2023-01-27 11:02:26
እንዴት እናስታርቃቸው??!!
በብሉይ ኪዳን የነበረው የቃልኪዳኑ ታቦት በአሁኑ ግዜ ስለሚገኝበት ቦታና ስላለበት ሁኔታ በተመለከተ መፅሃፍ ቅዱስ እና ክብረ ነገሥት የተባሉት ሁለት መፅሃፍት የተለያየ መረጃ ያቀርባሉ:-
መፅሃፍ ቅዱስ:-
2 ዜና 35
¹ ኢዮስያስም ለእግዚአብሔር በኢየሩሳሌም ፋሲካ አደረገ፤ በመጀመሪያውም ወር በአሥራ አራተኛው ቀን ፋሲካውን አረዱ።
² ካህናቱንም በየሥርዓታቸውም አቆመ፥ በእግዚአብሔርም ቤት ያገለግሉ ዘንድ አጸናቸው።
³ እስራኤልንም ሁሉ ያስተምሩ ለነበሩት፥ ለእግዚአብሔርም ለተቀደሱት ሌዋውያን እንዲህ አለ፦ ቅዱሱን ታቦት የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በሠራው ቤት ውስጥ አኑሩት፤ ከዚህም በኋላ በትከሻችሁ ላይ ሸክም አይሆንባችሁም፤ አሁንም አምላካችሁን እግዚአብሔርንና ሕዝቡን እስራኤልን አገልግሉ፤
ክብረ ነገስት
ምንጭ፤ ‹‹ክብረ ነገሥት ከገጽ ፳፩-፶፭›› ተርጓሚ ሥርግው ገላው በ፲፱፺፬ ዓ.ም. የታተመ
ንጉስ ኢዮስያስ(648-609ከክርስቶስ ልደት በፊት የነበረ የይሁዳ ንጉስ) ሲሆን በእርሱ ዘመን ታቦቱ በእስራኤል እንደነበር ከላይ በለጠፍኩላችሁ የመፅሃፍ ቅዱስ ጥቅስ ላይ ማየት ይቻላል....ክብረ ነገስት ደግሞ ታቦቱ በሰሎሞን ዘመነ መንግሥት(970-931ከክርስቶስ ልደት በፊት የነበረ የእስራኤል ንጉስ) ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ ይናገራል...በመካከላቸው ደግሞ ወደ 300 አመት የሚጠጉ የአመታት ልዮነቶች አሉ!!
እናስ ታድያ ትክክለኛው የቱ ነው
መፅሃፍ ቅዱስ እንደሚነግረን የቃልኪዳኑ ታቦት በኢዮስያስ ዘመን እስራኤል ውስጥ ከተገኘ ከ300 ምናምን አመት በፊት ማለትም በሰሎሞን ዘመን ኢትዮጵያ መጥቷል የሚባለውን ትርክት አያፈርሰውም ወይስ ተመልሶ ወደ እስራኤል ሄዶ ይሆን እስራኤላውያንስ እንደ ዐይን ብሌን የሚያዩት የቃል ኪዳኑ ታቦት ሲወሰድባቸው እንዴት ዝም አሉ
“በበዛችሁም ጊዜ በምድርም ላይ በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በዚያ ዘመን፦ የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም ልብ አያደርጉትም፥ አያስቡትምም፥ አይሹትምም፥ ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም።”
ኤርምያስ 3፥16
የእግዚአብሔር ቃል ግን ባለስልጣን ነው!!
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.5K viewsYonatan Worku, edited 08:02