Get Mystery Box with random crypto!

Zaphnath-paaneah

የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah
የሰርጥ አድራሻ: @zaphnathpaaneah1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 648

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-03-27 17:33:05 ትንቢታዊ ቃል
አዋጅ አዋጅ

ወደ ማዶ ትሻገራላችሁ..

“በዚያም ቀን በመሸ ጊዜ፦ ወደ ማዶ እንሻገር አላቸው።”ማርቆስ 4፥35

ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን ስለ እግዚአብሔር መንግስት ጉዳይ ብዙ ሚስጥሮችን ሲገልጥላቸውና ሲያስተምራቸው ከቆየ በኃላ ወደ ማዶ እንሻገር አላቸው.....ወደ ማዶ እንሻገር ያለበት ዋነኛ ምክንያት ከባህሩ ማዶ በሰንሰለት ታስሮ በመቃብር አካባቢ ይኖር የነበረ የዕብደት መንፈስ የተጠናወተው ሰው መፈታት ስለነበረበት ሲሆን ሲቀጥል ደግሞ ደቀመዛሙርቱ እስከዛሬ በህይወታቸው ካዩትና ከተለማመዱት ያለፈ አዲስ ክብርን ሊገልጥላቸውና ሊያሳያቸው ስለወደደ ነበር.....ሃሌሉያ ....መንፈስ ቅዱስ ይህንን ትንቢታዊ ቃል ሰጥቶኛል:-ብዙዎች ወደ ማዶ ይሻገራሉ፣ ከዚህ በፊት ወዳላዩትና ወዳልተለማመዱት ክብር ውስጥ የሚገቡ ሰዎች አሉ፣ አዲስ የሪቫይቫል ንፋስ። እንደገና በምድሪቱ ላይ በኃይል ሲመጣ አያለሁ.....በዚያች ቤተሳይዳ በምትባለዋ መጠመቂያ መልአኩ ውሃውን በኃይል ሲያናውጠው ቀድሞ የገባ ሁሉ የትኛውም ጥያቄ እንደሚመለስለት እንዲሁ እየመጣ ያለውን ክብር መቀበልና ማስተናገድ የፈቀዱ ሁሉ ወደ ማዶ ይሻገራሉ....ይህንን ትንቢታዊ መልዕክት በእምነት ለሚቀበል ሁሉ የሚሆን ድንቅ ነገር አለ.....በህይወታችን በሁሉም አቅጣጫዎች ላይ ትልቅ ሽግግር በእርግጥ ይሆናል.....ወደኃላ የሚጎትተን ገመድና የሚያስነክሰን ጉዳይ ዛሬ በኢየሱስ ስም ተበጣጠሰ....እስቲ በህይወቴ ሽግግር ይሆናል ብላችሁ ፃፉ


ከክብር ወደ ክብር እንሻገራለን፣
ኢየሱስን ይዘን ማነው የሚቋቋመን፣
ገና እናብባለን፤

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
936 viewsYonatan Worku, 14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 15:25:38 የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ!!

“በነቢዩ በኢሳይያስ ቃል መጽሐፍ፦ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ፤ ዐዘቅቱ ሁሉ ይሙላ ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይበል፥ ጠማማውም የቀና መንገድ ይሁን፥ ሸካራውም መንገድ ትክክል ይሁን፤ ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ ተብሎ እንደ ተጻፈ ለኃጢአት ስርየት የንስሐን ጥምቀት እየሰበከ በዮርዳኖስ ዙሪያ ወዳለችው አገር ሁሉ መጣ።”ሉቃስ 3፥3-6

የእግዚአብሔር ክብር ወደ ህይወታችን በኃይል እንዲመጣ መንገዶች እንዲህ መስተካከል አለባቸው:-

ዐዘቅቱ ይሙላ(ሽለቆው ከፍ ይበል)
እኔ መቼም አልበቃም ብሎ ማሰብ
እግዚአብሔር በእኔ ሊጠቀም አይችልም ማለት
በሰው ፊት ቆሜ መናገር አይሆንልኝም ብሎ ማሰብ
ካለሁበት የኃጢያት ሱስ አልላቀቅም ብሎ መደምደም
እግዚአብሔር አይወደኝም፣ አይፈልገኝም ብሎ ማመን
መፍራት
ሰው የምሆን አይመስለኝም ብሎ ማለት እና የመሳሰሉት አይነት ሽለቆዎች ይሞላሉ!!

ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይበል
ትዕቢት፣ ራስ ወዳድነት፣እኔነት፣ ለራስ የሚሰጥ የተጋነነ ግምት፣ አጉል ድፍረት፣ ደንዳናነት፣ እንደኔ ለእግዚአብሔር የቀረበ የለም ብሎ ማለት፣ የእኔ አገልግሎት ላይ የሚደርስ የለም ብሎ ማሰብ፣ እግዚአብሔርን አለመፍራት፣ ሰዎችን(በተለይም እናትና አባትን) አለማክበርና አለመታዘዝ...ወዘተ በኢየሱስ ስም ይስተካከል!!

