Get Mystery Box with random crypto!

Zaphnath-paaneah

የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah
የሰርጥ አድራሻ: @zaphnathpaaneah1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 648

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-01-24 10:21:50 የህግ መሰጠትና የብሉይ ኪዳን የመቅደስ ሥርዓት(ታቦትን ጨምሮ) የተሰጠው ለአህዛብ ሳይሆን ለእስራኤላውያን መሆኑን ያውቁ ኖሯል!!

ሮሜ 9
³ በሥጋ ዘመዶቼ ስለ ሆኑ ስለ ወንድሞቼ ከክርስቶስ ተለይቼ እኔ ራሴ የተረገምሁ እንድሆን እጸልይ ነበርና።
⁴ እነርሱ እስራኤላውያን ናቸውና፥ ልጅነትና ክብር ኪዳንም የሕግም መሰጠት የመቅደስም ሥርዓት የተስፋውም ቃላት ለእነርሱ ናቸውና፤
⁵ አባቶችም ለእነርሱ ናቸውና፤ ከእነርሱም ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥ እርሱም ከሁሉ በላይ ሆኖ ለዘላለም የተባረከ አምላክ ነው፤ አሜን።

ለእስራኤላውያን የተሰጡ ነገሮች:-
1. ልጅነት
2. ክብር
3. ኪዳን
4. የሕግ መሰጠት
5. የመቅደስ ሥርዓት
6. የተስፋው ቃላት
7. አባቶችም ለእነርሱ ናቸውና፤
ከእነርሱም ክርስቶስ በሥጋ መጣ!!

ከእስራኤል ውጭ ያሉ ሁሉ አህዛብ ይባላሉ.....አህዛብ ህግ ወይም የመቅደስ ሥርዓት ያልነበራቸው ናቸው.....በዘርህ አህዛብ ይባረካሉ ተብሎ ለአብርሃም የተገባለትን ኪዳን ግን በክርስቶስ በኩል በእምነት ወራሾች ሆነዋል......በዚህም ምክንያት ሐዋርያው ጳውሎስ ህግ ለሌላቸው እንደ እኛ ላሉ አህዛብ ህግ እንደሌለው ሆኖ በመቅረብ ሰዎችን ሁሉ በፀጋ ብቻ(ያለ ህግ) የሚያድነውን የምስራች ይሰብክላቸዋል:-

“ሕግ የሌላቸውን እጠቅም ዘንድ፥ ያለ እግዚአብሔር ሕግ ሳልኖር ነገር ግን በክርስቶስ ሕግ በታች ሳለሁ፥ ሕግ ለሌላቸው ሕግ እንደ ሌለኝ ሆንሁ፤”1ኛ ቆሮንቶስ 9፥21

“አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥”ሮሜ 3፥21

ታድያ በዚህ ዘመን ምነው የሚያድነንን የእግዚአብሔር ፀጋ በእምነት ተቀብለን አህዛብ እንደመሆናችን መዳን ሲገባን ለእስራኤላውያን ብቻ የተሰጠውን ህግንና የመቅደስ ስርዓት ምስጢር(ብሉይ ኪዳን) በጣም ይመለከተናል አልን??

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.6K viewsYonatan Worku, edited  07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 08:04:27 ያለቀና የተቆረጠ ነገራችሁ በኢየሱስ ስም ይቀጥላል!!
አበቃ አከተመ የተባለው ጉዳይ መንቀሳቀስ ይጀምራል!!
ተስፋ ቆርጣችሁ የቀበራችሁትም ከጉድጓድ ይወጣል!!

@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
132 viewsYonatan Worku, edited  05:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-22 19:00:50 አይደለም የዳንኩት የምኖረውም በፀጋ ነው!!

