2023-04-05 03:59:23
ወደድንም ጠላንም እውነቱ ይህ ነው፤ እንሸሽገውም ዘንድ አይቻለንም
በህግ ለመፅደቅ ማሰብ የኢየሱስን ሞት ከንቱ ማድረግ ነው
“የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።”ገላትያ 2፥21
ያለ ህግ እንዲሁ በነፃ የፀደቅሁበትን የእግዚአብሔርን ፀጋ አልጥልም....ህግን በመጠበቅ ለመፅደቅ መጣጣር/ መታገል ከፀጋ መጉደል ብቻ ሳይሆን መውደቅም ጭምር ነው!!
“በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።”ገላትያ 5፥4
እግዚአብሔር ሰዎች በፀጋ የሚፀድቁበትን መንገድ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ያሰናዳው በህግ በኩል ቢሆን ማንም እንደማይፀድቅ ስለሚያውቅ ነው!!
“ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎአልና ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው።”ገላትያ 3፥11
አንዳንዶች ከይሁዳ ወርደው እንደሙሴ ስርዐት ካልተገረዛችሁ አትድኑም በማለት በፀጋ ከዳኑበት ወደ ህግና ትዕዛዛት በመጠበቅ መዳን ወደሚል አስተምሮ ሊመልሷቸው ሲሞክሩ(ሐዋ 15:1)..ጴጥሮስ ተነስቶ የመለሰላቸው መልስ ያስገርማል.....እንዲህ አለ:-ይሄ በህግ በኩል የመፅደቅ ጉዳይ እንኳን ለአዳዲስ ደቀመዛሙርት ይቅርና እኛና አባቶቻችንም እንኳን ልንሸከመው ያልቻልነው ቀንበር ነበር....እዩትማ ቃሉን:-
ሐዋርያት 15
¹⁰ እንግዲህ አባቶቻችንና እኛ ልንሸከመው ያልቻልነውን ቀንበር በደቀ መዛሙርት ጫንቃ ላይ በመጫን እግዚአብሔርን አሁን ስለ ምን ትፈታተናላችሁ?
¹¹ ነገር ግን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ እንደ እነርሱ ደግሞ እንድን ዘንድ እናምናለን።
የህግ ፍፃሜ የሆነውን ክርስቶስ ኢየሱስን ማመን ብቻውን ለመፅደቅ ይበቃል.....ከዛ ውጪ ያለ አስተምሮ የስጋና የአጋንንት ነው!!
“የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።”ሮሜ 10፥4
ለምትሰሙኝ ሁሉ ቅዱሱ መፅሃፍ የሚለውን እናገራለሁ.....እግዚአብሔር በአንድያ ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ሥራ በኩል ሰርቶ የጨረሰልን እኛን ከዘላለም ፍርድ አድኖ ለማፅደቅ ያለምንም የእኛ መዋጮ(አስተዋፅዖ) ከበቂ በላይ ነው!!ሃሌሉያ
ኤፌሶን 2
⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።
1ኛ ቆሮንቶስ 1
²⁹ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት እንዳይመካ።
³⁰-³¹ ነገር ግን፦ የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደ ተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።
#SHARE #SHARE #SHARE
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
https://t.me/+I4DSx0eJ2iI2MDg0
130 viewsYonatan Worku, edited 00:59