ጠማማውም የቀና መንገድ ይሁን
ተንኮለኝነት፣ ውሸት፣ አስመሳይነት፣ አድመኝነት፣ ከሃዲነት፣ እግዚአብሔርን አለመስማት፣ ሰዎችን አለመቀበል፣ ነገሮችን በተቃራኒው መረዳት፣ በቅንነት አለመመላለስ....እና ከዚሁ ጋር የተያየዙ ሁሉ ይለወጡ!!

ሽካራውም መንገድ ይስተካከል(ስርጓጉጡም ሜዳ ይሁን)
ይቅር አለማለት፣ ቂመኝነት፣ ቅንዐት፣
፣ የሃጢያት ልምምድ፣ አለመታመን፣ አለመዋደድ እና ሌሎችም ከሰው ልብ ላይ ይጠረጉ!!

“የእግዚአብሔርም ክብር ይገለጣል፥ ሥጋ ለባሹም ሁሉ በአንድነት ያየዋል፥ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።”ኢሳይያስ 40፥5

አሜን ጌታ ሆይ ክብርህ በህይወታችን ላይ በኃይል ይገለጥ ሌላ ረሃብ የለንምና ......ለክብርህ የማይመች የትኛውም ነገር እኛ ላይ እንዳይኖር በኢየሱስ ስም እፀልያለሁ!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.0K viewsYonatan Worku, 12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 19:17:55 የቅንነት ወይስ የቅንዐት መንፈስ!!

የእግዚአብሔርን እጅ በህይወታችን ላይ በኃይል ከሚያንቀሳቅሱና በጨለማው አለም ሥርዐት ወጥመድ ውስጥ በቀላሉ ወድቀን እንዳንሰባበር ከሚያደርጉን መንፈሳዊ እሴቶች መካከል ዋነኛው ቅንነት ይባላል........ቅንነት የምንለው ለሰዎች፣ ለነገሮች እንዲሁም ለሁኔታዎች ያለን የተቃናና ያልተዛባ እንዲሁም በተፈወሰ ህሊና ላይ የተመሰረተ ድንቅ መረዳት ሲሆን ይህም የተጣመመና የተዛነፈ ድምዳሜ ፈጥነን  እንዳናደርግ ይጠብቀናል......ቅንዐት ግን ለሌሎች ሰዎች አንዳች ነገር ቢደረግ እንኳን በዚያ ጉዳይ አብሮ ከመደሰት ይልቅ ቆይ ለኔስ ግን ብሎ በመቆጣት ሁሉንም ነገር ከራስ ጥቅም አንፃር ብቻ ማየት ሲሆን ምንጩም አጋንንት ነው(መልካም የሆነ መንፈሳዊ ቅንዐት መኖሩን ግን አምናለሁ).....መፅሃፍ ቅዱሳችን ከቅንዐት መንፈስ ተላቅቀን በቅንነት መንፈስ እንድንመላለስ ደጋግሞ ይመክረናል......ቅንዐት ከሥጋ ሥራዎች መካከል ዋነኛው ሲሆን ልቡ በዚህ መንፈስ የተሞላ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልቷል፤ በተቃራኒው ደግሞ በቅንነት የተሞላ ልብ ለእግዚአብሔር እንደ ጣፋጭ መስዋዕት በመሆኑ በቀላሉ የጌታ መገኘት በህይወታችን ላይ በኃይል እንዲበዛ ያደርጋል....ሃሌሉያ....በአለማችን ላይ ከመቼውም ግዜ ይልቅ ቀናነት እየጠፋ ቅንዐት ግን እንደ አሸን እየፈላ ያለበት ግዜ ላይ እንገኛለን ብል ማጋነን አይሆንም፤ በዘመናት መካከል ግን እግዚአብሔር የተጠቀመባቸውን ሰዎች ህይወት ብናጠና ዋናው መገለጫቸው የቅንነት ህይወታቸው ነው...ለምሳሌ ያህል ዳንኤልን፣ ኢዮብን,,,መመልከት ይቻላል:-

“በፊቱ ቅንነት ተገኝቶብኛልና፥ በአንተም ፊት ደግሞ፥ ንጉሥ ሆይ፥ አልበደልሁምና አምላኬ መልአኩን ልኮ የአንበሶችን አፍ ዘጋ፥ እነርሱም አልጐዱኝም አለው።”ዳንኤል 6፥22