መዳን በሥራ ነው ወይስ በፀጋ ተብሎ ለሚነሣው ጥያቄ የተወሰኑት በፀጋ ሌሎች በሥራ የተቀሩት ደግሞ በሥራና በፀጋ ብለው ይናገራሉ.....መፅሃፍ ቅዱሳችንን በደንብ ስናጠና ግን በግልፅ የሚነግረን መዳንም ሆነ መሥራት የምንችለው በእግዚአብሔር ፀጋ ብቻ መሆኑን ነው.....ከዘላለም ሞትና ከጨለማ ስልጣን ያዳነንና ያፀደቀን ያው ፀጋ በምድር ላይ እንዴት በቅድስናና በንፅህና እንዲሁም እግዚአብሔርን በመፍራት መኖር እንዴት እንደምንችል ያስተምረናል.....ኤፌ ምዕራፍ 2 ላይ ከቁጥር 8-9 ስናነብ የዳንነው በፀጋ መሆኑንና ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ እንጂ የሰው ጥረትና ግረት ውጤት አለመሆኑን ያብራራልናል.... በዚህም ምክንያት ማንም መመካት እንዳይችል ሆኗል.....ስለዚህ በመዳናችን ጉዳይ ላይ የማናችንም ቅንጣት እንኳን አስተዋፅዖ የለበትም.....ኢየሱስን ለመቀበል ያስቻለንን እምነት እንኳን ያገኘነው የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ውስጥ ነው......በመቀጠል ቲቶ ምዕራፍ 2 ላይ ከቁ11-13 ያለውን ክፍል ስናነብ ደግሞ ያዳነን የእግዚአብሔር ፀጋ እኛን ከማዳን በዘለለ መልካም ሥራዎችን በመስራት በብቃት በዘመናችን ኖረን ማለፍ እንችል ዘንድ እንደሚያደርገን ይነግረናል.....በፀጋ ድነን በስጋ እንድኖር የእግዚአብሔር ሀሳብ አይደለም.....አብዛኛውን ግዜ ግን የእኛ አስተዋፅዖ የሌለበትን ገዳይ ለመቀበል ሲያዳግተን ይታያል.....እግዚአብሔር አምላክ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ሰርቶ የጨረሰልን እውነት በቂ ብቻ ሳይሆን ከበቂ በላይ በመሆኑ ያለእኛ አስተዋፅዖ የተሰራልንን በእምነት በመቀበል ማረፍን መለማመድ ይገባናል......ውቂያኖስ ላይ በማንኪያ ውሃ ብንጨምርበት እንደማይጨምር ሁሉ እግዚአብሔር ስለመዳናችን ሰርቶ የፈፀመው ሥራ ላይ ምንም ብንጨምር አንጨምርበትም.....ሐዋርያው ጳውሎስ የእግዚአብሔር ፀጋ በቂ እንደሆነ በመልዕክቶቹ ይፅፋል:-

“በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።”ገላትያ 5፥4

ገላትያ 2
²⁰ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።
²¹ የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.6K viewsYonatan Worku, edited  16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-22 01:42:57 ከአንድ ሰው የመጣ ጥያቄ..

ጥያቄ..."ከፅድቅ አኳያ ያዕቆብ 2:21ን እንዴት ትመለከተዋከህ???..ሰው የሚፀድቀው በእምነት ነው ወይስ በሥራ???

መልስ...በመጀመሪያ ስለ ጥያቄው አመሰግናለሁ!....ጥያቄውን ለመመለስ እንዲረዳን ያዕ 2:21ን ልለጥፈው:-

“አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?”ያዕቆብ 2፥21

ቀጥታ ጥቅሱ ስናነበው እውነትም ሰው በሥራ ይፀድቃል የሚል አንድምታ ያለው ይመስላል....አዎን በሥራ ይፀድቃል ብለን ካልን ደግሞ ጳውሎስ ኤፌ 2:8-9 ከተናገረው ጋርና ከሌሎች ጥቅሶች ጋር ይላተምብናል ይህም መፅሃፍ ቅዱስን እርስ በእርሱ የሚጋጭ እንደሆነ ያስመስለዋል.....ኤፌሶን ላይ ያለውን አንዴ ልለጥፈው:-

