Get Mystery Box with random crypto!

Zaphnath-paaneah

የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah
የሰርጥ አድራሻ: @zaphnathpaaneah1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 648

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-04-22 16:48:11 አባክኖ ለመጣው ልጅ ፍሪዳ ይታረድለታልን??

(የእግዚአብሔርን ፍቅር መረዳት)

በመንፈሳዊ ህይወታችን ሥር ሰድደን ለማደግ ከፈለግን የእግዚአብሔርን ፍቅር በጥልቀት መረዳት ይቀድማል....ይሄ ብቻ አይደለም እንደ ሳይኖሶይዳል ሞገድ ከሚዋዥቅም የህይወት ዘይቤ የሚያድነን ይኽው የእግዚአብሔርን ፍቅር የምንገነዘብበት መንገድ ነው!!

በቅጡ የእግዚአብሔርን ፍቅር ሳያውቁና ሳይረዱ መንፈሳዊ ጉዞ ውስጥ የገቡ ብሎም አገልግሎት የጀመሩ ሰዎች ረጅም ርቀት መዝለቅ አይችሉም....ይልቁንም የሰዎችን ተለዋዋጭ ባህሪ እንዲሁም የአለምን ብልጭልጭታ ሲመለከቱ እንደገና ወደኃላ ማፈግፈጋቸው ሳይታለፍ የተፈታ ኃቅ ነው!!

አብዛኛውን ግዜ የእግዚአብሔርን ፍቅር ከሰዎች ፍቅር ጋር ስለምናነፃፅረው ልዩነቱ በጉልህ አይገባንም....የእግዚአብሔር ፍቅር ግን ከሌሎች ፍቅሮች በየትኛውም መለኪያ ፈፅሞ ሊወዳደር አይችልም፤ እንደውም እየተረዳነው እንሄዳለን እንጂ ተረድተን አንጨርሰውም!!

“ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ።”
ኤፌሶን 3፥18-19

የእግዚአብሔር ፍቅር እንደ አየር ፀባዩ አብሮ የሚለዋወጥ አይደለም...በሌላ አባባል በእኛ መልካም ሥራ ላይ የሚመሠረት ሳይሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር ባህሪ የሚመነጭ ሆኖ ዘላለማዊ ዋስትናን(የልብ እርግጠኝነት) የሚያጎናፅፍ ድንቅ ስጦታ ነው!!

እግዚአብሔር ፍቅሩን ሁሉ ለአለም የገለጠው እንዲሁ እወዳችኃለሁ ብቻ በማለት ሳይሆን ውድና ብቸኛ የሆነውን አንድያ ልጁን ስለ እኛ በመስጠት በተግባር ነበር የገለጠው...ሃሌሉያ!!

“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።”
ዮሐንስ 3፥16

በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት በልባችን ላይ የፈሰሰውን የእግዚአብሔርን ፍቅር ባሰብነውና ባሰላሰልነው መጠን ህይወታችን በፍጥነት መለወጥ ይጀምራል.....የጌታ ፍቅር የገባው ሰው ሌሎች ሰዎችን መውደድና ይቅር ማለት አይከብደውም!!

“በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም።”ሮሜ 5፥5
የጌታ ፍቅሩ አስደናቂ ነው!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
https://t.me/ZaphnathPaaneah1
653 viewsYonatan Worku, edited  13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 03:28:58 ይህን የመሰለ ራዕይ ስመለከት ለሁለተኛ ግዜ ሲሆን ይኽውም ኮሮና ከመግባቱ አስቀድሞ

(ስለምድራችን አሁንም እባካችሁ እንፀልይ )

ትላንትና መንፈስ ቅዱስ አይኖቼን በኃይል ከፍቶ ራዕይን አሳየኝ....ይህንን አይነት ራዕይ ስመለከት ለሁለተኛዬ ነው.......የመጀመሪያው ልክ ኮሮና ወደ ምድራችን ከመምጣቱ ከ3ት ወር በፊት አይቼው የነበረውና በሶሽያል ሚድያዎች ላይ የለቀቅሁት ነው(ከኮሮናው ጋር በተያያዘ)፤ በእርግጥም ምድራችንን ያናወጠ የኮሮና ቫይረስ ተከስቶ ያሳለፍነውን ታስታውሳላችሁ!!