እግዚአብሔር ስለ ኢዮብ ቅንነት የተናገረውን እናንብብ:-

“እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ በውኑ ባሪያዬን ኢዮብን ተመለከትኸውን? በምድር ላይ እንደ እርሱ ፍጹምና ቅን፥ እግዚአብሔርንም የሚፈራ፥ ከክፋትም የራቀ ሰው የለም፤ በከንቱም አጠፋው ዘንድ አንተ በእርሱ ላይ ምንም ብታንቀሳቅሰኝ፥ እስከ አሁን ፍጹምነቱን ይዞአል።” ኢዮብ 2፥3

ኢየሱስ ራሱ በናትናኤል ልብ ውስጥ ተንኮል እንደሌለ መስክሯል:-

“ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ፦ ተንኰል የሌለበት በእውነት የእስራኤል ሰው እነሆ አለ።”ዮሐንስ 1፥48

ቅንዐት የዚህ አለም(የአጋንንት) ጥበብ መገለጫ ነው.....በቅንዐት መንፈስ ህይወቱ የተሞላ ሰው ወደደም ጠላም የጠላት መጠቀሚያ ሆኗል:-

ያዕቆብ 3
¹⁴ ነገር ግን መራራ ቅንዓትና አድመኛነት በልባችሁ ቢኖርባችሁ፥ አትመኩ በእውነትም ላይ አትዋሹ።
¹⁵ ይህ ጥበብ ከላይ የሚወርድ አይደለም፤ ነገር ግን የምድር ነው፥ የሥጋም ነው፥ የአጋንንትም ነው፤
¹⁶ ቅንዓትና አድመኛነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ስራ ሁሉ አሉና።.

በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ መነጋገር ይቻላል ሆኖም ግን ለዛሬ እዚህ ጋር ላብቃ.....እንዲህ ግን ልባርካችሁ:- በልባችን ውስጥ የተሰገሰገ የቅንዐት መንፈስ ምናልባት ቢኖር አሁን ከልባችን ውስጥ ተጠራርጎ በኢየሱስ ስም ይውጣ፤ ጌታ ልባችንን በቅንነት መንፈስ ይሙላው.....ተባርካችኃል!!

“ዘሩ በምድር ላይ ኃያል ይሆናል፤ የቅኖች ትውልድ ትባረካለች።”መዝሙር 112፥2
“የኀጥኣን ቤት ይፈርሳል፤ የቅኖች ማደሪያ ግን ያብባል።”ምሳሌ 14፥11
“የኀጥኣን መሥዋዕት በእግዚአብሔር ዘንድ አስጸያፊ ነው፤ የቅኖች ጸሎት ግን በእርሱ ዘንድ የተወደደ ነው።”ምሳሌ 15፥8

@ZaphnathPaaneah1
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
999 viewsYonatan Worku, 16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 11:45:30 ቅባት በባህሪው አቧራ ይስባል!!

አብዛኛዎቻችን እንደምናውቀው ቅባትና ዘይት ነክ የሆኑ ነገሮች አቧራን በቀላሉ የመያዝ(absorb) ባህሪ አላቸው....የመኪና ዘይትን እንደምሳሌ ብንወስድ 5ሺህ ኪ.ሜትር ከሄደ በኃላ መቀየር ግድ የሚለው በዋነኝነት ከዚህ ጋር በተያያዘ ምክንያት ነው.....ምናልባት የተጠቀምኩት ምሳሌ አሊጎሪክ ቢመስልም ነገር ግን በእኔ መረዳት አንድምታው ለመንፈሳዊ ጉዳይም በደንብ ይሠራል.....ጌታ ኢየሱስን በማመናችን ምክንያት የተቀበልነው መለኮታዊ ቅባት በውስጣችን እንዳለ ይታወቃል.....በተመሳሳይ ሁኔታ ማወቅ ያለብን መራራ የሚመስል እውነት ቢኖር ከተቀበልነው ቅባት ጋር መከራ እና ስደት በፓኬጅ ውስጥ መኖራቸውን ነው....ይህ ብቻ ሳይሆን መቀባታችንን የሰማና ያየ እንዲሁም የደነገጠ ባላጋራችን ዲያቢሎስ ደግሞ ከወትሮው በተለየ ከፍተኛ ጦርነት አስከትቶ ማዝመቱ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ መሆኑን ጠንቅቀን መረዳት ይገባናል......ይህንን ከዳዊት ህይወት እንኳን ማየት ይቻላል:-

“ፍልስጥኤማውያንም ዳዊት በእስራኤል ላይ ንጉሥ ሆኖ እንደ ተቀባ ሰሙ፥ ፍልስጥኤማውያንም ሁሉ ዳዊትን ሊፈልጉ ወጡ፤ ዳዊትም በሰማ ጊዜ ወደ ምሽጉ ወረደ።”2ኛ ሳሙኤል 5፥17

አስተውላችሁ ተመልከቱ:-ፍልስጤማውያን ዳዊት በእስራኤል ላይ ንጉስ ተደርጎ መቀባቱን ሲሰሙ ሊይዙትና ሊገድሉት እርሱን መፈለግ እንደጀመሩ በግልጥ እናያለን.....ሌላው በብዙ በፈተና ውስጥ ያለፈው ዮሴፍ ነው:-

