Get Mystery Box with random crypto!

Zaphnath-paaneah

የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah
የሰርጥ አድራሻ: @zaphnathpaaneah1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 648

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-03-15 09:45:30

376 viewsYonatan Worku, 06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 17:47:00 @ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
@Yoni4Christ
66 viewsYonatan Worku, edited  14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 16:16:48

አይቼዋለሁ ጌታን

እኔም እንዲህ እንዲህ ወግ ደረሰኝ
ከመቅበዝበዝ ጌታ በቃ ሲለኝ
ያ መራራ ህይወቴ ጣፈጠ
በኢየሱሴ ታሪክ ተለወጠ

አይቼዋለሁ ጌታን አይቼዋለሁ
አይቼዋለሁ ኢየሱሴን ለእኔስ ልዩ ነው
እኔ አውቀዋለሁ ጌታን እኔ አውቀዋለሁ
እኔ አውቀዋለሁ ኢየሱሴን ለእኔስ ልዩ ነው

እኔስ ገና ገና በልጅነት
አይቻለሁ የጌታዬን ምህረት
ሲርበኝም ከእጁ በልቻለሁ
ያንን ሁሉ መች እዘነጋለሁ

አይቼዋለሁ ጌታን አይቼዋለሁ
አይቼዋለሁ ኢየሱሴን ለእኔስ ልዩ ነው
እኔ አውቀዋለሁ ጌታን እኔ አውቀዋለሁ
እኔ አውቀዋለሁ ኢየሱሴን ለእኔስ ልዩ ነው

መች ይረሳል ያለፍኩት በሙሉ
አማረብኝ በአንተ በኃያሉ
ያየኝ ሁሉ እንዲህ ተገረመ
ደረቅ በትር ይኽው ለመለመ

አይቼዋለሁ ጌታን አይቼዋለሁ
አይቼዋለሁ ኢየሱሴን ለእኔስ ልዩ ነው
እኔ አውቀዋለሁ ጌታን እኔ አውቀዋለሁ
እኔ አውቀዋለሁ ኢየሱሴን ለእኔስ ልዩ ነው

አይዞህ ባይለኝ ጌታ እሱ ባይረዳኝ
ማንስ ሊጎበኘኝ ማንስ ሊቀርበኝ
በቃ ሲል አበቃ ያዘነውን ልቤን
ጭጋጉ ከፊቴ ይኽው ተገፈፈ
ለእኔስ ብዙ ብዙ
ብዙ አድርጎልኛል
ያደላል ብላችሁ ማን ይቀየመኛል
ከእናት ከአባት በላይ ስለተመቸኝ
እንደሱ ያለ የለም ሁሌ እላለሁኝ
ቢጠማኝም ውሃ ቢርበኝ ምግቤ ነው
በረሀቡ ዘመን ከእጁ በልቻለሁ
ማንም በሌለበት በምድረበዳ ላይ
ምንጭን አፈለቀ ከጥሜም አረካኝ
የሸሹኝ የራቁኝ የተፀየፉኝ
አንቅረው የተፉኝ ጀርባ የሰጡኝ
ጌታ ሲጎበኘኝ እሱ ሲረዳኝ
ጎንበስ አሉ ጎንበስ ወዳጅ ሆኑልኝ
ሁሉ በእርሱ ሆነ/2×
ይህም በእርሱ ሆነ/2×

አንዳች ከእኔ የምለው የለም
ሁሉም በእርሱ ነው/2×

ያ መራራ ከእኔ አለፈ
በእርሱ ነው/2×

ጭጋጉ የተገፈፈው
በእርሱ ነው/2×

ማን ልበለው ምን ልብለው/2×
በምን ቋንቋ በምን አንደበት
ይነገራል የእሱ ደግነት/2×

አይቼዋለሁ/2×
እኔ አውቀዋለሁ/2×

ሰሞኑን ይሄ ይሄ የተኬ መዝሙር ወደ ልቤ ደጋግሞ ይመጣል...ተጋበዙልኝ....ተከስተን ጌታ ይባርከው!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
708 viewsYonatan Worku, 13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 10:33:35 ኢሳይያስ 7
⁵-⁶ ሶርያና ኤፍሬም የሮሜልዩም ልጅ፦ ወደ ይሁዳ እንውጣ እናስጨንቀውም፥ እንስበረውም፥ የጣብኤልንም ልጅ እናንግሥበት ብለው ክፋት ስለ መከሩብህ፤
⁷ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ይህ ምክር አይጸናምና አይሆንም።

