Get Mystery Box with random crypto!

Zaphnath-paaneah

የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah
የሰርጥ አድራሻ: @zaphnathpaaneah1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 648

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-03-06 12:03:36 ኃይለኛውን ሳያሥሩ የኃይለኛውን ቤት መበዝበዝ አይቻልም!!

“ነገር ግን አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ ዕቃውን ሊበዘብዝ የሚችል የለም፥ ከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል።”ማርቆስ 3፥27

መፅሃፍ ቅዱሳችን በመክብብ ምዕራፍ ዘጠኝ ቁጥር አሥራ አንድ ላይ ሩጫ ለፈጣኖች፣ ሰልፍ ለሃያላን፣ እንጀራ ለጠቢባን፣ ባለጠግነት ለአስተዋዮች፣ ሞገስም ለአዋቂዋች እንዳልሆነ በአፅንዖት ያሳስበናል.....ይህም ማለት ሰው በጣም ፈጣን ስለሆነ አይደርስም፣ በጣም ኃያል ስለሆነ አያሸንፍም፣ በጣም ጠቢብና አስተዋይ ስለሆነም ብቻ ባለጠጋ መሆን አይቻለውም......በሌላ አነጋገር ሰዎች በጣም ስለለፉና ነጭ ላብ እስኪያልባቸው ድረስ በሥራ ስለደከሙ ብቻ ህይወታቸው ብሎም ቤተሰባቸው ይለወጣል ማለት አይደለም(ምንም እንኳን መሥራት መልካም ቢሆንም).....ወዳጆቼ ሆይ የእግዚአብሔርን ምሪት እንዴት መከተል እንዳለብን ካላወቅን ጉልበታችን በከንቱ ድካም ዕድሜያችንም በመንከራተት ያልቅብናል ደግሞም ይባክንብናል.......ደጋግሜ ለማንሣት እንደምሞክረው ከገሃዱ አለም ጀርባ ያለውን መንፈሳዊ አለም እንደሚገባ አለመረዳት ምስኪንነት ይመስለኛል፤ የሚታየው ሁሉ የመጣውና የሚዘወረው በመንፈሳዊ አለም ነውና.......በርዕሴ ላይ እንደለጠፍኩት በአንድ ቤት ውስጥ ያለውን የትኛውንም ሀብት ለመውሰድ በቅድሚያ ቤቱን የተቆጣጠረውንና የሚጠብቀውን የበላይ ጠባቂ እንዴት መያዝና ማስወገድ እንዳለብን ማወቅ እንደሚጠይቅ እንዲሁ ወደ ተባለልን ነገር ውስጥ ለመግባት በፊታችን የቆመውን ከልካይ መንፈስ መቃወምና ማፍረስ ይፈልጋል.....ብዙ የተነገረልን ነገር ቢኖርም ወደዚያ በሙላት እንዳንገባ የሚታገል የጨለማው መንፈስ አሰራር እንዳለ ማወቅ አማራጭ የለውም.....ምንም እንኳን በአለም ካለው ይልቅ በእኛ ያለው በጣም የሚበልጥ ቢሆንም መዘናጋት ግን ለጠላታችን ዕድልን ስለሚከፍትለት ብዙ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል፤ ስለዚህ ከእንቅልፋችን እንንቃ።።።።

እኔ በኢየሱስ ስም እፀልያለሁ:-በፊታችን እንደ ኤርትራ ባህር
የተጋደመና አላሳልፍ በማለት የሚፎክር የጨለማው ጉልበት የፈረሰ ይሁን፣ እንደ ፈርዖን ሠራዊት እግር እግራችንን የሚከታተል ሁሉ ለዘላለም ይዋረድ፣ ከእንግዲህ ከታየልን ከፍታ ወርደን በፍፁም አንኖርም፣ በፍርሃትና በመቅበዝበዝ አንመላለስም፣ ቤል የዋጠውን ይተፋል፣ አብ ያልተከለው ተክል ሁሉ ይነቀላል፣ ከአቅማችን በታች መኖር አበቃ፣ አዲስ ታሪክ ፅፈን እናልፋለን.....አሜን ያለ ሁሉ ሆነለት!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
983 viewsYonatan Worku, edited  09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 18:45:07 የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ ጌታና የዘላለም ህይወት ነው፤ ከእርሱ ውጭ ህይወትና ሰላም እንዲሁ እውነተኛ እረፍት የለም!!