ዘፍጥረት 39
⁶ ያለውንም ሁሉ ለዮሴፍ አስረከበ፤ ከሚበላውም እንጀራ በቀር ምንም የሚያውቀው አልነበረም። የዮሴፍም ፊቱ መልከ መልካምና ውብ ነበረ።
⁷ ከዚህም በኋላ እንዲህ ሆነ፤ የጌታው ሚስት በዮሴፍ ላይ ዓይንዋን ጣለች፦ ከእኔም ጋር ተኛ አለችው።

ሌሎችንም ብዙ ምሳሌዎች ከመፅሃፍ ቅዱስ መጥቀስ ይቻላል.....ባጠቃላይ ልንረዳው የሚገባን እውነት ግን መቀባታችን ከችግርና ከፈተና ነፃ እንደማያደርገንና የቀባን ጌታ ደግሞ እኛን ፈፅሞ ሊያድነን የታመነ መሆኑን ነው....ሃሌሉያ....ማን ነበር እንዲህ የዘመረው:-"የተቀባ ሰው ሰልፉ ብዙ ነው፤ ነገር ግን ጌታ ከእርሱ ጋራ ነው"!!

ይህንን ጉዳይ ያነሣሁት በተለይም በኔ ዘመን የእግዚአብሔርን ክብርና ቅባት ቀንና ሌሊት እንደ ኦክስጅን የምትናፍቁ የትዬለሌ ወጣቶችና ቲኔጀሮች እንዳላችሁ ስለማውቅና(እኔም አንዱ ነኝ!!) ቅባቱ ሲገለጥ አብረውና ተያይዘው የሚመጡ ፈተናዎች መኖራቸውን ለማስታወስ ስለምወድ ነው......ምናልባት አንዳንድ ልጆች ይህንን ቢያውቁ ኖሮ ክብር ክብር ብለው ላይሉ ይችሉ ነበር ብዬ እገምታለሁ...
.ያው እውነት እውነቱን ተነጋግረን በብርሃን እንደር ብዬ ነው......የሆነው ሆኖ ግን ያለ እግዚአብሔር ክብር ለሺህ አመታት በምድር ላይ ከምንንከላወስ በእግዚአብሔር ክብር ውስጥ(ከነ ተግዳሮቶቹ) አንድ ቀን ብቻ ኖረን ማለፍ ይሻለናል.....ጌታ ሆይ ክብርህ አሁንም በኃይል ያግኘኝ....ሻሎም!!!

“ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፤ መታመኛዬም እግዚአብሔር ነው በጽዮን ልጅ በሮች ምስጋናህን ሁሉ እናገር ዘንድ።”መዝሙር 73፥28

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.1K viewsYonatan Worku, 08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 17:20:25 ሙሴ እጁን ባነሣ ጊዜ እስራኤል ድል ያደርግ ነበር፤ እጁንም ባወረደ ጊዜ አማሌቅ ድል ያደርግ ነበር!!

ዘጸአት 17
¹¹ እንዲህም ሆነ፤ ሙሴ እጁን ባነሣ ጊዜ እስራኤል ድል ያደርግ ነበር፤ እጁንም ባወረደ ጊዜ አማሌቅ ድል ያደርግ ነበር።
¹² የሙሴ እጆች ግን ከብደው ነበር፤ ድንጋይም ወሰዱ፥ በበታቹም አኖሩ፥ እርሱም ተቀመጠበት፤ አሮንና ሖርም አንዱ በዚህ አንዱ በዚያ ሆነው እጆቹን ይደግፉ ነበር፤ ፀሐይም እስክትገባ ድረስ እጆቹ ጠነከሩ።