ኤፌሶን 2
⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።

ሆኖም ግን ዶክትሪን አንድ ጥቅስ ላይ በፍፁም አይመሰረትምና አውዳዊ ፍቺውን ለመረዳት መሞከር ይገባል.....በተለይ ከቁ14-26 ያለውን ብናነበው ምዕራፉ እያወራ ያለውን ጉዳይ ለማስተዋል አያዳግተንም(ረዘም ስለሚል እኔ እዚህ ሙሉውን አልለጥፈውም እናንተ አንብቡት).....አስቀድመን ማወቅ ያለብን ነገር ቢኖር ምዕራፉ እያብራራ ያለው እምነት አለኝ ስለሚል ነገር ግን ሥራ ላይ ወፍ ስለሆነ ሰው ወይም ደግሞ እምነትና ሥራ ስላላቸው ቁርኝት እንጂ የሚፀደቀው በእምነት ነው ወይስ በሥራ ስለሚሉት ሁለት የክርክር ነጥቦች/የሙግት ሃሳቦች አይደለም......በመሠረቱ እምነትንና ሥራን መለያየት መንፈሳዊውን እውነት በቅጡ ካለማወቅ ይመነጫል.....ይሁንና ግን ሥራን የሚያመጣው እምነታችን እንጂ ሥራችን እምነታችንን በፍፁም አይቀድመውም......ዮሐ ወንጌል ምዕ 15ትን ብንመለከት ሃሳባችንን የተሻለ ያብራራልናል.....እስቲ ቆይ የወይን ግንዱ ላይ የተተከለችው ቅርንጫፍ የፍሬአማነቷ ምስጢር ምንድነው?? ...ቅርንጫፏ ፍሬ ማፍራት የምትችለው ከግንዱ ጋር ካላት አግባብነት ያለው ቁርኝት የተነሣ እንጂ ያለግንዱ ፍሬ ማፍራት በፍፁም አይታሰብም በተመሳሳይ መንገድ ያለ እኔ ምንም ማድረግ አትችሉም ብሎ እንዳለ ጌታ እኛም በእርሱ ላይ በእምነት ሳንተከል የምንሠራው ሥራ ሁሉ ከንቱና የከንቱ ከንቱ ንፋስንም እንደመከተል ይሆንብናል......በአጭሩ ለማስቀመጥ ያህል ሥራችን በልባችን የምናመነውን እምነት እውነተኝነት/አስመሳይነት ይገልጣል ወይም ደግሞ የተተከልንበትን አለም ፍንትው አድርጎ የተቀዳንበትን ምንጭ ጮክ ብሎ ያወራል......ስለዚህ ማንም ሰው ክርስቶስ ላይ በእምነት ከተተከለ መልካምን ፍሬ ማፍራቱ/መልካም ሥራን መስራቱ ሳይታለም የተፈታና የማይታገልበት ተፈጥሮው ይሆናል......ሃሌሉያ......ስለዚህ ልክ ቅርንጫፍ ፍሬን ለማፍራት መጨነቅ ሳይሆን በግንዱ ላይ መተከል እንዳለባት እንዲሁ እያንዳንዱን አማኝ ሊያሳስበው የሚገባው በክርስቶስ ላይ በእምነት ስለመተከሉ ጉዳይ ሲሆን ከላይ እንዳነሣሁት መልካም ሥራ የሚባለው ተያይዞና ቀጥሎ መምጣቱ አይቀርም.....በሥራ ግን ተጀምሮ ለዘላለም ወደ እምነት መድረስ አይቻልም....ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች የተናገረውን እስቲ እንመልከት:-

“የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።”ገላትያ 2፥21

ስለዚህ የክፍሉን ዐውድ መረዳት ከስህተት ይታደገናል....እምነትና ሥራ በተመለከተ በነዚህ ነጥቦች የምዕራፉን ሃይለ ቃል ለማስቀመጥ ልሞክር:-

አንድ እምነት እውነት ወይም ውሸት መሆኑ በሥራው ይገለጣል

እምነት የሥራ ምንጭ ሲሆን ሥራ ደግሞ የእምነት መገለጫው

እምነት ሥራን ሲቀድም ሥራ ደግሞ እምነትን ይከተላል

ሙሉ የመፅሃፍ ቅዱስን ዐውድ ስንመለከት ማንም ቢሆን የሚፀድቀው ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሠርቶ የጨረሰውን ሥራ በእምነት በመቀበል እንጂ ሥራን በመሥራት አይደለም!!