“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።”
ዮሐንስ 5፥24

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
489 viewsYonatan Worku, 15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 13:14:59
Helps to study..
@ZaphnathPaaneah1
58 viewsYonatan Worku, 10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 13:09:34 እውነተኛ መነካት ወይስ መነካካት??

ታሪክን ስንመረምር በምድር ላይ አብዛኞቹ የመንፈስ ቅዱስ ሪቫይቫሎች የተነሱት ሰዎች ከፍተኛ ጭንቀት እና ውጥረት ውስጥ ገብተውና የመኖር ተስፋቸው ጨልሞ ባለበት ሰዓት ነበር ብንል ማጋነን አይሆንም.....የፓለቲካ፣ የኢኮኖሚ እንዲሁም የማህበረሰብ ልዩ ልዩ ችግሮች አፍጥጠውና አግጠው ሲመጡና ሰዎች ሰርተው መብላት እንኳን ሲያቅታቸው፣ ወጥተው መግባት ስቃይ ሲሆንባቸው፣ ከመኖር ይልቅ መሞት ሲያሰኛቸው በአጠቃላይ የሰው ጥረትና ግረት ሲያበቃ አስደናቂው የእግዚአብሔር እጅ መንቀሳቀስ ይጀምራል......ምድራችን ከተፈጠረች አንስቶ አሁን እስካለችበት ግዜ ድረስ ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ የሆኑ ዘርፈ ብዙና መጠነ ሰፊ የሆኑ ችግሮችን አስተናግዳለች፤ በዚህም የብዙዎች ህይወት እንደቅጠል ረግፏል....ለምሳሌ ያህል ጦርነቶች፣ በተለያዩ ስፍራዎች የተከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦች፣ አለማቀፍ ወረርሽኞች፣ አደጋዎች፣ ረሃብና ድርቆች ወዘተረፈ.....እግዚአብሔር በእንደዚህና በመሳሰሉ ችግሮች የተናጠችውን ምድር ለማፅናናትና ለማረጋጋት የሪቫይቫልን ንፋስ በተለምዶ ያነፍሳል.....ሃሌሉያ.....ወዳጆቼ ሆይ የእግዚአብሔር ክብር ግን አልናፈቃችሁም????......በተለይ በ20ኛው ክፍለ ዘመን በሃገረ አሜሪካ ብሎም በአለም ላይ የተከሰተውን "ዘ ግሬት ዲፕረሽን" እንዲሁም በ21ኛው ክፍለ ዘመን ተፈጥሮ የነበረውንና የአለማችንን ክፍለ ኢኮኖሚ በእጅጉ ያናጋውን "ሪሴሽን" ማስታወስ ብቻ ይበቃል......ይሁንና በእንደዚህ አይነት አስጨናቂና ተስፋ የሚደረግበት ምንም ነገር ሲጠፋ የሰዎች ዐይንና እጅ ወደ ልዑሉ አምላክ መነሳቱ ስለማይቀር በዘመናት መካከል አስደናቂ ነገር ይሆናል....ዛፍ እንኳን ቢቆረጥ ሥሩም ቢደርቅ ከውሃ ሽታ የተነሣ እንደገና እንደሚያቆጠቁጥ እንዲሁ የመንፈስ ቅዱስ ደመና ሲመጣ የማይታደስና የማይፈወስ እንዲሁም የማይፅናናና የማይበረታታ ማንም የለም....ይሄ ክብር ናፍቆኛል ......የእግዚአብሔር ክብር ከመቼውም ግዜ ይልቅ አሁን ለኢትዮጵያ ብሎም ለምድራችን ያስፈልገናል፥ የደረቁ አጥንቶቻችን እንዲገጣጠሙ፣ የፈረሱብን ቅጥሮች እንዲሰሩ፣ የተበላሹብን ነገሮች እንዲስተካከሉ፣ የደረቁብን ጉዳዮች እንዲለመልሙ፣ ዘመን ያስቆጠረ ጥያቄና እንቆቅልሽ እንዲፈታ.....በኢየሱስ ስም የእግዚአብሔር ክብር እንደገና ይምጣልን ...ከልምምድና ስጋዊ ነገር ከበዛበት አገልግሎት የሚያወጣ ክብር ከመቼውም ግዜ ይልቅ ያስፈልገናል....ልክ አስበሪ(ኬንታኪ) ላይ እየሆነ እንዳለው አይነት ሰዎችን ወደ ንሰሃ የሚያመጣ ጉብኝት ምድራችንም በኃይል ያሻታል.......ጌታ ሆይ:-እንደገና ሰማያት ይከፈቱና ክብርህን አጥግበን፤ የሚያረካን ይሄ ብቻ ነውና...አሁን ማጋፋት ሳይሆን እውነተኛ መነካትን እንናፍቃለን!!