እስራኤልና አሜሌቅ ጦርነት ላይ በነበሩ ግዜ የተከሰተ ክስተት ነበር....የእስራኤል መሪ የነበረው ኢያሱ ጎልማሶችን መርጦ ከአማሌቃውያን ጋር ለመዋጋት ወደጦርነቱ ሜዳ ሲሄድ ሙሴ ደግሞ ለእስራኤል ለመፀለይ ከአሮንና ከሖር ጋር የእግዚአብሔርን በትር በመያዝ ወደ ኮረብታው ራስ ሲሄድ እንመለከታለን......ጦርነት ብቻ ሳይሆን በዚህ ምድር ላይ የምንኖረው ህይወት በአጠቃላይ መንፈሳዊ ነው(life is spiritual) ብለን የምንለው ለዚሁ ነው......እስራኤላውያን የገቡበት ውግያ ስጋዊ ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊም በመሆኑ በፊዚካል አለም ላይ ከሚደረግ ውግያ ባለፈ በመንፈሳዊ አለም ላይም መዋጋት አማራጭ አልነበራቸውም፤ እንደውም መንፈሳዊው አለም ላይ ያላቸው አቅም የስጋዊውን ጦርነት ውጤት በግልፅ ይወስነው ነበር.....ለዚህ አይመስላችሁም ከላይ በለጠፍኩላችሀ ጥቅስ ላይ እንደምንመለለተው ሙሴ እጁን ወደ ላይ(ወደ እግዚአብሔር) ሲያነሣ እስራኤል በግልፅ ሲያሸንፍ ደክሞት እጁን ሲያወርድ ግን አማሌቅ ድል ማድረግ የሚጀምረው!!.....ተወዳጆች ሆይ መንፈሳዊው አለም ላይ ተሽንፈን በገሀዱ አለም ላይ ነጭ ላብ እስኪያልበን ብንለፋና ብንፍጨረጨር የምንፈጥረው ምንም ነገር አይኖርም.......ሁልግዜ መንፈሳዊው አለም ላይ ከፍተኛውን ስፍራ(the upper hand) መያዛችንን እርግጠኛ መሆን ይገባናል......ወደ ላይ ያለን ነገር(vertically) የሰመረና የተቃና ከሆነ ወደ ጎንም(horizontally) የተሳለጠ መሆኑ ይታወቃል......እጅን ወደ እግዚአብሔር ማንሣት ምን ያህል አስፈላጊ መሆኑን ከሙሴ በቀላሉ ማየት ይቻላል......ደክሞትና እጁ ዝሎ እንኳን እጆቹን ሲያወርድ ወዲያው አማሌቅ ማሸነፍ ይጀምራል እንጂ መንፈሳዊው አለም አይ ስለደከመው ነው ብሎ ምህረት አያደርግለትም.....አሮንና ሖርም ይሄ በደንብ ስለገባቸው ሙሴ እንዲቀመጥ ድንጋይ አዘጋጅተውለት እጆቹንም በቀኝና በግራ ይደግፉት እንደነበር መፅሃፍ ቅዱስ ይነግረናል....ሳጠቃልል መንፈሳዊው አለማችንን ከምንም በፊት ጤንነቱ የተጠበቀ መሆኑን እርግጠኛ መሆን አለብን.....ቆመን እጃችንን ማንሣት ቢያቅተን እንኳን ተንበርክከን አሊያ ተቀምጠን ብቻ ግን እጃችንን ማንሣት መቀጠል የድላችንን ከፍታና ፍጥነት ይወስነዋል፤ ይሄ ብቻ አይደለም ለብቻችን መፀለይ ቢያቅተን እንኳን ከወንድሞችና ከእህቶች ጋር በመሆን መንፈሳዊ ውግያን እስከመጨረሻው በመቀጠል አሽናፊነታችንን ማስቀጠል ግድ ይላል.....እጆቻችንን ወደ ላይ ስናነሣ የተበተኑብን ሁሉ ይሰበሰባሉ፣ ምርኮአችንም ይመለሳል፣ ደስታችን ይበዛል፣ ሞገሳችን ይጨምራል፣ አሸናፊነታችን ይቀጥላል....ፀጋ ከሁላችን ጋር ይሁን!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.2K viewsYonatan Worku, edited  14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 17:10:25 ዕዝራ የእግዚአብሔርን ሕግ:-
        ፨ለማጥናት
        ፨ለማድረግ
        ፨ለማስተማር..ፈፅሞ ራሱን ሰጥቶ ነበር።።።

“ዕዝራ የእግዚአብሔርን ሕግ በማጥናትና በማድረግ፣ ለእስራኤልም ሥርዐቱንና ሕጉን በማስተማር ራሱን ፈጽሞ ሰጥቶ ነበር።”ዕዝራ 7፥10 (አዲሱ መ.ት)

ልክ እንደ ዕዝራ ለተሻለው እና ለዘላለም ፀንቶ ለሚኖረው የእግዚአብሔር ቃል ራሳችንን እንስጥ...ቃሉን ላከ ፈወሳቸው ተብሎ እንደተፃፈ ህይወታችንን ለቃሉ ስንሰጥ መለኮታዊ ፈውስ ያገኘናል....ስለዚህ ከምንም ነገር በፊት ለዘላለማዊው የእግዚአብሔር ቃል ዋጋ እንስጥ....ያኔ ተራ መሆን አንችልም....ይልቁንም የፈራረሱብን ነገሮች ሁሉ እንደገና ይጠገናሉ፣ እንደ ደረቁ አጥንቶች እዚህም እዚያም የተበታተኑብንም ጉዳዮች ተቀራርበው ይገጣጠማሉ እንዲሁም ትርጉም ያለው ህይወት መኖር እንጀምራለን...ተባርካችኃል!!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.2K viewsYonatan Worku, 14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 18:36:47 ከሁሉም በላይ የእግዚአብሔር ክብር