ሌሎቻችሁም ጨምሩበት!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.4K viewsYonatan Worku, edited  22:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-20 12:31:02 በእርግጥ ታቦት በአዲስ ኪዳን አለን??

“በበዛችሁም ጊዜ በምድርም ላይ በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በዚያ ዘመን፦ የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም ልብ አያደርጉትም፥ አያስቡትምም፥ አይሹትምም፥ ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም።”
ኤርምያስ 3፥16

በበዛችሁም ጊዜ በምድርም ላይ በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥

የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው:-
ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም፤
ልብ አያደርጉትም፤
አያስቡትምም፤
አይሹትምም፤ ብቻም ሳይሆን
ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም።”

በሌላ ግዜ ጠለቅ ብለን ለማየት እንሞክራለን!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.8K viewsYonatan Worku, edited  09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-19 09:41:08 ቅርብ
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
171 viewsYonatan Worku, edited  06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-19 09:03:24 ምክንያት አልባ በሆነ ፍቅር ተወድጃለሁ!!

በመሠረቱ እውነተኛ ፍቅር የሚብራራው እግዚአብሔር እኛን በወደደበትና ባፈቀረበት ፍቅር እንጂ እኛ እሱን በወደድንበት አይደለም.......ገና ኃጢያተኞች ሳለን እግዚአብሔር አብ አንድያ ልጁን ስለ ኃጢያታችን አሳልፎ በመስጠት ለእኛ ያለውን አጋፔያዊ ፍቅር በተግባር አሳይቷል.....አጋፔ የምንለው የፍቅር አይነት ከማንም ምንም ምላሽን የማይጠብቅና ለመውደድ ምክንያትን በፍፁም የማይፈልግ ነው......ለዚህ እኮ ነው ያለምክንያት የወደደኝ አምላክ በምክንያት ሊጠላኝ አይችልም ብዬ ገግሜ የማወራው.....በምክንያት የቀረቡ ሁሉ አንድ ቀን በምክንያት መራቃቸው/መሽሻቸው አይቀርም......