አሁንም በራዕይ ያየሁት አስቤውና ገምቼው የማላውቀው ጎርፍ ምድራችንን እንደገና ሲያጥለቀልቅ ነው(ጎርፉ ምን ሊሆን እንደሚችል አላወቅሁም)......ከዚህ ጎርፍ ለማምለጥ ብዙ ሰዎች ወደተራራዎችና ከፍ ወዳሉ ፎቆች ነፍሳቸውን ለማዳን በከፍተኛ ፍጥነት ሲሮጡም አየሁ ......የማቃቸውም የማላቃቸው ብዙ ሰዎች በትዕይንቱ ውስጥ ነበሩ(የተለያየ ኃይማኖት ውስጥ ያሉ ሰዎችን አይቻለሁ)፤ እኔም ጭምር ነበርኩ!!

በመጨረሻ ግን ተራራው ላይ የደረሱ ሰዎች ጎርፉ ሳይነካቸው ሲያልፍና ደስ ብሏቸው ሲተቃቀፉ አይ ነበር፤ ሆኖም ገና ጥቂት ግዜ መከራዎች እንዳሉ በራዕዩ ውስጥ አስተዋለኩ!!

ባላጋራችን ዲያቢሎስ ሊያስነሳው ያለው አውሎ ንፋስ እንዳለ መንፈስ ቅዱስ ተናገረኝ....ሊገለጥ ያለውን ክብር ስለሚያውቅ ባለ በሌለ አቅሙ ብዙዎችን ለጥፋትና ለሞት ለመማገድ እየታገለ ቢሆንም ከእግዚአብሔር ጋር የተጣበቁ ግን ይህንን ዘመን በክብር ይሻገራሉ!!

ተወዳጆች ሆይ ከመቼውም ግዜ ይልቅ በአግዚአብሔር ቃል መታጠቅና በፀሎት መጋደል ይኖርብናል፤ ውግያችን ከደምና ከስጋ ጋር አይደለምና!!

በኢየሱስ ስም እፀልያለሁ ሃገራችንና ምድራችን በኢየሱስ ደም ትሸፈን....በአንቺ ላይ የተሰራ መሳሪያ አይከናወንም ተብሎ እንደተፃፈ የትኛውም የክፉ እቅድና መሳሪያ ይፈራርስ...አሜን

በዮናታን ወርቁ

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
https://t.me/ZaphnathPaaneah1
607 viewsYonatan Worku, edited  00:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 09:53:40
.                  ሥነ መላዕክት


የትምሕርት ጊዜ
አርብ 13/08/2015
ከ12፡30 - 2፡00 ሰዓት
በብስራተ ወንጌል ገነት ቤተክርስቲያን
(ከዘነቦርቅ የ72 ባጃጅ መዞሪያ)

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
https://t.me/ZaphnathPaaneah1
640 viewsYonatan Worku, 06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 03:39:57 በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ!!
(Fervent in the spirit)

በዚህች አጭር የመንፈሳዊ ህይወቴና የአገልግሎት ዘመኔ ያስተዋልኩት ነገር ቢኖር ለመንፈሳዊ ዕድገት መንፈሳዊ ረሀብ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን ነው!!

የሃይማኖት ስርዓቶችን ሳያጓድል የፈፀመ ሁሉ በእርግጥም እግዚአብሔርን ፈልጎት ላይሆን ይችላል፤ ገሀነምን ለማምለጫ ብቻ ብለው እግዚአብሔርን የሚፈልጉም አይጠፉም!!

እግዚአብሔርን መፈለግና መራብ ከመስበክና ከመዘመር በአጠቃላይ የትኛውንም አገልግሎት ከመከወን ያልፋል!!