ከምናስበው በላይ፣ ከምንፈልገው በላይ፣ ከሚመስለን በላይ፣ ከምንፀልየው በላይ፣ ከምንጠማው በላይ፣ ከምንናፍቀው በላይ፣ ከምንራበው በላይ፣ ከሁኔታዎች በላይ፣ ከቤተሰቦቻችን በላይ፣,,,,ከሁሉም በላይ የእግዚአብሔር ክብር ያስፈልገናል....ያለ እግዚአብሔር ክብር ምንም ነን፣ ባዶ ነን፣ ሰላም የለንም፣ እረፍት የለንም፣ ደስታ የለንም፣ ህይወታችን አያምርም፣ አገልግሎታችን የሰውን ህይወት አይቀይርም፣ ከድካማችን መበርታት አንችልም፣ ከውድቀታችን መነሣት አንችልም፣ ወንጌል መስበክ አንችልም፣,,,ምንም ማድረግ አንችልም

ዘጸአት 33
¹⁷ እግዚአብሔርም ሙሴን፦ በፊቴ ሞገስ ስላገኘህ በስምህም ስላወቅሁህ ይህን ያልኸውን ነገር አደርጋለሁ አለው።
¹⁸ እርሱም፦ እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለ።

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
979 viewsYonatan Worku, 15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 11:43:25 የእግዚአብሔር ክብር ሲመጣ:-
(እባካችሁ የእግዚአብሔርን ክብር ቀንና ሌሊት ለሚራቡ ሁሉ አድርሱልኝ)

የወደቁ ይነሣሉ
የሳቱ ይመለሳሉ
ሰዎች ይቀደሳሉ
ያዘኑ ይፅናናሉ
መርገም ይሰበራል
የተበታተኑ አጥንቶች ይሰበሰባሉ
የተጣሉ ይታረቃሉ
የደከሙ ይበረታሉ
የታመሙ ይፈወሳሉ
የሞቱ ይነሣሉ
የደረቀው ይለመልማል
የፈረሰው ይገነባል
የተገነባው ይፈርሳል
የተረሳው ይታወሳል
ጨለማው ይበራል
የጠፋው ይገኛል
የተዘረፈው ይመለሳል
ሒሳብ ይወራረዳል
ምርኮ ይመለሳል
ሰላምና እረፍት ይበዛል
ጭንቀትና ድባቴ ይገፈፋል
ፍቅርና መቀባበል ይሆናል
ንሰሃና የንሰሃ ፍሬ ይታያል
ገደብና ክልከላ ይነሣል
ተዓምራት ይሆናል
ነፍሳት ወደ እግዚአብሔር መንግስት ይጨመራሉ
ፀጋዎች ይገለጣሉ
ባለራዕይ መሪዎች ይነሣሉ
ነብያቶች ይነሣሉ
እውነትና ፅድቅ ከፍ ይላሉ
ውሽትና ማስመሰል ስፍራ ያጣሉ
ዐመፀኝነት እና ትዕቢት፣ አድመኝነትና ራስ ወዳድነት ይጠራረጋሉ
ቅንነትና ትህትና ምድሪቱን ይቆጣጠራል
ዘፋኝነት ለዝማሬ፤ አለምን መውደድ እግዚአብሔር ብቻ እንዲመለክ ስፍራ ይለቃሉ
ፉክክር ወደ ትብብር ይለወጣል
መለያየት ወደ አንድነት ይመጣል
መከፋፈል በመቀባበል፤ መራራቅ በመቀራረብ ይተካል
ትውልድ ወደ ቤ/ክን ይመለሳል፤ ይጎርፋል
ከቸርች መከፋፈል ይወገዳል
ቤ/ክን ማስፈራት ትጀምራለኝ
መዐዛና ጠረን ይቀየራል
ጉስቁልናና ድህነት አይታሰብም
ትዳሮች ይገነባሉ
ቤቶች ይሰራሉ
ያላገቡ ያገባሉ፣ የከሰሩ ያተርፋሉ
የተደበቁ ይገለጣሉ
ኃያላን ይወለዳሉ
ምድር ታርፋለች፣ ጦርነት ይቆማል
ርህራሄና መተሳሰብ ይመጣል
ቅድስናና ንፅህና ታማኝነትና እውነተኝነት ይበዛል
ታሪክ ይቀየራል፣ ታሪክ ይሰራል
የሰዎች አዕምሮ ስለሚከፈት ስልጣኔዎች ይስፋፋሉ
ጨለማ ስፍራ ይለቃል፣ ሰይጣን ይዋረዳል፣ የተያዘ ይለቀቃል
ያረጁ ጥያቄዎች ይመለሳሉ
እንቆቅልሾች ይፈታሉ
ባልና ሚስት፣ ወላጆችና ልጆች ይቀባበላሉ፤ ይከባበራሉ
እግዚአብሔርን የማወቅና የመፍራት መንፈስ ይለቀቃል
የጥበብና የመገለጥ መንፈስ ይለቀቃል
የኃይልና የተዓምራት መንፈስ ይለቀቃል
የትንቢት መንፈስ ይለቀቃል፣ የትዕቢት መንፈስ ይነቀላል
ጫካው ይገለጣል፣ ተራራው ይደለደላል፣ ጠማማው ይቃናል፣ ስርጓጎጡ ሜዳ ይሆናል
ኢየሱስ ይደምቅና ሌላው ይፈዛል

