንደጅረት እያፈሰሰ ያለም የእውነት ነው ብሎ መደምደም አይቻልም.....በተመሳሳይ ሁኔታ የሰውን እውነተኛ ማንነት ውጫዊውን ገፅታ ብቻ በማየት መናገር ፈፅሞ አይታሰብም.....እንደዛማ ቢሆን አስቆሮቶ ይሁዳ ጌታችንን ግጥም አድርጎ ሲስመው ከአንጀቱ ይመስለን ነበር...

እናስ ካልን በተፈወሰ ሞቲቭ ከወዳጆቻችን የሚደርሱንን አስተያየቶችና ቦክሶች ከጠላቶቻችን አደገኛ ማንቆለጳጰስ በእጅጉ ስለሚሻሉ ለግዜው ባይመቹም የሚያሳድጉን ናቸውና ጠበቅ አድርገን እንያዛቸው እላለሁ እንጂ ምክርና ቦክስ ምናምን ብለን አናጣጥለው...ፀጋ ይብዛልን!!

“የተገለጠ ዘለፋ፣ ከተደበቀ ፍቅር ይሻላል።”ምሳሌ 27፥5 (አዲሱ መ.ት)

“ለመሆኑ የምትበሉበትና የምትጠጡበት ቤት የላችሁምን? ወይስ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን በመናቅ፣ ምንም የሌላቸውን ታሳፍራላችሁን? እንግዲህ ምን ልበላችሁ? በዚህ ነገር ላመስግናችሁን? ፈጽሞ አላመሰግናችሁም።”1ኛ ቆሮንቶስ 11፥22 (አዲሱ መ.ት)

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
786 viewsYonatan Worku, edited  07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 11:21:32 ስለ ወጋችሁ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ስለ ምን ትተላለፋላችሁ?

“እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ እናንተስ ስለ ወጋችሁ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ስለ ምን ትተላለፋላችሁ?”
ማቴዎስ 15፥3

ከላይ የለጠፍኩላችሁ ጥቅስ ጌታ ኢየሱስ ፃፎችና ፈሪሳውያን ለጠየቁት ጥያቄ የመለሰላቸው መልስ ነው......እነዚህ ሰዎች ወደ ኢየሱስ መጥተው ደቀመዛሙርቱን በተመለከተ የክስ ይዘት ያለውን ጥያቄ ይጠይቁታል፤ እንዲህ በማለት:-

“ደቀ መዛሙርትህ ስለ ምን የሽማግሎችን ወግ ይተላለፋሉ? እንጀራ ሲበሉ እጃቸውን አይታጠቡምና አሉት።”ማቴዎስ 15፥2

ፃፎችና ፈሪሳውያን በሚያሳዝን ሁኔታ ለሽማግሌዎች ወግ የሚጠነቀቁትን ያህል እንኳን ለእግዚአብሔር ህግ ግድ አይሰኙም ነበር....አባትንና እናትን ስለማክበር የተቀመጠውን ህግ ትተው እንጀራ ከመበላቱ በፊት መታጠብ ይገባል አይገባም በሚለው ጉዳይ ተይዘዋል.....ይህም ከውስጠኛው ማንነት ይልቅ የውጭው እንደከበደባቸው ያሳብቃል....እስቲ እኛም ብንሆን ራሳችንንና አንዳንድ ድርጊቶቻችንን በቅንነት እንቃኝ.....ምናልባት ከእግዚአብሔር ቃል የምናስበልጣቸው በጉያችን የደበቅናቸው ጉዳዮሽ ካሉን፤ ራሳችንን ብንመረምር ባልተፈረደን ነበር አይደልስ የሚለው ቅዱስ ቃሉ!......ምንም እንኳን የታላላቆቻችንን ወግ ማክበር መልካምና የተወደደ ነገር ቢሆንም ከዛ በላይ ግን ልናውቃቸው የሚገቡን ነገሮች አሉ...አንደኛው የእግዚአብሔር ቃል የመጨረሻ ባለስልጣን መሆኑን ሲሆን ሌላው ደግሞ የትኛውም ወግና ባህል ሊመዘን የሚገባው በዚሁ በፈጣሪ ቃል እንደሆነ ብቻ ነው....

ኢየሱስም ይቀጥልና ግብዝነታቸውንና ለታይታ የሚያፈርጉትን ነገር ትክክል አለመሆኑን በግልፅ በመናገር ይገስፃቸዋል:-

ማቴዎስ 15
⁷ እናንተ ግብዞች፥ ኢሳይያስ ስለ እናንተ፦
⁸ ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤
⁹ የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።

ከማስመሰልና ከትያትረኝነት ህይወት እግዚአብሔር ይጠብቀን!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.5K viewsYonatan Worku, edited  08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 13:10:03 የነቃ ያነቃል፥ ያልነቃ ያንቃል፤

ከእንቅልፍ የምትነሱበት ሰዓት አሁን እንደደረሰ ዘመኑን እወቁ!!

“ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።”ሮሜ 13፥11

መፅሃፍ ቅዱሳችን ዘመኑን ስለማወቅ በተደጋጋሚ ይናገራል.....ለምሳሌ ዘመኑን የሚያውቁ የተባለላቸውን የይሳኮርን ልጆች መመልከት ይቻላል:-

“እስራኤልም የሚገባውን ያደርግ ዘንድ ዘመኑን የሚያውቁ ጥበበኞች ሰዎች የይሳኮር ልጆች አለቆች ሁለት መቶ ነበሩ፤ ወንድሞቻቸውም ሁሉ ይታዘዙአቸው ነበር።”1 ዜና 12፥32

እነዚህ የይሳኮር ልጆች ጥበበኞች ስለነበሩ ዘመኑን በሚገባ ተረድተዋል.....በዚህም ምክንያት እስራኤላውያን በዛ ዘመን ላይ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ያስተምሩ ነበር....ዘመንን የሚያውቁ ብቻ በዘመኑ ውስጥ የታጨቀውን የእግዚአብሔር በረከትና ዕድል እንዲሁም ክብር ጋር መገናኘት ይችላሉ...

ዘመናችን በስኬትና በአሸናፊነትና የታጀበ እንዲሆን ካስፈለገ ዘመኑን በሚገባ መመርመርና ማወቅ አማራጭ የለውም......በርዕሱ ላይ እንደለጠፍኩላችሁ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በአፅንዖት የሚፅፍላቸው ከእንቅልፋቸው የሚነሱበት ሰዓት አሁን እንደሆነና መንቃት እንዳለባቸው ነው.....

ወዳጆቼ ሆይ እንቅልፍ ሲባል እኮ የግድ ዐይን ተጨፍኖ የሚተኛበትን አለም ለማመልከት አይደለም ይልቁንም በክፍሉ ላይ እያወራ ያለው በአዚምና በድንዛዜ ውስጥ ተሸብበው ስለሚንከላወሱት ሰዎች እንጂ......

በምድራችን ላይ እየሆኑ ያሉትን አብዛኛውን ጉዳዮች ብንመለከት ዘመኑ በግልጥ የመጨረሻ መጨረሻ መሆኑን ያመላክታል....ጦርነቱ፣ የመሬት መንቀጥቀጡ፣ ጉስቁልናው፣ አመፁ፣ ፍትጊያው፣ በሽታው ሁሉ ጌታችን ሊመጣ በደጅ እንደሆነ ይመሰክሩልናል....

ስለዚህ ከመንቃትና ከማንቃት ውጪ አማራጭ የለንም....ዘይታችን አልቆ ሙሽራው በድንገት እንዳይመጣብን በፅድቅ ልንነቃና ልንቆም ይገባናል......ለመንቃት ሰዓቱ አሁን ሲሆን ነገን የሚያውቅ ደግሞ አንድዬ ብቻ ነው......

በኢየሱስ ስም እፀልያለሁ የእንቅልፍና የስካር፣ የአዚምና የድንዛዜ መንፈስ ዕብቅ በንፋስ እንደሚጠረግ ከምድሪራችን ላይ የተጠረገ ይሁን...አሜን!!

“ስለዚህ፦ አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።”ኤፌሶን 5፥14

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
794 viewsYonatan Worku, edited  10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 12:56:42 መልካሞችን ቀኖች ሊያይ የሚወድ ምን ያድርግ??

“ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤”1ኛ ጴጥሮስ 3፥10

በረከትን፣ ሰላምን እና የተትረፈረፈ ህይወትን በዘመኑ ማየትን የሚወድ ሰው እንዴት መኖር እንዳለበት መፅሃፍ ቅዱሳችን ያስተምረናል......በመሠረቱ ጤነኛ አስተሳሰብና የተፈወሰ አዕምሮ ያለው ሰው ሁሉ በደስታና በተድላ እንጂ በመቅበዝበዝና በመንከራተት የምድር ቆይታውን አጠናቅቆ መሄድ አይፈልግም.....ነገር ግን እያንዳንዱ ጉዳይ የራሱ የሆነ መርህ አለው......እያንዳንዱ ሰው የራሱ ህይወት ቀራፂ ነው እንደሚባለው ህይወታችንን በምንፈልገው አቅጣጫ እንዲጓዝ የማድረግ መብትም ሆነ ውሳኔ ያለው እጃችን ላይ ነው.......አስተዋይና ዐይኖቹ የተከፈቱለት ሰው ህይወቱን በእግዚአብሔር ቃል ሲመራ ሞኝና ነሆለል ግን በዘፈቀደ ወዲህና ወዲያ ይንከላወሳል.....ለምሳሌ የእግዚአብሔር ቃል ሰው ሁሉ የዘራውን እንደሚያጭድ በግልፅ ይነግረናል ይህም ማለት መልካምን የዘራ መልካምን ፍሬን ክፉውን የዘራም ልክ እንደዘራው ማጨዱ አይቀርም.......ማነው በቆሎ ዘርቶ ስንዴን ገብስን ዘርቶስ ማሽላን የሚያጭደው???.....እናስ ታድያ መልካም ቀኖችንና ህይወትን ሊያይ የሚወድ ምን ያድርግ ብለን ካልን በአጭሩ መልካምን ያድርግ ከማለት ውጪ ምን ልንል እንችላለን??.......ይሄ ግልፅና ቀጥተኛ ነገር ነው.....በተለይ ደግሞ ምላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኮልን ከመናገር ይከልክል የሚለው የጌታ ቃል ሊሰመርበት ይገባል.......በያዕቆብ መፅሃፍም ላይ አንደበት የፍጥረትን ሩጫ እንደሚያቃጥል በአፅንዖት ይነግረናል.....ስለ አንደበት አደገኝነት ያልተረዱ ሰዎች እንደፈለጉ ሲናገሩና ሲያማርሩ ይታያል፤ ህይወታቸው ወደፊት ፈቀቅ አልል ሲል ግን ግራ ይጋባሉ.......መዝሙረኛው አቤቱ ለአንደበቴ ጠባቂን አኑር ብሎ የሚፀልየው ለዚህ ይሆን??.....በኢየሱስ ስም እጅግ ከከበረውና እግዚአብሔር ካቀደልን ታላቅ ፍፃሜ ጋር መገናኘት ይሁንልን!!