በነገራችን ላይ የእግዚአብሔርን ፍቅር ለመግለፅ አቅም ያላቸው ቃላቶች እስካሁን ድረስ በምድር ላይ አልተፈጠሩም፤ ከዚህም በኃላ ሊገኙ አይችሉም.......በፍቅር ፍርሀት የለም ተብሎ እንደተፃፈ በእግዚአብሔር ፍፁም ፍቅር እንደተወደደ የገባው ሰው በአኗኗሩ ይለያል.....ልክ የአንድ ህፃን ልጅ ድፍረት የሚመነጨው ከተወደደበት የወላጆቹ ወይም የቤተሰቦቹ ፍቅርና እንክብካቤ እንደሆነ እንዲሁ ይሄ ቀላል የመሰለ ግን ታላቅ የሆነ እውነት የገባው ሰው የሚመላለስበት የፅድቅ ድፍረት ያስደንቃል......ክርስትናን ከአምላክ ፍቅር ውጪ መረዳት ከቶ አይታሰብም......ሌላው ይቅርና ባልንጀሮቻችንን መውደድና የበደሉንን ሁሉ ይቅር ማለት እንኳን የምንችለው ጌታ ለእኛ ያለውን ፍቅር በተረዳንበት መጠንና ልክ ብቻ ነው....ያልተወደደ እንዴት ሊወድ ይችላል? ይቅር ተብሎ የማያውቅ ይቅር ማለት እንዴት ይሆንለታል?.....የፍቅርን ሀ ሁ ያስተማረን የፍቅር ሁሉ አምላክ ለዘላለም ይባረክ.....ነገ ምን እሆናለሁ ብዬ የማልሰጋው ስጋትን የሚያጭሩ ጉዳዮች ጠፍተው ሳይሆን(እንደውም ከመቼውም ግዜ ይልቅ በይዘትም ሆነ በአይነት እንደ አሽን የፈሉበት ሁኔታ ነው ያለው) እውነተኛው ወዳጄ አሳልፎ እንደማይሰጠኝና ሌትና ቀን እንደሚጠብቀኝ ስለገባኝ እንጂ.....እኛ ተኝተን እንኳን እኮ እሱ አይተኛም፤ እንደ አይን ብሌን ይጠብቀናል...ሃሌሉያ....ምናልባት ሰዎች እኔን አይወዱኝም ደግሞም አይቀበሉኝም የምትሉ ብትኖሩ ወደዚህ ታላቅ ፍቅር እጋብዛችኃለሁ.....ኢየሱስ ይወዳችኃል....ለህይወታችሁም ዘላለማዊና እጅግ የከበረ ፍፃሜ አዘጋጅቶላችኃል....አሁን ከገባችሁበትም የተመሰቃቀለ ሁኔታ ውስጥ እንደሚያወጣችሁ እኔ ምስክር ነኝ....የተገለጠው የመለኮት ፀጋ አለምን ሁሉ ማዳን የሚችል ብቃት አለው.....ስለዚህ ለመዳን ብለን በራሳችን ጥረትና ግረት ከምናደርገው ነገር አሁኑኑ ወጥተን የእግዚአብሔርን የፍቅር ስጦታ በእምነት እንቀበል.....መንፈሳዊ ጉዳይን የሚያወሳስቡት ሰይጣን እና ሰዎች እንጂ በመሠረታዊነት እንደዛ ሆኖ አይደለም.....ክርስትና ሰዎች ወደ እግዚአብሔር ከፍታ መድረስ ባለመቻላቸው እግዚአብሔር ወደ ሰዎች ዝቅታ በመውረድ ፍቅሩንና ምህረቱን የገለጠበት የምሥራች ነው ....ይህን በልቡ አምኖ የተቀበለና በአፉ የመሰከረ ሁሉ የዘላለም ህይወት አለው.....በቃ እንደዚህ ቀላል ነው....በዚህ ጉዳይ ላይ በደንብ መነጋገር የምትፈልጉና ከስቃይና ከግራ መጋባት እንዲሁም ከመቅበዝበዝ በመውጣት የነፍስን እረፍት ማግኘት የምትፈልጉ በውስጥ መስመር ፃፉልኝ እንነጋገራለን... እወዳችኃለሁ!!