“ውኃ ባሕርን እንደሚከድን ምድር የእግዚአብሔርን ክብር በማወቅ ትሞላለችና።”ዕንባቆም 2፥14

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
743 viewsYonatan Worku, 10:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 23:29:38 7ቱ የብሉይ ኪዳን በዓላትና ኢየሱስን የሚያሳዩበት መንገድ:-
{Amharic + english+ hebrew}

1. የፋሲካ በዓል(passover)[pesach]
ዘፀ 12:1-20፣ ዘሌ 23:5-8

የኢየሱስን ስቅለት(crucifiction) ያሳያል

2. የቂጣ በዓል(unleavened bread)[Matzah]
ዘፀ 12:1-20፣ ዘሌ 23:5-8

የኢየሱስን ሞት(death) ያሳያል

3.የበኩራት በዓል/የመወዝወዝ በዓል
(first fruits)[yom habikkurim]
ዘፀ 23:16፣ ዘሌ 23:9-14

የኢየሱስን ትንሣኤ(resurrection) ያሳያል

4. የመከር/በዓለ ሃምሳ/ጴንጤ ቆስጤ/የሰባቱ ሳምንታት በዓል(pentecost)[shavuot]
ዘፀ 34:22

የመንፈስ ቅዱስን መውረድ ያሳያል

5. የመለከት ቀን በዓል(trumpets)[yom teruah]
ዘሌ 23:23-25፣ ዘኁ 29:1፣ 1ተሰ 4:16

ንጥቀትን(rupture) ያመለክታል

6. የስርየት ቀን በዓል(atonement)[yom kippur]
ዘሌ 23:26-32

የኢየሱስን ዳግም ምፅዐትና ህዝቡን ይቅር ማለቱን(መታረቁን) ያሳያል

7. የዳስ በዓል(tabernacles)[sukkot]
ዘሌ 23:39-43፣ ዘካ 14:16

ኢየሱስ በህዝቡ መካከል ማደሩን ያመለክታል(የሺህ አመቱን መንግስት/millinial kingdom)

ከሰባቱ በዓላት በ3ቱ ወንዶች ሁሉ ቤተመቅደስ ድረስ መጥተው በዓሉን ማክበር ግዴታቸው ነበር(የቂጣ በዓል፣ በዓለ ሃምሳ እና የዳስ በዓል)

“በዓመት ሦስት ጊዜ፥ በቂጣ በዓል፥ በሰባቱ ሱባዔም በዓል፥ በዳስም በዓል ወንዶችህ ሁሉ በአምላክህ በእግዚአብሔር ፊት እርሱ በመረጠው ስፍራ ይታዩ፤ በእግዚአብሔርም ፊት ባዶ እጃቸውን አይታዩ።”ዘዳግም 16፥16

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
788 viewsYonatan Worku, 20:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 10:15:01 በመንፈስ ቅዱስ መረጋጋት!!