መንፈሳዊ ረሀብ ውስጥ ያለ ሰው በምንም ሁኔታ ውስጥ ቢያልፍ እግዚአብሔርን የሙጥኝ በማለት ይታወቃል.....ከእግዚአብሔር ጋር ህብረትም ለማድረግ ግዜና ቦታ አይመርጥም፤ ቀንና ሌሊት ያለመታከት አምላኩን ይፈልጋል!!

በዘመኔ ያስተዋልኩት ነገር ቢኖር ብዙ መንፈሳዊ እውቀት ካላቸው ሰዎች ይልቅ ጥልቅ መንፈሳዊ ረሀብና ጥማት ውስጥ የገቡ ሰዎች ላቅ ያለ ተፅዕኖ ፈጥረው ማለፍ ችለዋል!!

በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እግዚአብሔር የሚፈለግ አምላክ መሆኑንና ያለ እርሱ ምንም ማድረግ እንደማንችል መገንዘብ አስተዋይነት ነው!!

እግዚአብሔርን የሚፈልጉ ከመልካም ነገር ሁሉ አይጎድሉም!!

ጥልቅ የሆነና እረፍት የማይሰጥ እግዚአብሔርን የመፈለግ መንፈስ በኢየሱስ ስም ይለቀቅልን!!

መዝሙር 42
¹ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች።
² ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?
³ ዘወትር፦ አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ።

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
https://t.me/ZaphnathPaaneah1
854 viewsYonatan Worku, 00:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 13:15:51
ይሄ ሁሉ ግን ለእኔ ነው??

ተጨነቀ

ተሰቃየ

አፉንም አልከፈተም

ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት

በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ

አፉን አልከፈተም

በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ

ስለህዝቤ ኃጢያት ተመትቶ ከህያዋን ምድር እንደተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ

ከክፉዎች ጋር መቃብሩን አደረጉ

ከባለጠጎችም ጋቱ በሞቱ

ሆኖም ግን ግፍን አላደረገም

በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም

እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ

ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል

ዕድሜውም ይረዝማል

የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል

ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል

ደስም ይለዋል

ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል

ኃጢአታቸውን ይሸከማል
(ኢሳይያስ 53:7-11)

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
https://t.me/ZaphnathPaaneah1
948 viewsYonatan Worku, edited  10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 15:16:04 ለወደደን....
ከኃጢያታችንም በደሙ ላጠበን...
ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን..

ራእይ 1

⁴-⁵ ዮሐንስ በእስያ ላሉት ለሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት፤ ካለውና ከነበረው ከሚመጣውም፥ በዙፋኑም ፊት ካሉት ከሰባቱ መናፍስት፥ ከታመነውም ምስክር ከሙታንም በኵር የምድርም ነገሥታት ገዥ ከሆነ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን፥
⁶ መንግሥትም ለአምላኩና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ፥ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ክብርና ኃይል ይሁን፤ አሜን።
⁷ እነሆ፥ ከደመና ጋር ይመጣል፤ ዓይንም ሁሉ የወጉትም ያዩታል፥ የምድርም ወገኖች ሁሉ ስለ እርሱ ዋይ ዋይ ይላሉ። አዎን፥ አሜን


መልካም የትንሣኤ በዓል
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
https://t.me/ZaphnathPaaneah1
698 viewsYonatan Worku, edited  12:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 15:51:00 7ት አይነት የፍቅር አይነቶችን አውቃለሁ፤
8ተኛው ግን ከአእምሮዬ በላይ ነው!! 

1.ፊሊያ(brotherly love)
-የወንድማማች/የጓደኛማቾች ፍቅር

2.ፕራግማ(enduring love)
-ብዙ ዘመን አብሮ በማሳለፍ ውስጥ የሚፈጠር ፍቅር(ልክ አብሮ አደግ የሆኑ ሰዎች ከሸመገሉም በኃላ እንደሚፈላለጉ

3.ስቶርጄ(familiar love)
-በቤተሰብ መካከል ያለ ፍቅር(በወላጆችና በልጆች፣ በዘመዳሞች..)..ትንሽ ስጋ እንደ መርፌ ትወጋ እንደሚባለው

4.ኢሮስ(romantic love
-በወንድና በሴት መካከል ያለ የመሳሳብና የመፈላለግ ስሜት(sexual love)

5.ሉዱስ(playful love)
-ይህም የኢሮስ አይነት ቢሆንም በአብዛኛው የሚስተዋለው በታዳጊዎችና ገና ወደ ሪሌሽን ሺፕ እየገቡ ያሉ የገቡም ሊሆን ይችላል....flirting, loughing....መልከፍ፣ ለማሳቅና ለመቀለድ መሞከር...