#share
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.8K viewsYonatan Worku, edited  06:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 08:55:17 እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን?

“ኢየሱስም ለአሥራ ሁለቱ፦ እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን? አለ።”ዮሐንስ 6፥67

ኢየሱስ እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን በማለት ደቀመዛሙርቱን ያፋጠጠበትን ክፍል ሳነብ ብዙ ግዜ የድንጋጤና የግራ መጋባት ስሜት ይሰማኛል.......እንዴት ጌታ ግን እንደዚህ ይላል?! ብዬ እንድጠይቅ ያደርገኛል......በተቻለ መጠን ተከታዮችን(አባላትን) ስለመሰብሰብና ማብዛት እንዲሁም የመጡትን ስለመያዝና ማቆየት መታሰብና መጠናት ሲገባ እንዴት በቀላሉ እንዲበተኑ ዕድል ይመቻቻል??......ታስቦበታል ግን????.....በነገራችን ላይ እዛው ምዕራፍ ላይ ትንሽ ከፍ ብለን ብናነበው በኢየሱስ አገልግሎት ተሰናክለው የተበተኑት ገበያ የሚያክል ቁጥር ያላቸው ሰዎች ነበሩ:-

“ከዚህም የተነሣ ከደቀ መዛሙርቱ ብዙዎች ወደ ኋላ ተመለሱ፤ ወደ ፊትም ከእርሱ ጋር አልሄዱም።”ዮሐንስ 6፥66

ጌታ ግን የተበተኑትን አባላት እንደገና ተመልሰው አገልግሎቱን እንዲታደሙና ፓርትነር እንዲሆኑለት ሲለምንና ሲለማመጥ በፍፁም አናይም ይልቁንም በጣም የቅርብ ወደሆኑትና እርሱ ወደመረጣቸው ደቀመዛሙርት ዘወር በማለት ምናልባት እነሱም ቢሆኑ የመሄድ ፍላጎት ካላቸው ይሉኝታ ይዟቸው እንዳይቀሩ ተመሳሳይና ግልፅ ጥያቄ ያቀርብላቸዋል.....ከዚህ የምንረዳው እግዚአብሔር እንድንከተለው የሚፈልገው ወደንና ፈቅደን እንዲሁም ገብቶን እንጂ በመንጋ ወይም በግድ አይደለም......እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ ወደ እርሱ እገባለሁ እንዲል ቅዱስ ቃሉ ታላቁ አምላክ ምንም እንኳን ማንም የማይቋቋመው ኃይል ቢኖረውም ራሱ የሰጠውን ፈቃድ ግን መልሶ በግድ ከሰዎች አይወስድም፤ እርሱ የፈቃድ አምላክ ነውና!

ጌታችን ኢየሱስ እውነት እውነት እላችኃለሁ ብሎ ጀምሮ በግልፅ ያስተምርና እንደተናገረው ሲያደርግ ሰዎችን ለማዳን ሲሆን ሐሰተኛው ዲያቢሎስ ግን ውሸትን በእውነት መጠቅለያ ጠቅልሎ በማደናገር ብዙዎችን ያጠምዳል፤ ለጥፋትም ይማግዳል......በእኔ መረዳት ብዙ ማስታወቅያና ማንቆለጳጰስ የበዛበት የትኛውም ጉዳይ አንዳች የተሰወረ ችግር አለበት ብዬ አምናለሁ ምክንያቱም እውነት የሆነ ነገር በራሱ ይቆማል እንጂ ሌላ ምንም ድጋፍ አያስፈልገውም......እውነት ለመናገር ግን ኢየሱስ የተናገረበት ድፍረት አሁንም ድረስ ለመገንዘብ ያስቸግረኛል......ከጌታችን እንደተማርነው ለቲፎዞ ብለን በእውነት ጉዳይ ላይ በፍፁም አናመቻምች ይልቁንም እስከመጨረሻ በመፅናት አገልግሎታችንን መፈፀም ይገባናል፤ ሰውን ሳይሆን እግዚአብሔርን ለማክበር ተጠርተናልና.....ፀጋ ይብዛልን.....ሻሎም

“ለእውነት እንጂ በእውነት ላይ ምንም ለማድረግ አንችልምና።”
2ኛ ቆሮ 13፥8

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.6K viewsYonatan Worku, edited  05:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-15 19:52:07 መንግስትህ ትምጣ ብለን በናፍቆት የምንፀልየው እግዚአብሔርን ወደን እንጂ የገሀነም እሣትን ለማምለጥ ብቻ ብለን አይደለም!!

“ይህን የሚመሰክር፦ አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።”ራእይ 22፥20

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
502 viewsYonatan Worku, 16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-15 13:16:05 ይህንን ትንቢታዊ መልዕክት ተቀበሉ:-

እግዚአብሔር ትዕቢተኛውን ማዕበልህን/ሽን ፀጥ ያሰኘዋል!

ዘመን ያስቆጠረውና ያረጀው ወደኃላ የሚጎትተው ስውር ሠንሠለት ይበጠሳል!

አታልፍም/ፊም ብሎ የሚዝተውና የሚገዳደረው ገደብ ዛሬ ከፊታችን ገለል ይላል!

ወደ ተባለልን የክብር ፍፃሜ ፈጥነን መግባት ሆነልን!

በኢየሱስ ስም አሜን...


“እስከዚህ ድረስ ድረሺ፥ አትለፊ በዚህም ለትዕቢተኛው ማዕበልሽ ገደብ ይሁን አልሁ።”ኢዮብ 38፥11

“የተርሴስ ልጅ ሆይ፥ የሚከለክልሽ የለምና እንደ ዓባይ ወንዝ በአገርሽ ላይ ጐርፈሽ እለፊ።”ኢሳይያስ 23፥10

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
Jan15,2023
691 viewsYonatan Worku, edited  10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