በዮናታን ወርቁ
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
84 viewsYonatan Worku, edited  07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 14:53:09 ━━━━━⊱✿⊰━━━━━
600 ደርሰናል

ውድ የቻናሌ ቤተሰቦች በያላችሁበት የጌታ ሰላምና ፀጋ ይብዛላችሁ....ወንድማችሁ ዮናታን ነኝ......በእግዚአብሔር እርዳታ በአጭር ግዜ 600 ሰብስክራይበር ደርሰናል......አሁንም ይህ አገልግሎት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል.....በመሆኑም በየቀኑ የምለቃቸው የእግዚአብሔር ቃል መልዕክቶች ብዙ ሰዎች ጋር ደርሰው እንዲፅናኑና እንዲበረታቱ ሼር ሼር በማድረግ አብረን እንድናገለግል እጋብዛችኃለሁ......ሁላችንም እንደምናውቀው ዘንድሮ ከእግዚአብሔር ቃል ይልቅ አለማዊነት የተቆጣጠራቸው ሶሻል ሚድያዎች እንደ አሸን ፈልተዋል.....በመሆኑም በፅድቅ ተፅዕኖ መፍጠር ከእያንዳንዳችን ይጠበቃል......እስካሁን አብራችሁኝ ለሆናችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ላቅ ያለ ነው.....ሃሳብ አስተያየት ካላችሁ እንደተለመደው በውስጥ መስመር ላኩልኝ.....እወዳችኃለሁ!!!!

@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
@Yoni4Christ
@Yoni4Christ
@Yoni4Christ
━━━━━⊱✿⊰━━━━━
499 viewsYonatan Worku, edited  11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 15:34:45 ከአደገኛ የአድመኝነት መንፈስ ጋር አንተባበር!!

የመፅሃፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አድመኝነትን እንደዚህ ይፈታዋል:-

አድመኝነት=ጠብን፣ ክርክርን፣ መለያየትን መፍጠር ይህም በዓመፅ፣ በትግል፣ ባለመስማማት፣ በመከፋፈል፣ በውድድር ይገለጣል......እንግሊዘኛው ደግሞ 'strife' ይለዋል.

Strife=bitter sometimes violent conflict or dissension,
an act of contention(fight,struggle) for superiority,
division, conflict,,,,,,etc

አድመኝነት አንድ ትልቅ ስብስብን ለማፍረስ ከስብስቡ ውስጥ በእንቢተኝነትና በትዕቢት ብሎ በእኔ አውቃለሁነት በወጡ ሰዎች አማካኝነት ይከናወናል.....ምናልባት በእውነት ሆነ በሐሰት መረጃ ላይ ተመስርቶ የሚደረግ ሊሆን ቢችልም የመነሻ ሃሳቡ(ሞቲቭ) ግን ጠማማ ነው......በነገራችን ላይ ይሄ ጉዳይ በእኛ ሃገር ላይ በእጅጉ ይስተዋላል(በሃገር፣ በቤ/ክን እንዲሁም በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች)

መፅሃፍ ቅዱስ አድመኝነት(ማደም) የሥጋዊነት መገለጫ እንደሆነ ያስተምረናል:-

“ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥”ገላትያ 5፥20

“ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና።”ያዕቆብ 3፥16

“ስመጣ፥ እንደምወደው ሳትሆኑ አገኛችሁ ይሆናል እኔም እንደምትወዱት ሳልሆን ታገኙኝ ይሆናል ብዬ እፈራለሁና፤ ምናልባት ክርክር ቅንዓትም ቁጣም አድመኝነትም ሐሜትም ማሾክሾክም ኩራትም ሁከትም ይሆናሉ፤”2ኛ ቆሮ 12፥20