6.ማንያ(obsessive love)
-አንድን ሰው ወይም ነገር ከመጠን በላይ ማፍቀር(በዚያ ነገር obsessed መሆን፣ ያለዚያ ነገር ባዶነት መሰማት)

7.ፊላውትያ(self love)
-ራስን መውደድ፣ መቀበል፣ ማክበር....ጤናማ የሆነ ፍቅር ነው

8.አጋፔ...(unconditional/selfless love)
-እግዚአብሔር እኛን የወደደበት ፍቅር
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ

https://t.me/ZaphnathPaaneah1
847 viewsYonatan Worku, edited  12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 16:24:38 እውነተኛ ማንነትህ የሚለካው በመከራ ቀን ነው!!

“በመከራ ቀን ብትላላ ጉልበትህ ጥቂት ነው።”ምሳሌ 24፥10

መቼስ ይህች አለም ዥንጉርጉር ናት.....ደስታ ብቻም ሳይሆን ሃዘን፣ ማግኘት ብቻም ሳይሆን ማጣት፣ መወለድ ብቻም ሳይሆን ማርጀት፣ መነሣት ብቻም ሳይሆን መውደቅ፣ መበርታት ብቻም ሳይሆን መድከም ይፈራረቁባታል......ቋሚና ዘላለማዊ መኖሪያችን ወደሆነውና በሰው እጅ ወዳልተሰራው ሀገራችን እስክንሄድ ድረስ ይሄ እውነታ የሚቀር አይደለም!!

“በምድር ላይ የሰው ሕይወት ብርቱ ሰልፍ አይደለምን? ወራቱም እንደ ምንደኛ ወራት አይደለምን?”ኢዮብ 7፥1

ይህ እንዳለ ሆኖ ግን ፃድቅ በእንደዚህ አይነት ጉራማይሌ በሆነ ውጣ ውረዶች ውስጥ ሲያልፍ በምን አይነት የህይወት ዘይቤ ሊመላለስ ይገባዋል የሚለውን መረዳት ይገባል......በተለይም ደግሞ በርዕሱ ላይ እንዳስቀመጥኩት የሰው ልጅ በተለያዩ መንገዶች ውስጥ ቢያልፍ እንኳን እውነተኛ ማንነቱና የውስጥ ጥንካሬው የሚለካው ግን በመከራ ውስጥ ሲያልፍ እንደሆነ መፅሃፍ ቅዱሳችን ያስተምረናል!!

አንድ ሰው ጠንካራ ነው ወይስ ልል ነው ብለን መናገር የምንችለው ሰውዬው በጭንቅና በመከራ ውስጥ እያለፈ ባለበት ግዜ እንጂ በመልካሙ ወቅት አይደለም(በእርግጥ ምቾትንም መቋቋም የማይችሉ ብዙ ሰዎች መኖራቸው አይካድም).....የሆነው ሆኖ ግን በሃገር ሰላም ሁሉም ሰው ፍቅር፣ ደስተኛ፣ ሰላማዊ፣ ታጋሽ፣ ቸር፣ ይቅር ባይ፣ ሩህሩህ፣ ታማኝ,,,,ሲሆን ሰልፍ ውስጥ እያለፈች ያለች ነፍስ ግን ከከበባት ወጀብና አውሎ ንፋስ የተነሣ እውነተኛ ማንነቷ መገለጥ ይጀምራል!!