መንፈስ ቅዱስ የሞላበት ሰው በመረጋጋት ይታወቃል

መቼስ ጥድፊያና ችኮላ የሞላበት ዘመን ላይ እንደሆንን ለመረዳት ነብይ መሆን አያስፈልግም......አደገኛው ነገር ደግሞ የብዙ ሰዎች ውጫዊ አለመረጋጋት መነሻው የውስጥ(የልብ) እረፍት ማጣት መሆኑ ነው.......ማንም ውስጡ ሰላም ያልሆነና ያልተረጋጋ ሰው ውጭው ሰላም ሊሆንና ሊረጋጋ ከዛም ሌላውን ሊያሳርፍ በፍፁም አይቻለውም......በነገራችን ላይ በግሌ ይሄ ጉዳይ በጣም ይገባኛል ምክንያቱም ውስጣዊ አለመረጋጋትን በተግባር አውቀዋለሁ፤ እጅጉኑ ያስጨንቃል.......የሰው ልጅ ውስጡ ከሚታመም አሥር እጅ ውጭውን ቢታመም ይሻላል.....ወደ ነፍሱ(ራሱ) ያልተመለሰና ለምን እንደሚኖር እንኳን የማያውቅ ሰው በባዶነት የሚሰቃይ ብሎም በመቅበዝበዝና በመንከራተት ዘመኑን የሚጨርስ ነው........ዳግም የተወለደና መንፈስ ቅዱስ የተሞላ ሰው ግን ዋነኛ መገለጫው 'መረጋጋት' እንደሆነ በደንብ ገብቶኛል......ይሄ ማለት ግን ሰላምን የሚገዳደሩ ውጫዊ ተፅዕኖዎች የሉም ማለት አይደለም ይልቁንም መንፈስ ቅዱስ የተሞላ ልብ በየትኛውም ተግዳሮት በቀላሉ አይፍረከረክም....ሃሌሉያ....ወዳጆቼ ሆይ ይህንን ጉዳይ ከመፅሃፍት አንብቤና መርምሬ ሳይሆን የምነግራችሁ በራሴ ህይወቴ ላይ በዐይኔ በብረቱ አይቼና አጣጥሜ እንጂ!....መንፈስ ቅዱስ ይሄ ነው ከማይባል መቅበዝበዝና ግራ መጋባት እንዲሁም የውስጥ ሁካታና ረብሻ አድኖኛል ስል ከዚህ በፊት ያለ መንፈስ ቅዱስ የተንከራተትኩባቸውን ጊዜያት ጠንቅቄ ስለማስታውስና በእርግጥም መዳኔን በሰውነቴ አሁን ስላረጋገጥኩ ነው.......ይሄ ማለት ግን ውጫዊ ችግሮች የሉም ማለት አይደለም፤ ውስጡ ያረፈና የተፈወሰ ሰው ግን የትኛውንም ውጫዊ ግፊት ያሸንፋል እንጂ እሱ አይሽነፍም.......አሁን መንፈስ ቅዱስ የማይናወጥ መረጋጋቴ ነው ብዬ ላገኘሁት ሁሉ ስመሰክር በፍፁም አላፍርም.....ምናልባት እንደ 'ድሮው እኔ' የመረጋጋት ጥያቄ ያለባችሁ ብትኖሩ መፍትሄው ኢየሱስ ብቻ ነው....ገንዘብ፣ ዝና፣ ሃብት፣ ስልጣን፣ ትዳር፣ ሃገር መቀየር እና የመሳሰሉት በራሳቸው መልካም ቢሆኑም የውስጥን ባዶነት ግን ሞልተው ሊያረጋጉ አይችሉም...ሱስም ቢሆን ደስታ የሚሰጥ ቢመስልም ግዜያዊና ለአደገኛ የጎንዮሽ መዘዝ ያጋልጣል.....ስለዚህ ወደ ኢየሱስ መጥታችሁ እንድትገላገሉ እጋብዛችኃለሁ፤ እርሱ እውነተኛ የዘለላም እረፍት ምንጭ ነው...ፀጋ ይብዛልን!!

“ዕረፉ፥ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ እወቁ፤ በአሕዛብ ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፥ በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።”
መዝሙር 46፥10

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
781 viewsYonatan Worku, edited  07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 11:51:36 አይዟችሁ ሰይጣን ትንሹን ሲዘጋው እግዚአብሔር ትልቁን ይከፍተዋል!!