የእግዚአብሔር ቃል መሪዎችንና ባለስልጣናትን በምን አይነት አግባብ መቅረብና ማናገር ስህተቶችም ቢኖሩ ማሳወቅ እንዳለብን እየነገረን በስጋዊነት ተነስተን ማበሻቀጥና ማዋረድ ምን ያህል ከመንፈሳዊነት እየራቅን እንደሆነ ያመላክታል.......ለስልጣን ስርዓት መገዛት(submission) መንፈሳዊነት ነው፤ መሪዎችን የሚሾም እግዚአብሔር ነውና.....በነገራችን ላይ ጳውሎስ ለመሪዎች ስለመገዛት ሲሰብክ የነበረው ክፉና ጨካኝ በነበረው ንጉስ ቄሣር ዘመን መሆኑ ያስደንቃል.....ለምንድነው ግን በዘመናችን ብዙ ሰው በአድመኝነት መንፈስ ተሞልቶ ለመሪዎች መገዛት የተሣነው???.....ይልቁንም የራሱን ትንንሽ መንግስት ለመመስረት ደፋ ቀና የሚለው???.....እንዴትስ ሁላችንም የአንድ ሃገር ወይም ቤ/ክን ወይም ተቋም መሪ ልንሆን እንችላለን???....ምናልባት እረፍትና ሰላም ያጣነው መገዛትን እንደ መሽነፍ አድርገን ስለምንቆጥረው ይሆን??? በዘመናችን ፀጥ እና ዝግ ብለን እንድንኖር ከተፈለገ ከአድመኝነት መንፈስ በመላቀቅ እግዚአብሔር ለመሪዎቻችን በአግባቡ መስራት የሚችሉበትን ጥበብ እንዲሰጣቸው መፀለይ ይጠበቅብናል....ፀጋ ይብዛልን!!

“እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ።”
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥1-2

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
704 viewsYonatan Worku, edited  12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 08:58:20 ፀሎት..ፀሎት..ፀሎት!!

የሚፀልይ ሰው:-
ዘመኑ አይበላም
ዕድሜው አይባክንም
ራዕዩ አይጨነግፍም
ህልሙ መና ሆኖ አይቀርም
በሮች በፊቱ አይዘጉም
እርምጃው አይሰነካከልም
ወደ ኃላ አይቀርም
አይዘገይም
አይቀደምም
አይሸነፍም
አይከሽፍም
አይዋረድም
የሰበሰበው አይበተንም
በጨለማው ወጥመድ አይያዝም
መሣለቂያ አይሆንም
ግራ አይጋባም
አይወዛገብም
አይከስርም
አይፀፀትም
ወድቆ አይቀርም
አይጨነግፍም
አያፍርም
አይቅበዘበዝም
አይንከራተትም
አይቦዝንም
አይበዘበዝም
አይደነግጥም
ተስፋ አይቆርጥም
በምንም አይቆምም
አይቆዝምም
አያጉረመርምም
አይጨነቅም
ታሪክ አልባ አይሆንም....

“እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።”ያዕቆብ 5፥16

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
839 viewsYonatan Worku, edited  05:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 08:44:33 እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሰውነቴም ድና ቀረች!!

“ያዕቆብም፦ እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሰውነቴም ድና ቀረች ሲል የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል ብሎ ጠራው።”ዘፍጥረት 32፥30

አባታችን ያዕቆብ አብዛኛውን ዘመኑን ያሳለፈው በትግል ነበር......ለዚህም በፈርዖን ፊት በቆመ ግዜ የኖረውን ዘመን ምን እንደሚመስል በአጭሩ ሲያስረዳ የተጠቀመውን አነጋገር መመልከት ብቻ ይበቃል:-

“ያዕቆብም ለፈርዖን አለው፦ የእንግድነቴ ዘመን መቶ ሠላሳ ዓመት ነው፤ የሕይወቴ ዘመኖች ጥቂትም ክፉም ሆኑብኝ፥ አባቶቼ በእንግድነት የተቀመጡበትንም ዘመን አያህሉም።”
ዘፍጥረት 47፥9

