Get Mystery Box with random crypto!

Zaphnath-paaneah

የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zaphnathpaaneah1 — Zaphnath-paaneah
የሰርጥ አድራሻ: @zaphnathpaaneah1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 648

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-01-14 11:02:00
75 viewsYonatan Worku, 08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-14 10:51:56 ኃላፊነትን ውሰድ/ጅ!

በህይወታችን ላይ ኃላፊነትን ያልወሰድንበት የትኛውንም ጉዳይ ልንለውጠው አንችልም.....ለውጥ የሚጀምረው ሰበበኝነትን አሽቀንጥረን ጥለን ለተፈጠሩት አያሌ ችግሮች ተጠያቂ እንደሆንን ስናስብና ኃላፊነትን መውሰድ ስንጀምር ብቻ ነው.....ምናልባት ነፍስያችንን እስክናውቅ ድረስ የኖርናቸውን ግዜያት በተመለከተ ቤተሰቦቻችን፣ የተማርንባቸው ትምህርት ቤቶች፣ ያደግንባቸው ሰፈሮች እና ጓደኞቻችን ተጠያቂ ሊሆኑ ይችሉ ይሆናል ከዛ በኃላ ግን ምንም ማሳበቢያ ብናቀርብ ተቀባይነት የለውም....እኛ እኮ አርፎ የተቀመጠበት ቦታ ላይ ሄደን መተነው ስናበቃ እንቅፋት መታኝ ብለን የምናወራ ኩሩ ህዝቦች ነን!......ኮሌጅም እያለን 'F' ሲሆን ፈላብኝ ወይም አስተማሪ አበላሽብኝ ወይም ሰጠኝ ብለን ስንል 'A' ሲሆን ግን ጎጆቤቱን ደረደርኩት፣ አገኘሁ እና የመሳሰሉትን መናገር በጣም ከመለመዱ የተነሣ በማህበረሰቡ ዘንድ ትክክል እየመሰለ ሄዷል......እንደኔ እንደኔ እንደ ሃገርም ሆነ እንደግለሰብ ብዙ ነገሮቻችን ሳይለወጡ ዘመናትን ያስቆጠሩት ራስን ተጠያቂ አድርጎና ኃላፊነትን ወስዶ ችግሮችን ለመቀየር ከመሞከር ይልቅ ሰበበኞች ስለሆንን ይመስለኛል....በነገራችን ላይ ማሳበብ የሚባለው ነገር ከተጀመረ መቼስ ማለቂያ እንደሌለው ዝናብ የማይቋረጥ እንደሆነ ይታወቃል.....ይሁንና ግን የእናቴ ቀሚስ አደናቀፈኝ እያሉ እንደ ገደል ማሚቱ መደጋገም ጉንጭ ከማልፋት በዘለለ ምንም ፋይዳ ከሌለው ኃላፊነትን መውሰድ አማራጭ የለውም.....ስለዚህ ይህንን የማሳበብና የማላከክ ካባ ከላያችን ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ቀድደን እንጣለው....እግዚአብሔር የእኛን ህይወት ለመቀየር የማንም እገዛ አያስፈልገውም......በህይወታችን ላይ ለሆነውና እየሆነ ስላለው ነገር ሁሉ ግን ኃላፊነትን እንውሰድ.....ፀጋ ይብዛልን!!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
903 viewsYonatan Worku, edited  07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 16:22:20 አገሬንም አስፋ(enlarge my territories/coast)

በመፅሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ የምናገኘውና ያቤፅ የተባለው ሰው ከፀለያቸው አራት ፀሎቶች ውስጥ አንደኛውም እባክህን አገሬን አስፋ ይሰኛል......በእርግጥም አስደናቂ ፀሎት ነው......አገሬን አስፋ ብሎ ሲል በዋነኝነት እየተናገረ ያለው እየኖረበት ስላለው አገር ስፋትና ጥበት ሳይሆን እሱ በምድር ላይ ሲኖር በተሰጠው ዘመኑ ሊፈጥር የሚገባውን የመልካም ተፅዕኖ መጠንን ይመለከታል.....ሁልግዜ እንደማነሳው ሁሉም ሰው የተፈጠረበትና ሊሰራው የተገባው የህይወት አሳይንመንት አለው....ይሁንና ግን ህልማችንን በምን ያህል የተፅዕኖ ልክ እናሳካዋለን የሚለውን በደንብ ደጋግሞ ማጤን ያስፈልጋል.....በአለም ደረጃ በጎ ተፅዕኖ በመፍጠር ለሰው ዘር ሁሉ ትልቅን አስተዋፅዖ ማበርከት እየቻልን ነገር ግን ከሰፈር ማለፍ ካልቻልን ዋጋ የለውም......ስለዚህ ህልማችንን እንዴት ወደ መሬት ማውረድ እንዳለብን በሚገባ ማጥናትና ከመንፈስ ቅዱስም ምሪትን መቀበል ግድ ይላል.....ያቤፅ ይሄ እውነት ስለገባው ይመስለኛል ይህንን ጉዳይ የዘወትር ፀሎቱ ያደረገው!.....እንደ ንሥር ከደመና በላይ መብረር እየቻልን እንደ ሸለምጥማጥ እየተሽለኮለክን በፍፁም ዕንቁ ዕድሜያችን ማለቅ የለበትም.....ዛሬ እኔ ለራሴና ለሚሰሙኝ ሁሉ ከልቤ እፀልያለሁ:-"እግዚአብሔር አምላካችን በነገር ሁሉ ድንበራችንን ያስፋው፣ ወደ ቀኝና ወደ ግራ እንዲሁም ወደ ላይ በነገር ሁሉ ማደግ ይሁንልን፣ የምንጀምረው ነገር ሁሉ የሚበዛና የሚትረፈረፍ ይሁን፣ የሚያየን ይውደደን፣ ራዕዮቻችን በብዙ እጥፍ ፍሬን ማፍራት እና መብዛት ይጀምሩ፣ ግዜው ያላለፈበትና ያልሻገተ በረከት ውስጥ መግባት ይሁንልን....በኢየሱስ ስም...አሜን።።።"

“ያቤጽም፦ እባክህ፥ መባረክን ባርከኝ፥ አገሬንም አስፋው፤ እጅህም ከእኔ ጋር ትሁን፤ እንዳያሳዝነኝም ከክፋት ጠብቀኝ ብሎ የእስራኤልን አምላክ ጠራ፤ እግዚአብሔርም የለመነውን ሰጠው።”
1 ዜና 4፥10

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.1K viewsYonatan Worku, edited  13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 10:12:17 ትልቅ እግዚአብሔር እንጂ ትልቅ ችግር የለም!!

ወደ አይናችን የቀረበ የትኛውም ትንሽ ነገር ትልቅ ሆኖ መታየቱ አይቀርም፤ በተቃራኒው ደግሞ ከአይናችን የራቀ ትልቅ ነገር ደግሞ አንሶ ይታየናል.....ይህም የሚያመላክተው አንድን ነገር ትልቅ ወይም ትንሽ የሚያሰኘው ከእይታችን ካለው ቅርበትና ርቀት የተነሣ መሆኑን ነው.....ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለችግሮቻችን ያለን ዕይታና እሳቤ ምን ያህል ችግሮቻችንን ሊያከብዱ ወይንም ሊያቀሉ እንደሚችሉ መገንዘብ እንችላለን.......በመሠረቱ ከባድ ወይም ትልቅ የሚባል ችግር የለም፤ ትልቅ አምላክ እንጂ!.......ይሁንና ግን ትንንሽ ችግሮቻችንን አንቆለጳጵሰን በገዛ እጃችን ልናገዝፈው እንደምንችል ማወቅ አለብን......መፅሃፍ ቅዱሳችን እግዚአብሔር በወጀብና በአውሎ ንፋስ ውስጥም ቢሆን መንገድ እንዳለው አስረግጦ ያስተምረናል......መንፈስ ቅዱስን እንዴት መስማት እንዳለብን ከተማርን መውጫና ማምለጫ የሌለው መከራና ችግር እዚህ ምድር ላይ የለም......አብዛኛውን ግዜ ግን ሰዎች እግዚአብሔርን ከመስማት ይልቅ ሰውንና ስጋን ወደመስማት ሲያዘነብሉ ውሉ እንደጠፋበት ክር ነገሮች ሁሉ ይቆላለፍባቸዋል.....በመንገዳችን ሁሉ ግን እግዚአብሔርን ስናስቀድም በፀጥታና በዕረፍት ስለምንመላለስ ለህይወታችን ፍፁም ዋስትና ይኖራታል......ችግሮቻችን እንደዚህ አድገው ያስጨነቁንና ያሳጡን እኮ ወደ እይታችን በማስጠጋት ከፍተኛ ትኩረት ስለሰጠናቸው እንጂ በጣም ትልቅ ሆነው አይደለም.....ተወዳጆች ሆይ ለችግሮች ያለን አመለካከት በአጠቃላይ መቀየር አለበት ብዬ አምናለሁ.....እውነቱን እንነጋገር ከተባለ በጣም ብዙ ሰውን የሚጎዳው ችግሩ ሳይሆን ለችግሩ ያለው ምልከታ የተንሸዋረረ መሆኑ እንጂ......ችግሮቻችንን እንደ መማሪያ ዕድል አድርገን መቁጠር መጀመር ይኖርብናል(<'problems are opportunities'>chinese proverb).....በአለማችን ላይ ያሉ ግኝቶች በሙሉ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረግ ጥረት የመጡ መሆናቸውን አንርሣ....ምናልባት የዛሬ ተግዳሮቶቻችን የነገ የቢዝነስ ምንጮቻችንና የጥንካሬዎቻችን ምክንያት ሊሆኑ እንደሚችሉ ማን ያውቃል??....ስለዚህ አሁን እያለፍንባቸው ስላሉ መጠነ ሰፊና ዘርፈ ብዙ ችግሮች ልባችን ሊሰበርና ሊያዝን በፍፁም አይገባም....በመሠረቱ ቋሚና ዘላለማዊ የሚባል ችግር በዚህ ምድር ላይ የለም፤ የምናመልከው አምላክ ብቻ ህያውና ዘላለማዊ ነው.....በመሆኑም መከራ መኖሪያችን ሳይሆን ማለፊያችን መሆኑን ተረድተንና አውቀን መፅናት አማራጭ የለውም....እግዚአብሔር ከችግሮቻችን ሁሉ ይልቅ ትልቅ አምላክ ነውና አይኖቻችን በእሱ ላይ ብቻ ይሁኑ እላለሁ..ሻሎም!!!

“ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።”1ኛ ቆሮንቶስ 10፥13

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.1K viewsYonatan Worku, edited  07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 17:30:58 ልትሞትለት/ችለት እንኳን የተዘጋጀህለት/ሽለት ህልም አለህን/ሽን???......ካለህ/ሽ በጣም ዕድለኛ ነህ/ሽ መኖር ጀምረሃል/ሻል ማለት ነው!!!!

"If you have not discovered something
you are willing to die
for, then you are not fit to live."

Martin Luther King Jr.

“ራእይ ባይኖር ሕዝብ መረን ይሆናል፤ ሕግን የሚጠብቅ ግን የተመሰገነ ነው።”ምሳሌ 29፥18

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.1K viewsYonatan Worku, 14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 12:13:04 መንፈሳዊውን አለም የምንረዳበት ጥልቀት(depth) በምድር ላይ ያለንን የተፅዕኖ መጠን(positive impact) ይወስነዋል!!

እያንዳንዱ ሰው በምድር ላይ ሲኖር የሚያስባቸው ነገሮች ተከናውነውና የህይወት አላማዎቹ ሰምረው ማየት ይፈልጋል....ይሁንና ግን ከመፈለግ እና ከመመኘት በዘለለ ነገሮች የሚሰሩበትን መርህ ጠንቅቆ ማወቅና ማድረግ አማራጭ የሌለው ሲሆን ወደምንናፍቀው ስኬትም በቀላሉ እንድንደርስ ይረዳናል.....መፅሃፍ ቅዱሳችን የሚታዩት ነገሮች ሁሉ ከማይታየው(ከመንፈሳዊው አለም) እንደመጡ ይነግረናል......መንፈሳዊው አለም ላይ ተሰርቶ የተጠናቀቀ ነገር ብቻ ወደዚህ ገሃዱ አለም ይገለጣል.....እስቲ ክፍሉን እንመልከተው:-

“ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተዘጋጁ፥ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን።”ዕብራውያን 11፥3

ስለዚህ የትኛውም ለውጥ የሚጀምረው ከመንፈሳዊው አለም ነው.....መንፈሳዊውን አለም በተረዳነውና እንዴት በአኗኗራችን መግለጥ እንዳለብን ባወቅን መጠን በምድር ላይ በየቀኑ በአሽናፊነትና በድል አድራጊነት መኖር እንችላለን፤ በዘመናችንም ሊያስቆመን የሚችል አንዳች ኃይል አይኖርም......ቀደም ብዬ ያነሣሁትና አሁንም ደግሜ በአፅንዖት መናገር የምፈልገው ነገር ቢኖር መንፈስ አለም ላይ ያልጀመረና በገሃዱ አለም ላይ የተገለጠ አንዳች ነገር አለመኖሩን ነው.....የሰው ሁለንተና መንፈስ ነፍስና ስጋ በአንድነት እንደሆነ እናውቃለን፤ አደራደሩም(order) ልክ እንደዚሁ ማለትም በመንፈስ ይጀምርና ከዚያ ነፍስ በመጨረሻም በስጋ ይገለጣል:-

“የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።”1ኛ ተሰሎንቄ 5፥23

መንፈስ አለም ላይ የተሸነፈና ግንኙነቱ የተቋረጠ ማለትም ከእግዚአብሔር መንፈስ ጋር ህብረትን በማድረግ ምሪትን መቀበል ያቆመና እንደ ስጋ ፈቃድ መመላለስ የጀመረ ሰው በምድር ላይ ያለው ህይወቱ የተዘበራረቀና የፈራረሰ እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ እውነት ነው......ስጋዊነት የተጠናወተው ህይወት ለጨለማው አለም ጥቃት በእጅጉ ተጋልጧል.....በተቃራኒው ግን ራሱን ቀንና ለሊት ለመንፈሳዊው አለም ያሰለጠነና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያልተቋረጠ ህብረት ያለው ሰው ህይወት በውሃ ፈሳሾች ዳር እንደተተከለች ፍሬዋንም በየጊዜዋ እንደምትሰጥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል ብቻም ሳይሆን ቅዱስ ቃሉም አስረግጦ እንደሚነግረን የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል.......ስለዚህ ከምንም አስቀድመን በውስጥ ሰውነታችን መጠንከርና ለመንፈሳዊነት ራሳችንን ማስለመድ ይኖርብናል......ወደ ጠለቀ መንፈሳዊ ህይወት የምንገባበት ዘመን ይሁንልን....በኢየሱስ ስም አሜን!!

“በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥”
ኤፌሶን 3፥16-17

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
747 viewsYonatan Worku, edited  09:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 13:50:42 Merry christmas

ድንቅ ስጦታ

ኢየሱስ ሲወለድ ሄሮድስ ደነገጠ፤ ለአለም ግን ታላቅ ደስታ ሆነ!

ኢየሱስ ለምን ተወለደ:-

የትኛውም ሰው ሲወለድ አላማው ለመኖር ሲሆን ኢየሱስ የተወለደው ግን በዋነኝነት ለመሞት(መሰዋዕት ለመሆን) ነው.... ከዚህ ጋር በተያያዘ ኢየሱስ በስጋ የተገለጠበትን 3ት ዋነኛ ምክንያቶችን እናንሣ !!

1. የሰይጣንን ራስ ለመቀጥቀጥ!

“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”
ዘፍጥረት 3፥15

“ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም፥ ዘሩ በእርሱ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔርም ተወልዶአልና ኃጢአትን ሊያደርግ አይችልም።”1ኛ ዮሐንስ 3፥9

ራስ(head) ብሎ ሲል:-
        - ጥበብና ዕውቀት
        - ስልጣን
        - ሃሳብ

2. አለምን ሁሉ ከኃጢያትና ከሃጢያት እርግማን ለማዳን!

ማቴዎስ 1
¹⁸ የኢየሱስ ክርስቶስም ልደት እንዲህ ነበረ። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች።
¹⁹ እጮኛዋ ዮሴፍም ጻድቅ ሆኖ ሊገልጣት ስላልወደደ በስውር ሊተዋት አሰበ።
²⁰ እርሱ ግን ይህን ሲያስብ፥ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ታየው፥ እንዲህም አለ፦ የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፥ ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ።
²¹ ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ።

በአለም ላይ ያለ የትኛውም መድሃኒት የሚያገለግለው ለአንድ በሽታ ነው፤ የኢየሱስ መድሃኒትነት ግን ለሁሉም በሽታ ፈውስ መሆን ይችላል።
የትኛውም መድሃኒት ኤክስፓየሪ ዴት አለው(shelf life)፤  የኢየሱስ መድሃኒትነት ግን ያለግዜ እና ቦታ ገደብ ያድናል።

3.የምድር አህዛብ ሁሉ በእርሱ እንዲባረኩ!