በዘመናት መካከል መልካም ነገር እንዳይሆንልን የሚፈልግ ክፉ ባላንጣ እንዳለን ማወቅ አለብን፤ ይኽውም ዲያቢሎስ ነው......ምንም እንኳን ስለ እርሱ እያወራው እሱን ማግዘፍና ማንቆለጳጰስ ባልወድም ነገር ግን ልንረዳቸው የሚገቡ እውነታዎች መኖራቸው ግን አያጠያይቅም.....ስለ ጠላታችን ዲያቢሎስ ፅንፍ የያዘ ዕውቀት ትክክል አይደለም......ይህንን ስል ምን ማለቴ ነው???? ለምሳሌ ሁሉንም ችግሮች ከሰይጣን ጋር ማያያዝ አንዱ ስህተት ሲሆን(devil conciousness) በተቃራኒው ደግሞ በምድር ላይ እየተከናወኑ ባሉ ነገሮች ላይ ሰይጣን ምንም ሚና እንደሌለው አድርጎ መገመትም ሞኝነት ነው፤ ይልቁኑ ግን መንፈሳዊ ሚዛናዊነታችንን መጠበቅ ግድ ይላል....የሆነው ሆኖ የእኛን ጥፋትና ውድቀት የሚፈልግ ስለዚህም ቀንና ሌሊት የሚተጋ ጠላት እንዳለን በፍፁም ሊታበል አይችልም....ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ስለ እኛ የሚራራ፣ ለሰከንድ እንኳ የማይተኛና የማያንቀላፋ፣ አይኖቹ እንደ እሳት ነበልባል የሆኑ፣ ጉልበቱ ከቶ የማይዝል የጌታዎች ሁሉ ጌታ የነገስታት ሁሉ ንጉሥ ከእኛ ጋራ ነው...ሃሌሉያ...ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምህረትና ጥበቃ የተነሣ እንጂ የሚያጠፉ ነገሮች ስላልነበሩ አይደለም......ወዳጆቼ ሆይ ይህን አንድ ነገር እወቁ ከጨለማው ፕሮግራም የጌታ ማዳን ይበልጣል፤ ይቀድምማል.......ጠላታችን ተጠንቅቆና ተጠብቦ የዘጋውን እግዚአብሔር ተረጋግቶ መክፈት እኮ ልማዱ ነው.....ይህንን ትንቢታዊ ቃል በኢየሱስ ስም አውጃለሁ:- የጠፋው እንኳን ጠፋ፣ የተበላሽው እንኳን ተበላሽ፣ የሄደው እንኳን ሄደ፣ የተቃጠለው እንኳን ተቃጠለ፤...ዝም በሉ እግዚአብሔር የተሻለ ነገር አለው......እንደሄደው ብቻ አይደለም:-እጥፍ ድርብ ሆኖ ይመለሳል፣ ሰባት እጥፍ ሆኖ ይመለሳል፣ ከበረከት ጋር ይመለሳል፣ ከመትረፍረፍ ጋር ይመለሳል.....ተወዳጆች ሆይ በሄደው ነገር ስንፀፀት የሚደሰተው ክፉው ዲያቢሎስ እና ጀሌዎቹ ብቻ ናቸው.....ስለዚህ ማመስገን እንጀምር፣ መፅናናት እንጀምር፣ ማምለክ እንጀምር፣ መደሰት እንጀምር፤ ያኔ የሞተብን አልዓዛር ይነሣል፣ የጠፋብን ይገኛል፣ የወደቀብን ይነሣል፣ የደከመብን ይበረታል፣ የጨለመብን ይበራል.....ሰላምና ፀጋ ከሁላችን ጋር ይሁን!!

“ጠላቴ ሆይ፥ ብወድቅ እነሣለሁና፥ በጨለማም ብቀመጥ እግዚአብሔር ብርሃን ይሆንልኛልና በእኔ ላይ ደስ አይበልሽ።”ሚክያስ 7፥8

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
895 viewsYonatan Worku, edited  08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 18:45:44 ቅጥራችሁን አብጁ!!