ለበረከትና ለብኩርና ብሎ ከወንድሙ ዔሳው ጋር እስከሞት ድረስ የታገለውን ትግልና በአጎቱ ላባ ቤት ለሃያ አመት ስለሚስቶችና ስለበጎች የከፈለውን ዋጋ ስናይ ያዕቆብ በውስጡ ያለውን ጥያቄ ለመመለስና ባዶነት ለመሙላት የማይሄድበት ርቀት እንደሌለ ነው.....ሆኖም ግን የታገላቸው መራራ ትግሎችና ልፋቶች ሙሉ በሙሉ የህይወቱን ጥያቄዎች መልሰውና ህመሙን አሽረው ለአንዴና ለመጨረሻ ሊያረጋጉትና ሊያሳርፉት አልቻሉም.....ይልቁንም ጠብ ሲል ስደፍን እንዲሉ አንዱ ጥያቄ ሲመለስ ሌላ እየወለደ ሌላኛውም እንደዛው እየሆነበት በጥያቄ አዙሪት ውስጥ ፍሬያማ ሊሆንበት የሚችልበትን ዕድሜውን እንደጨረሰ መፅሃፍ ቅዱስ ይነግረናል......ቁሳቁስን በተመለከተ የሁለት ክፍል ሠራዊት እስኪሆን ድረስ እየበዛ የሄደው ያዕቆብ ከእውነተኛ በረከት ጋር ባለመገናኘቱ ግን ውስጡ ሰላምና እርካታ አልነበርውም......በዘፍጥረት ሠላሳ ሁለት ላይ ግን አንዳች ህይወቱን ባልጠበቀው አቅጣጫ የሚለውጥ መለኮታዊ ጉብኝት ጋር ተገጣጠመ......ያዕቆብ የጥያቄ ሁሉ መልስ ከሆነው አምላክ ጋር ፊት ለፊት ተገናኘ፤ በራሱ አንደበትም እንደተገለፀው:-"እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁት ሰውነቴም ድና ቀረች".....ተውዳጆች ሆይ እውነተኛ እረፍትና ደስታ ያለው በምንም ሳይሆን እግዚአብሔርን በማየት ውስጥ ነው......ገንዘብ፣ ስልጣን፣ ዝና፣ መጠጥ እና የመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ እውነተኛና ዘላቂ እረፍት እንደሌለ እነዚህ ነገር ውስጥ ያሉ ሁሉ ጠንቅቀው ያውቃሉ.....የእግዚአብሔር ፊት ውስጥ ብቻ ሁለንተናን ደህና የሚያደርግ መለኮታዊ ብርሃን አለ......ሁላችሁንም ወደዚህ ህይወት ለዋጭ እውነት እንድትመጡና ለዘላለም እንድታርፉ እጋብዛችኃለሁ....ልክ እንዳ ያዕቆብ ጵንኤል ይሁንልን፤ እግዚአብሔርን በማየት ድኖ መቅረት!!

“እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?”
መዝሙር 27፥1

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
730 viewsYonatan Worku, 05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 10:55:21 ጴንጤዎች ግን ዝም ብለው የሚጮሁት ለምንድነው???

በየመንገዱ መጮህ፣ በየሰፈሩ መጮህ፣ በየቸርቹ መጮህ...መጮህ...መጮህ..መጮህ!!.....ቆይ ግን አይሰለችም??......ማለቴ መነጋገር እንኳን ካለብን በቀስታና ረጋ ብሎ መወያየት አይሻልም??? አይነትና የመሳሰሉ ጥያቄዎች በተደጋጋሚ ይነሣሉ.....ልማድ ነው ወይስ ማን አለብኝነት?? ያስብላል....በእርግጥ እኔ ራሴ በተረጋጋ ሁኔታ ጊዜ ወስዶ በመነጋገር በእጅጉ አምናለሁ...ሆኖም ግን መፅሃፍ ቅዱስን ሳጠና መጮህ የሚሰኘው ጉዳይ በመላዕክትም ዘንድ እንዳለ ስመለከት ተገርሜያለሁ......በኢሳይያስ ምዕራፍ ስድስት ላይ ሱራፌል የተባሉ መላዕክት ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እያሉ እግዚአብሔርን ሲያመልኩ ያወጡት የነበረው ድምፅ የመድረኩ መሠረት እንኳን ይናወጥ ጢስም ይወጣ ነበር:-