ዘፍጥረት 22
¹⁵ የእግዚአብሔር መልአክም አብርሃምን ከሰማይ ሁለተኛ ጊዜ ጠራው፥
¹⁶ እንዲህም አለው፦ እግዚአብሔር፦ በራሴ ማልሁ ይላል፤ ይህን ነገር አድርገሃልና፥ አንድ ልጅህንም አልከለከልህምና
¹⁷ በእውነት በረከትን እባርክሃለሁ፥ ዘርህንም እንደ ሰማይ ከዋክብትና በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ አበዛዋለሁ፤ ዘርህም የጠላቶችን ደጅ ይወርሳል፤
¹⁸ የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ፥ ቃሌን ሰምተሃልና።

“ለአብርሃምና ለዘሩም የተስፋው ቃል ተነገረ። ስለ ብዙዎች እንደሚነገር፦ ለዘሮቹም አይልም፤ ስለ አንድ እንደሚነገር ግን፦ ለዘርህም ይላል፥ እርሱም ክርስቶስ። " ገላትያ 3፥16

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
982 viewsYonatan Worku, 10:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 22:39:04 ባለ ልደቱ በሌለበት ግን እኮ ልደት የለም!!
ድንቅ ስጦታ..

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በጣም ከምወዳቸው በዓላት መካከል አንዱ ነው.......መለኮት ከነበረበት የፅድቅና የቅድስና ከፍታ የተነሣ እኛ የሰው ልጆች ልንደርስበት ከቶ ስላልቻልን መለኮት ራሱን ያለ መጠን ዝቅ ዝቅ ያደረገበትና በእኛ ልክ የወረደበትን እንዲሁም ወደር የሌለውን የፍቅሩን ጥልቀት የገለጠበትን እውነት ያሳያል......ሁሉን ካለመኖር ወደመኖር ያመጣውና የነገሮች ሁሉ ምንጭ የሆነው አምላክ ከሰማይ ሰማያት የወረደበትና የሰውን ስጋና ደም የተካፈለበትን ምስጢር ይሄ ሚጢጢ አዕምሮአችን በፍፁም ሊረዳው አይቻለውም......በአጠቃላይ ከኃጢያት በቀር በነገር ሁሉ እኛን የመሰለበት ትህትናና ፍቅር እጅግ ያስገርማል፤ በሰውም የቃላት ድርደራ አይገለጥም.......በኃጢያታችን ምክንያት የሞት ፍርድ የሚገባን የቁጣ ልጆች ሆነን ሳለን እግዚአብሔር ግን ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ የዘላለም ህይወትን ሰጠን.....ሃሌሉያ.....ጌታችን በድንግል ማህፀን ውስጥ አድሮ በማይመችና በሚሸት የከብቶች በረት ውስጥ የተወለደው በኃጢያታችን ምክንያት ይሸትና ይከረፋ የነበረውን የእያንዳንዳችንን ህይወት ለማጣፈጥና ለማሳመር ነው.....ስለዚህ ይህ በዓል ትልቅ ትርጉም አለው.....አሁን አሁን ግን በበዓሉ ሰበብ ከበዓሉ ጋር የማይገናኙና አላማውን የሚያደበዝዙ አያሌ ጉዳዮች ሲደረጉ ይስተዋላል......ባለልደቱ በሌለበት ግን ልደት የሚባል ነገር በፍፁም የለም....ልክ ያለሙሽሮች ሠርግ እንደማይታሰብ እንዲሁ ልደት እንዲኖር ባለልደቱ ሊኖር ግድ ይላል......በጌታችን ልደት ከፍ ብሎ ሊደምቅና ሊታይ የሚገባው ራሱ ባለልደቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው...ሃሌሉያ.....የጌታ መወለድ አንድምታው የእያንዳንዳችን ዳግም መወለድ ስለሆነ ይህንን እውነት በመቀበልና የአብን ድንቅ ስጦታ አክብረን በመውሰድ ከዘላለም ጥፋት እናምልጥ!!

ይህንን ፅሁፍ የምታነቡ እና የአብን ድንቅ ስጦታ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስን ያልተቀበላችሁ ሁሉ ግዜው ሳያልፍባችሁ ዛሬውኑ ነፍሳችሁን ሊያድን እና ሰላምን ሊሰጣችሁ ወደሚችለው ጌታ እንድትመጡ እጋብዛችኃለሁ!! በምድርም ሆነ በሰማይ ይህንን ድንቅ ስጦታ የሚያክል አንድም ስጦታ የለም፤ ሊኖርም አይችልም.... ኢየሱስ ይወዳችኃል!!

@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.2K viewsYonatan Worku, 19:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 10:13:27
Jesus is the reason for the season!!

Merry Christmas
@ZaphnathPaaneah1
@Yoni4Christ
1.0K viewsYonatan Worku, edited  07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 22:24:14 Never doubt God's love! He is truly faithful to His Words.
The God who is willing to send His only begotten son to save a sinner, Imagine what He is willing to do to those who are called by His name!
@ZaphnathPaaneah1
@Bill4Christ
133 viewsBehailu(Bill), 19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