“ጕድጓድን የሚምስ ይወድቅበታል፥ ቅጥርንም የሚያፈርስን እባብ ትነድፈዋለች።”መክብብ 10፥8

ቅጥርን በሚገባ ማበጀት ከብዙ ጥፋቶች ይታደጋል......አንድ ጥቃትን ለማድረስ ወጥኖ ወደ አንድ ቤት የመጣ ሰው በመጀመሪያ የሚያገኘው አጥሩን ነው......አጥሩ እንደነገሩ የተሰራ ቤት ከሆነ ለመጠነ ሰፊ አደጋዎች ይጋለጣል፤ በአግባቡና በጥንቃቄ የተሰራ ከሆነ ግን አስተማማኝና ቤት ውስጥ ያሉት ሃብትና ንብረቶች ሁሉ እንዲጠበቁ ያደርጋል......መፅሃፍ ቅዱሳችን ቅጥርን የሚያፈርስ በእባብ እንደሚነደፍ በግልፅ ያስተምረናል፤ በተለይ የነህምያን መፅሃፍ ስናጠና ቅጥርን መሥራትና መጠገን መሠረታዊ ነገር መሆኑን እንረዳለን......አይሁዳውያን ከ70 አመታት የባቢሎን ምርኮ ቆይታ በኃላ ወደ አገራቸው በ3ት ዙሮች እንደተመለሱ እናውቃለን.......ከተመለሱም በኃላ በመሪያቸው ዘሩባቤል አማካኝነት ቤተመቅደሱ የተሠራ ሲሆን ነህምያ ደግሞ የኢየሩሳሌምን ቅጥር በ52 ቀናት ሰርቶ አጠናቋል.....ይህም ቤተመቅደሱን ብቻ ሳይሆን ቅጥሩንም መስራት በጣም አስፈላጊ መሆኑን ያሳየናል....ቤተመቅደሱ በሚገባ ተገንብቶ ቅጥሩ ግን ከሌለ ምን ዋጋ አለው?? እንደገና ወደ ፍርስራሽነት የመቀየር አደጋ ይጋረጥበታል......ተወዳጆች ሆይ ቅጥራችንን መሥራት አለብን፤ እያወራሁት ያለሁት ስለመንፈሳዊ ቅጥር መሆኑን ይታወቅልኝ......አጥር የሌለው ህይወት የአጋንንቶችና የወንበዴዎች መፈንጫ ከመሆን ውጪ ምንም አማራጭ የለውም.......መንፈሳዊ ህይወታችን፣ ቤተሰባችን፣ ሥራችን፣ ሃገራችን,,,,እንዲጠበቁ የውስጥ ስራ መስራት መልካም እንደሆነ ሁሉ የፈረሰብንንም ቅጥር ማደስ ግድ ይላል.....በነገራችን ላይ እባብ አጥርን አልፎ ለመግባት የሚፈልገው በጣም ቀጭን ቀዳዳ ብቻ ሲሆን ይህም በህይወታችን ላይ የምንንቀው አንዳች ክፍተት ሊኖር እንደማይገባ ያሳየናል......ዛሬ ችግር የለውም ብለን የናቅነው ጉዳይ ህይወታችንን ጨምሮ ሌሎች ብዙ ነገሮችን እንዳያሳጣን ከእንቅልፋችን ልንነቃ ይገባል.....መክሊቶቻችንን(ውድ ሃብቶቻችንን) ከተሠረቅንና ከተዘረፍን በኃላ ብንባንን ምን ይጠቅመናል፤ ከማልቀስና ከመፀፀት ውጪ.....ዛሬ ለራሴም ሆነ ለሚሰሙኝም ሁሉ እፀልያለሁ:-ከእንቅልፋችን የሚያነቃን ፀጋ ይለቀቅልን፣ የፈረሱብን ቅጥሮቻችን እንደገና ይሰሩ፣ የጠፉብን መክሊቶች ይገኙ፣ ህይወታችን ይታደስ፣ ያረጁ ጥያቄዎቻችን ይመለሱ፣ የሞተብን ነገር ይነሣ፣ የታመመ ይፈወስ...በኢየሱስ ስም!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
919 viewsYonatan Worku, 15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 08:54:48 1ኛ ዮሐንስ 5
¹⁸ ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን እንዳያደርግ፥ ነገር ግን ከእግዚአብሔር የተወለደው ራሱን እንዲጠብቅ ክፉውም እንዳይነካው እናውቃለን።
¹⁹ ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
35 viewsYonatan Worku, edited  05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-26 17:57:34 በዘፈን አጋንንት ይገባል..
(ይድረስ ለዘፋኞችና ዘፈን አፍቃሪዎች ሁሉ)