የናፈቀኝ ይሄ ክብር ነው....አለምን አስንቆ ሰማይን የሚያተልቅ...በኢየሱስ ስም ያግኘን!!

አዋጅ አዋጅ የእግዚአብሔር ክብር እየመጣ ነው....get ready!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.3K viewsYonatan Worku, edited  08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 09:17:27 የሚያስፈልገን አንድ ነገር ብቻ እርሱም የእግዚአብሔር ክብር !!

ሉቃስ 10
⁴¹ ኢየሱስም መልሶ፦ ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥
⁴² የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።

መቼስ እኛ ሰዎች የምንፈልገው ነገር ማለቂያም ማብቂያም የለውም ብል ማጋነን አይሆንም፤ የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት ደግሞ የማንቆፍረው ጉድጓድ የማንፈነቅለውም ዐለት በፍፁም የለም.....በጣም የሚያሳዝነው ግን መፈለግ የሚገባንን ዋነኛ ጉዳይ ዘንግተን እርባና ቢስ የሆኑ ነገሮችን ለማግኘት ስንዳክር መገኘታችን ነው.......ጌታችን ኢየሱስ እህታችን ማርታ ከዋናው ይልቅ አላስፈላጊው ጉዳይ ሲያባክናት ተመልክቶ በግልፅ ቋንቋ የተናገራት ይህንኑ ነበር:-" ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው".....ተወዳጆች ሆይ አስተውላችሁታል ግን በጣም የሚያስጨንቀንና የሚያሳስበንን አብዛኛውን ጉዳይ ብንመለከት ይሄ ነው የሚባል አይደለም፤ ማለቴ ይህን ያህል ጨጓራችን እስኪላጥና ራስ ምታት እስኪይዘን ድረስ የሚያደርሰን መሆን አልነበረበትም........የሚያስፈልገን ጥቂት እና አንድ ነገር ብቻ ሆኖ ሳለ ልባችንን የከፋፈለው ጉዳይ ግን ብዛቱ ቤቱ ይቁጠረው.......ባጭር ቃል ለመናገር ለሰው ልጆች የሚያስፈልገን አንድ ነገር ብቻ ሲሆን እርሱም የእግዚአብሔር ክብር ነው፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ውስጥ የምንፈልገው ነገር በሙሉ አለና.....ልክ ወተት ውስጥ እርጎ፣ ቅቤ፣ አሬራ እና የመሳሰሉት ንጥረ ነገሮች እንዳሉ እንዲሁ እግዚአብሔርን ያገኘ ሰው የህይወት ጥያቄዎቹ ሁሉ የሚመለሱበት ማስተር ቁልፍ አግኝቷል፤ አምላካችን የጥያቄ ሁሉ መልስ ነውና......ሌላው ቀርቶ በህይወት መኖር እንኳን ያለው እግዚአብሔርን በመፈለግ ውስጥ ሲሆን እርሱን የሚፈልግ ደግሞ ለዘላለም አያፍርም:-“እግዚአብሔርም ለእስራኤል ቤት እንዲህ ይላልና፦ እኔን ፈልጉ፥ በሕይወትም ትኖራላችሁ፤”አሞጽ 5፥4.....ምን ዋጋ አለው ባለቤቱ በሌለበት ቤቱ ቢሞላና ቢደምቅ??? እውነቱን ልንገራችሁ የሚያምርብንና በሰላም የምንኖረው እንኳን ከህይወታችን ባለቤት ጋር ህብረታችን የሰመረ ሲሆን ብቻ ነው:-“አሁንም ከእርሱ ጋር ተስማማ፥ ሰላምም ይኑርህ፤ በዚያም በጎነት ታገኛለህ።”ኢዮብ 22፥21....ተወዳጆች ሆይ ለምን እንቅበዘበዛለን??? ለምንስ እንንከራተታለን?? የማይገባ ዋጋስ ለምን እንከፍላለን?? እንግዲህ የሚያባክኑንን ጉዳዮች ነቅሰን ከህይወታችን ላይ በመቀነስ ዋናው ላይ ብቻ ትኩረት እናድርግ እንጂ በይሉኝታ ገመድ ታሥረን ራሳችንን አንጉዳ፤ እግዚአብሔርም ካየልን ክብር አንጉደል......እግዚአብሔር ያላሸከመንን ቀንበር ተሸክመን ነፍሳችንን አናስመርራት......ዕድሜያችን አጭር በመሆኗ ለሚጠፋ መብል ሳይሆን ለዘላለም ህይወት እንሥራ......ዋናው ነገር ዋነኛ ማድረግ የህይወት መርሆዋችን ይሁን.......ብቻ እንደዚህ አይነትና የመሳሰሉትን ሃሳቦች እያሰብኩ ነበር.....እግዚአብሔር ዐይኖቻችንን ይክፈትልን!!