የእውነት የሞተን ሰው በመርፌ ቢወጉት እንኳን እንደማይሰማ እንዲሁ ለዚህ አለም ነገርና ለሃጢያት የሞተን ሰው በምንም ነገር ቢወጋ ከውስጡ ከመልካም ነገር ውጪ የሚወጣ ምንም ነገር የለም....ሃሌሉያ....ተወዳጆች ሆይ የውሻ አይነት ተናካሽ የእባብ አይነት ደግሞ ተናዳፊ ባህሪ ያላቸውን ነገር ግን የበግ ለምድ ለብሰው የሚዞሩ ሰዎችን የውስጥ ባህሪ(identity) መለየት የምንችለውም አንዳች ምቾት የሚነሣ ከባቢ ውስጥ ሲገቡ ብቻ ነው!!

ሯጮች ውድድር ሲኖራቸው ሊሄዱ ያለበትን ሃገር የአየር ንብረት አስቀድመው ያጠኑና ከዛ የባሰ ሙቀት ወይም ቅዝቃዜ ያለበት ስፍራ ላይ ሄደው ጠንካራ ልምምድ ያደርጋሉ፤ ይህም ከባዱን የአየር ሁኔታ መቋቋም እስከሚችሉ ልምምድ ካደረጉ ውድድራቸውን በቀላሉ እንደሚያሸንፉ ስለሚያውቁ ነው.....መፅሃፍ ቅዱሳችን በግዜውም ብቻ ሳይሆን ያለግዜውም፣ በሚመች ሁኔታ ውስጥ ብቻም ሳይሆን በማይመችም ሁኔታ ውስጥ ብናልፍ እንኳን ፀንተን መቆም እንዳለብን ደጋግሞ ይመክረናል፤ ያሳስበንማል...ዐይኖቻችን ይከፈቱ!!

ፀጋ ይብዛልን!!!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
811 viewsYonatan Worku, edited  13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 15:09:57 በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ!!

“በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው።”1 ዜና 16፥10

መጓደድ ማለት ምን እንደሆነ አስቀድመን እንይ:-

የመጓደድ ትርጉም - መኵራት ፣ መደገግ ፣ መታበይ ፣ መታጀር፣ መመካት፣ መተማመን,,,!!

መፅሃፍ ቅዱሳን በአንድ ነገር ብቻ እንድንጓደድ(እንድንመካ) ያሳስበናል ይመክረንማል እርሱም በእግዚአብሔር ስም ነው.....ከዚያ ውጪ በምንም ነገር መኩራራት(ለመደገፍ መሞከር) ከእግዚአብሔር ጋር እንደ መጣላት ብቻም ሳይሆን ከንቱና ፈፅሞ አያስተማምንም፤ ልክ በሸምበቆ ላይ እንደ መደገፍ ይቆጠራል!!

“የእግዚአብሔር ስም የጸና ግምብ ነው፤ ጻድቅ ወደ እርሱ ሮጦ ከፍ ከፍ ይላል።”ምሳሌ 18፥10

የሰው ልጆች በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚጓደዱባቸው እልፍ ነገሮች አሉ......አንዳንዶች ባካበቱት ሃብትና ንብረት ብርና ወርቅ ይመካሉ ሌሎች ደግሞ በሰበሰቡት ዕውቀትና ጥበብ፣ ሌሎች በስልጣናቸውና በዝናቸው፣ ሌሎችም በሚኖሩበት ሃገርና ባላቸው ዘመድ እና የተቀሩቱም በውበታቸውና በደም ግባታቸው የመሳሰሉት ይመካሉ፤ ይጓደዳሉም.......ብዙዎች ያላስተዋሉት እውነት ግን ከላይ ከዘረዘርናቸው አንዳቸውም የማያስተማምኑና ድንገት ሊከዱን የሚችሉ እንደሆነ ነው.....ከአጠገባችን በቅፅበት ልናጣው በምንችለው ነገር እንዴት እንተማመናለን!?