ዘፈንን በተመለከተ እዚህም እዚያም ክርክሮች ይነሣሉ፤ ለምን እንደሚነሱ ግን አይገባኝም.......በእኔ እምነት ዘፈንን በተመለከተ ይፈቀዳል ወይስ አይፈቀድም ብሎ ለድርድር መቀመጥ መንፈሳዊ ዝቅጠት ውስጥ የመግባት ዋነኛ መገለጫ ነው(ልክ መርዝ መጠጣት ይፈቀዳል ወይስ አይፈቀድም ከማለት ለይቼ አላየውም)....Its weird.....ትኩረታቸው እግዚአብሔር ላይ ያልሆኑና አለማዊነትን የሚያስፋፉ እንዲሁም ንፅህናን በማጉደል ስጋዊነትን የሚያንቆለጳጵሱ ሙዚቃዎች በሙሉ ዘፈኖች ናቸው፤ አምላክንም አያከብሩም......እንደዚህ አይነት ሙዚቃዎች ፈጣሪን ሳይሆን ፍጡርን ያመልካሉ ብቻም ሳይሆን ለጨለማው አለም በር ከፋች(portal) ናቸው.......ርኩሳን መናፍስት ወደ ሰዎች ህይወት ከሚገቡባቸው ዋነኛ በሮች መካከል ዘፈን ግንባር ቀደም ነው.....ልክ እውነተኛ ዝማሬዎችንና መንፈሳዊ ቅኔዎችን ለእግዚአብሔር በምንዘምርበት ግዜ የእግዚአብሔር ህልውና ሁለንተናችንን እንደሚቆጣጠረው ሁሉ ዘፋኝነት ውስጥ ደግሞ የኤልዛቤል መንፈስ(የርኩሰት መናፍስት) እና በአጠቃላይ አለማዊነትንና የሞራል ውድቀትን የሚያስፋፉ የጨለማው አለም ጀሌዎች ወደ ሰዎችና ወደ ምድሪቱ ይለቀቃሉ......የመጥምቁ ዮሐንስ አንገት እንዲቆረጥ ምክንያት የሆነው እኮ የሄሮዳይዳ ልጅ ላይ የነበረው የዘፈን መንፈስ ነው.....ለዚህ ይመስለኛል መፅሃፍ ቅዱስ በግልጥ ዘፋኞች የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርሱም ብሎ የሚናገረው.....ምን አለበትና/ምን ችግር አለው አይነት እሳቤዎች ውድቀትን ያስከትላሉ....ይህንን ስናገር ግን በተለይ በዚህ ዘመን ቀላል ቁጥር የሌላቸው "መዝሙሮች" ከዘፈን የተሻሉ እንዳይደሉ በመካድ አይደለም.....ኢየሱስንና መስቀሉን እንዲሁም ዳግም ምፅዐቱን የሚያጎሉ ዝማሬዎች በእጅጉ ያስፈልጉናል.....በተረፈ ግን ሁለት እግር አለኝ ተብሎ እዚህና እዚያ መርገጥ መፅሃፍ ቅዱሳዊ አይደለም፤ አደጋም አለው......ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ ሁሉ ቅን ላትሆን ትችላለች፤ ሰባት ግዜ ከተጣራ ብር ይልቅ የነጠረው የእግዚአብሔር ቃል ወደሚያስተምረን እውነት ብንመለስ ብቻ ግን ህይወትና እረፍት ይሆንልናል.......የጌታ ሰላምና ፀጋ ከሁላችንም ጋር ይሁን!!!

ገላትያ 5
¹⁹ የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥ መዳራት፥
²⁰ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥
²¹ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
723 viewsYonatan Worku, edited  14:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