እግዚአብሔርን መፈለግ ስንጀምር የሚያስፈልገን ነገር በሙሉ ማግኔት በብረት እንደሚሳብ ወደ እኛ መምጣቱ ግድ ነው..

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.2K viewsYonatan Worku, edited  06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 09:06:16 ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን ነው!!

“ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።”ሮሜ 13፥11

በተለያየ ምክንያት ደክሞንና አቅም አጥተን ያለን ሰዎች እንዲሁም የህይወት ማዕበል መርከባችንን ወደ ቀኝና ወደ ግራ እያላጋ ተስፋ ቆርጠን መነሣት ላቃተን በሙሉ መልዕክት አለኝ.....ከእንቅልፍ የምንነሣበት ሰዓት ደርሷል፤ የነቃ ብቻ ክብሩን ያያልና......እንቅልፍ ውስጥ ያለ ሰው ግን የእግዚአብሔርን ሃሳብ መረዳት ስለማይችል ከመለኮታዊ ጉብኝት ጋር ፈፅሞ ይተላለፋል......ዛሬ በኢየሱስ ስም እፀልያለሁ ትውልዱን ከድካምና ከዝለት የሚቀሰቅስ የመንፈስ ቅዱስ ንፋስ መንቀሳቀስና በምድራችን ላይ እንደገና መንፈስ ይጀምር......ወዳጆቼ ሆይ ከእንቅልፋችን የምንነቃበት ዋነኛ ምክንያት ካመንንበት ግዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ላይ በእጅጉ ወደ እኛ በመቅረቡ ነው.......ሙሽራው ኢየሱስ ሊመጣ በደጅ ባለበት በዚህ በመጨረሻው ዘመን መዘናጋት ትርፉ እንደ ሰነፎቹ ቆነጃጅት መሆን ሲሆን አስተዋዮቹ ግን ድካሙን የሚቋቋሙበት በቂ ዘይት ይዘው ስለነበር ሙሽራውን አግኝተውታል.....ደጋግሜ እንደምናገረው የነቃ ያነቃል፤ ያልነቃ ግን ያንቃል......በፅድቅና በእውነት ለመንቃት ግን መንፈስ ቅዱስ ያሻናል፤ ያለ እርሱ እግዚአብሔርን መፈለግም ሆነ ለመንቃት መፈለግ አይታሰብምና.....በዚህ ምድር ላይ በስጋዊነት የሚደረግ ነገር ሁሉ ከንቱ ብቻ ሳይሆን አድካሚና ህይወት የለውም......ክርስትና በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተን ኢየሱስን በኃይልና በስልጣን የምንገልጥበት ከፍ ያለ ህይወት እንጂ ተረት ተረት አይደለም.......በነገራችን ላይ እግዚአብሔርን ማወቅ(ኢፒግኖሲስ) አዕምሮአችንን በመረጃዎች ከመሙላት ያልፋል ይልቁንም በሁለንተናችን እለት እለት የምንለማመደው እና የምንገልጠው ሰማያዊ ብርሃን ነው.....ሃሌሉያ......ያለ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ኢየሱስን በሙላት መግለጥ አይቻልም.......ወዳጆቼ ሆይ ሰማይ ሰማይ የማይሽት ነገር ሁሉ ምድር ምድር መሽተቱ፣ መንፈስ የሌለበትም እጅ እጅ ማለቱ አይቀርም!!......ስለዚህ ለእግዚአብሔር ክብር መንቃትና እንደወደደ እንዲሰራብን ራሳችንን መስጠት አለብን.......ወንዝ ከማይሻገር አገልግሎትና የህይወት ዘይቤ የምንድነው የመለኮት ክብር ሲያገኘን ብቻ ነው.....ወርቅና ብር እንኳን ያለመንፈስ ቅዱስ ከቆርቆሮነት ያለፈ ዋጋ የላቸውም.......ደቀመዛሙርቱም ነቅተው ክብሩን አዩ ተብሎ እንደተፃፈ በኢየሱስ ስም ከተኛንበት በመለኮት ክብር መንቃት ይሁንልን...ሻሎም!!

“ነገር ግን ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ ነቅተው ግን ክብሩንና ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች አዩ።”ሉቃስ 9፥32

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
122 viewsYonatan Worku, edited  06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