በሰማይም ሆነ በምድር ከምድርም በታች ጉልበት ሁሉ የሚንበረከክለት ምላስም የሚመሰክርለት አብ ያከበረው አንድ ብቻ አስተማማኝ ስም አለ:-ኢየሱስ!.....ይሄ ስም ልክ እንደ ሌሎች ስሞች በድንገት ተንኮታኩቶ የሚያሳፍር አይደለም ይልቁንም ለተደገፉበትና ለተማመኑበት ሁሉ ሙሉ ዋስትናን የሚሰጥ ደግሞም ኤክስፓየርድ የማያደርግ በባህር ውስጥ ካለ አለት ይልቅ ደግሞ የጠነከረ ፍቱን መድሃኒትና የተዘጋን በር ሁሉ መክፈት የሚችል ማስተር ቁልፍ ነው ....ሃሌሉያ ....እስቲ አንድ ግዜ ኢየሱስ ብላችሁ አውጁ!!

ፃድቅ ወደ እግዚአብሔር ስም እየሮጠ ከፍ ከፍ እንዲል ታድሏል.....የእግዚአብሔር ስም ያለው ሰው ምንም እንደሌለው ሰው ማጉረምረምና ማለቃቀስ አይገባውም.....በምድር ላይ ስንኖር የመንፈስ ቅዱስን ኃይል በሙላት እንድናንቀሳቅስበት የተሰጠን ላይሰንስ(license) ኢየሱስ ይባላል.....በዚህ ስም የማይቀልጥ በሽታ የለም፣ የማይፈርስ ዘመን ያስቆጠረ የዘር መርገም የለም፣ የማይደረመስ ኢያሪኮ የለም፣ የማይከፈል ቀይ ባህር የለም፣ የማይመለስ ጥያቄ የማይፈታ እንቆቅልሽ የለም፣ የማይስተካከል ምስቅልቅሎሽ የለም፣ የማይተረተር ሽባ የማይቀና ጉብጥና የለም፣ የማይበራ እውርነት የማይሰማ ድንቁርናም የለም,,,,!!

“ጴጥሮስ ግን፦ ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።”ሐዋርያት 3፥6

ተወዳጆች ሆይ አሁን ቅዱስ ስሙን በነገሮቻችሁ ሁሉ ላይ ማወጅ ጀምሩ ባልገመታችሁት ቅፅበት ሥራችሁ ተሰርቶና ጉዳያችሁ አልቆ ከምስክርነት ጋር ትመለሳላችሁ.....ቆይ ግን ስሙን በእምነት ጠርቶ ያፈረ ማን አለ?? ስምህ እንደሚፈስ ዘይት ነው ተብሎ እንደተፃፈ የስሙ ዘይት በኃይል እንዲፈስስባችሁ ዛሬ እፀልያለሁ....አሜን!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
964 viewsYonatan Worku, 12:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 16:28:57 እግዚአብሔርን በቆይታ መፈለግ!!

አስቀድመን መረዳት ያለብን እውነት ቢኖር እግዚአብሔር መታወቅ የሚወድና እንዲታወቅም ራሱን በልዩ ልዩ መንገዶች የገለጠ መሆኑን እንጂ አንዳንዶች እንደሚመስላቸው ከፍጥረታት ሁሉ ተደብቆና ተሸሽጎ መኖር የሚፈልግ አምላክ አይደለም!!

“በስውር ወይም በጨለማ ምድር ስፍራ አልተናገርሁም፤ ለያዕቆብ ዘር፦ በከንቱ ፈልጉኝ አላልሁም እኔ እግዚአብሔር ጽድቅን እናገራለሁ ቅንንም አወራለሁ።”ኢሳይያስ 45፥19

እግዚአብሔርን መፈለግ ማለት ህይወትን፣ ሰላምን፣ እረፍትን፣ ደስታን፣ እርካታን፣ በረከትን,,,ወዘተ እንደመፈለግ ይቆጠራል፤ እርሱ የመልካም ነገር ሁሉ ምንጭ ነውና...ሃሌሉያ!