“የመድረኩም መሠረት ከጭዋኺው ድምፅ የተነሣ ተናወጠ፥ ቤቱንም ጢስ ሞላበት።”ኢሳይያስ 6፥4

ለነገሩ ማንም የእግዚአብሔርን ክብር ሲገለጥ እያየ ዝም ማለት አይችልም.....ሃሌሉያ.....ደሞም እግዚአብሔርን በፍፁም ልባችን፣ ኃይላችን እና ሃሳባችን ልዋንወድደውና ስለ እርሱ ታላቅነት ለአለም ሁሉ በኃይል ልናውጅ ይገባል:-

መዝሙር 19
¹ ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል።
² ቀን ለቀን ነገርን ታወጣለች፥ ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ትናገራለች።
³ ነገር የለም መናገርም የለም፥ ድምፃቸውም አይሰማም።
⁴ ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ፥ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ።

ይሄ ብቻም አይደለም ታላቁ የወንጌል አገልጋይ የነበሩት ራይንሃርድ ቦንኬ ሲናገሩ በመንገድ ስታልፍ አንድ አንበሳ አንድን ህፃን ልጅ ሊበላ ይዞ ብታየው ምን ታደርጋለህ ብለው ይጠይቃሉ??...በተለይም ደግሞ ህፃኑ የአንተ የቤተሰብ አባል ቢሆን??....ያለምንም ጥያቄ ያለ የሌለ ኃይልህን ተጠቅመህ ህፃኑን ለማዳን ትጣጣራለህ ካልሆነም ሰዎች እንዲደርሱልህ በኃይል ትጮኃለህ....በተመሳሳይ መልኩ ሰዎች ኢየሱስን ባለማመናቸው ወደ ሲኦል ሲወርዱ ስታይ የምትሰብክበት መንገድ ከወትሮው የተለየ ይሆናል.....እነሱ ያሉበት ስቃይና ሰቆቃ ስሜትህን በኃይል ስለሚጎዳው እነሱ ይድኑ ዘንድ ጉሮሮህ እስኪነቃ ድረስ ትጮሃለህ፤ የምትጮኽው ግን የመጮህ ሃራራ ስላለብህ ሳይሆን ሰዎችን ከዘላለም ሞት ለማስመለጥ ብለህ ነው......አሊያ ወንጌል አለመቀበል የሚያስከትለው አደጋ ምነኛ ክፉ እንደሆነ አንተ ሰባኪው ራሱ በቅጡ አልተረዳኽውም ይሆናል!!.....ቆይ እስቲ በቤታችን ውስጥ ድንገተኛ እሳት ቢነሣና ማጥፋት ቢቸግረን ለእርዳታ የማንጮህ ስንቶቻችን ነን??.....ተወዳጆች ሆይ ገሀነም እሳት እንደምናስበው ቀልድ ወይም ቀላል አይደለም......ምነው ጮኽንም ቢሆን ሰዎች በዳኑልም......ለማንኛውም ግን ማንም ወደዚህ አስጨናቂና የሰይጣንና የመላዕክቱ መኖሪያ ወደ ሆነ ቦታ በፍፁም መሄድ የለበትም......ስለዚህ እውነት እኔም እጮሃለሁ!!.....ብቻ አንዳንዱን ጮኽን ሌላውን ረጋ ብለን ከገሀነም ፍርድ እንዲያመልጡ ወንጌልን ከመናገር አንታክት.....ጌታችን ኢየሱስ ራሱ በምድር በነበረበት ግዜ ጮሆ እንደነበር የሚያሳይ አንድ ክፍል ጠቅሼ ልሰናበት.....ፀጋ ይብዛላችሁ!!

ዮሐንስ 7
³⁷ ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ፦ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።
³⁸ በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ።

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
873 viewsYonatan Worku, edited  07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 09:10:30 Maranatha concert JJF ማራናታ ኮንሰርት 2015 || አለምገና ሙሉ ወንጌል የሽብሸባ መዘምራን




@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
593 viewsYonatan Worku, edited  06:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