ምሳሌ 18
²⁰ የሰው ሆድ ከአፉ ፍሬ ይሞላል፥ ከንፈሩም ከሚያፈራው ይጠግባል።
²¹ ሞትና ሕይወት በምላስ እጅ ናቸው፤ የሚወድዱአትም ፍሬዋን ይበላሉ።

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
694 viewsYonatan Worku, 09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 16:59:45 እግዚአብሔርን ስለማወቅ...

“ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፤ ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፥ ከወልድም በቀር ወልድም ሊገለጥለት ከሚፈቅድ በቀር አብን የሚያውቅ የለም።”ማቴዎስ 11፥27

መቼስ ስለ እግዚአብሔር በማወቅና ራሱን እግዚአብሔርን በማወቅ መካከል ትልቅ ልዩነት አለ.....እግዚአብሔርን በተመለከተ ብዙ መረጃና ማስረጃዎች ከመፅሃፍ ቅዱስ ጥቅሶች ጀምሮ ሊኖሩን ቢችሉም ራሱን እግዚአብሔርን ለማወቅ ግን ማረጋገጫ አይደሉም(ምንም እንኳን ጥቅሶችን ማወቅ ጥሩ ቢሆንም)....አንድ ማወቅ ያለብን መንፈሳዊ ነገር በህይወታችን ላይ የሚጀምረው በልባችን ላይ መለኮታዊ ብርሃን ሲበራ ብቻ መሆኑን ነው....እግዚአብሔር ብርሃን ነው ለእኛም በራልን እንዲል ቅዱስ ቃሉ ከአዕምሮ ዕውቀት አልፎ ልባችን ውስጥ ያልፈሰሰ ሰማያዊ እውነት ህይወታችንን ሊቀይር ከቶ አይችልም......ከላይ በለጠፍኩት ክፍል ላይ እንደሚናገረው ማንም ሰው ከአብ በቀር ወልድን ሊያውቀው እንደማይችልና ከወልድም በቀር ወልድም ሊገልጥለት ከሚፈቅድ በቀር አብን ማንም ሊያውቅ እንደማይችል እንመለከታለን.....ስለዚህ መንፈሳዊ ነገር እንደ ባይሎጂና ኬምስትሪ ሽምድደን ብቻ የምንረዳው ነገር ሳይሆን እግዚአብሔር በገለጠልንና በፈቀደልን መጠን ብቻ የምንረዳው እውነት ነው.....ምንም እንኳ እግዚአብሔር ራሱን በተለያየ መንገድ ለፍጥረታት የገለጠ ቢሆንም በጥልቀት በግላችን እንድናውቀው ግን በትህትና በፊቱ መቅረብ አማራጭ የለውም....አሊያ እያዩ እንደማያዩ እየሰሙ እንደማያስተውሉ እንሆናለን.....በኢየሱስ ስም እግዚአብሔርን እንድናውቀው የውስጥ ዐይኖቻችን ይከፈቱልን(ምንም እንኳን አውቀን መጨረስ ባንችልም)......በምድራችን ላይ እግዚአብሔርን የማወቅ መንፈስ ይፍሰስ....ምድራችን ከታሰረችበትና ከተተበተበችበት እግዚአብሔርን የሚጋርድ ሃይማኖታዊ ሠንሰለቶች ትፈታ.....እውነት መንገድና ህይወት የሆነውንና ብቻውን ወደ አብ የሚያደርሰውን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ይሁንልን....አሜን!!

“መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው።”ዮሐንስ 1፥18

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
933 viewsYonatan Worku, edited  13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