“ባለጠጎች ደኸዩ፥ ተራቡም፥ እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ግን ከመልካም ነገር ሁሉ አይጐድሉም።”መዝሙር 34፥10

የሰው ልጆች ሁላችን አንድ ልናውቀው የሚገባን ነገር ቢኖር እግዚአብሔር አምላክ ከምንገምተውና ከምናስበው በላይ እንደሚያስፈልገንና ያለእርሱ ህይወታችን ከንቱና ባዶ እንዲሁም ትርጉም አልባ መሆኑን ነው!!

“ከእናንተ ከባለ ቅኔዎች አንዳንዶች ደግሞ፦ እኛ ደግሞ ዘመዶቹ ነንና ብለው እንደ ተናገሩ፥ በእርሱ ሕያዋን ነንና እንንቀሳቀሳለን እንኖርማለን።”ሐዋርያት 17፥28

እግዚአብሔርን መፈለግ የሚገባን በፍፁም ልባችን፣ነፍሳችን፣ ሃሳባችን ኃይላችን ሲሆን በፈለግነው መጠንም እናገኘዋለን......በጣም የሚገርመው ምንም እንኳን አምላካችን ይታወቅ ዘንድ ለሁሉም ሰው ራሱን እኩል የገለጠ ቢሆንም ሁላችንም ግን እኩል አናውቀውም፤ የተጠጋነውንና የቀረብነውን ያህል ብቻ እንጂ!!

አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሔርን የመፈለግ አፒታይታቸው ብዙም ባለመሆኑ ከትንሽ ፍለጋ በኃላ ይደክማቸዋል ከዚያም ያቆማሉ......ሌሎች ደግሞ አሉ አሣ ከውኃ ውስጥ ወጥቶ መኖር እንደማይችል በቃላት ሊገለጥ በማይችል ረሃብ እግዚአብሔርን ቀንና ሌሊት የሚናፍቁ ፤ እንደዚህ አይነት ሰዎች አንድ የበራላቸው እውነት ስላለ እግዚአብሔርን በሙሉ ትኩረትና በፍፁም መሻት እንዲሁም በረጅም ቆይታ ሲፈልጉት ይታያል....ጌታ ሆይ እባክህ እኔንም እንደነዚህ ልባሞች አድርገኝ!!

መዝሙር 42
¹ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች።
² ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?

ተወዳጆች ሆይ እግዚአብሔርን መፈለግ ብለን ስናወራ ለእርሱ ያለን ትኩረት፣ ረሃብ፣ ናፍቆት፣ ጥማት ብቻ ሳይሆን ግዜን(ቆይታ) ይመለከታል.....ወደድንም ጠላንም ለአንድ ነገር ያለን እውነተኛ ፍቅር የሚለካው ለነገሩ በምንሰጠው ግዜ እንጂ የንግርት ቃል ብቻ አይደለም......በጣም ቢዚ ነኝ እንኳን ብለን ብናስብ ከልብ ለምንወደው መቼም ግዜ አናጣም(ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም)

እግዚአብሔርን በቆይታ ውስጥ በፅናት መፈለግ ወደ እኛና ወደነገራችን ዘንበል እንዲል ያደርገዋል....እርሱን የመፈለጋችን እውነተኝነት የሚረጋገጠው በግዜ ውስጥ እንደወርቅ ተፈትኖ ሲያልፍ ነው.....እግዚአብሔርን መፈለግ አለብኝ ብለው መንገድ የሚጀምሩት ብዙ ቢሆኑም ፍለጋቸው ፍሬ አፍርቶ ናፍቆታቸው ጋር የሚገናኙ ግን በጣም ጥቂቶችና እስከመጨረሻ የፀኑ ብቻ ናቸው!!

  ዳዊት በመዝሙሩ የሚያስታውሰን ይንኑ ነው፤ ዛሬ ለሁላችንም እፀልያለሁ:-"እግዚአብሔርን ወደህይወታችን ዘንበል የሚያስደርግ በፊቱ የምንቆይበት መለኮታዊ ፀጋ በኃይል ይለቀቅልን..በኢየሱስ ስም!!"

መዝሙር 42
¹ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች።
² ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.0K viewsYonatan Worku, 13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