Get Mystery Box with random crypto!

Yoni Arts

የቴሌግራም ቻናል አርማ yoniarts5 — Yoni Arts Y
የቴሌግራም ቻናል አርማ yoniarts5 — Yoni Arts
የሰርጥ አድራሻ: @yoniarts5
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 761
የሰርጥ መግለጫ

👉 ያነበብኳቸውን የብእር ትሩፋቶች፣ የሰማኋቸውን መረጃዎችና ያየኋቸውን እውነቶች የማቀርብበት ቻናል ነው። ቤተሰብ ይሁኑ!
You Tube Channel Subscribe Now
https://youtube.com/channel/UCekLT0ck645BHB8D6rJ5g4w

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-12 14:04:37 አዲስ አመት (2015)

እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም በጤና አደረሳችሁ! አደረሰን!
     
አዲሱ አመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የመከባበር፣ የአንድነት፣ የመረዳዳት፣ የመደማመጥ፣ የመቻቻል፣ ተማሪው በትምህርቱ፣ ሰራተኛው በስራው፣ ውጤታማ የሚሆንበት፣ እንዲሆን እንመኛለን!

       ጥላቻን በ  -
       ያለንን በ    ÷
       ይቅርታን በ   ×
       ፍቅርን በ     +

ቀንን በቀናት
ሳምንትን በሳምንታት
ወርን በወራት
ዘመንን በዘመናት
የሚለውጥ እርሱ ግን የማይለወጥ ፈጣሪ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር መልካም ዘመንን ይጨምርልን

  በአዲሱ አመት ለሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላም ሰፍኖ ፍቅር ነግሶ የወረራት የጥላቻ መንፈስ ከላይዋ ተገፉ፤ አድጋ ፤ለምልማ ትበልፅግልን!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

በየቀኑ የምንለቃቸው ጽሑፎች እንዲደርሷችሁ ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.7K viewsedited  11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 12:38:43 ቅምሻ

አዲስ ዘመን ከወቅትና ከመልክአ ምድራዊ፣ ከባህልና  ከሃይማኖት አንጻር

አዲስ ዘመን የሚከበርበት በርካታ ምክንያቶች አሉ፡፡ አንደኛ ወንዞች የሚጎሉበት፣ ገበሬው የክረምቱን ወራት አርሶ ዘርቶ አርሞ ወዘተ… የአዝመራውን አላባ የሚጠብቅበት፣ የጥጋቡ ዘመን የሚመጣበት፣ ብርሃናት ዑደታቸውን ጨርሰው አዲስ የሚጀምሩበት  ወዘተ. ሲሆን ሁኔታውን ከወቅቶችና ከመልከአምድራዊ ሁኔታ ጋር አሰናስሎ መመልከት ይቻላል፡፡

መስከረም ሲጠባ አደይ ሲፈነዳ፣
እንኳን ሰው ዘመዱን ይጠይቃል ባዳ፡፡


የሚለው ግጥም ወቅትና መልከአ ምድርን የሚመለከት ነው፡፡ በክረምት ወንዝ እስከሚጎድል /ድልድይ እንኳን ያኔ አሁንም በየጎጡ አይታሰብም/ ዘመድና ዘመድ የማይገናኝበት መሆኑን ያመላክታል፡፡

ሁለተኛው በኖኅ ዘመን ምድርን ያጥለቀለቃት የጥፋት ውሃ የደረቀበት በመሆኑ ነው፡፡ በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ መጽሐፈ ኩፋሌ ላይ በአስረኛው ወር፣ የተራሮች ራስ ታየ ይልና፤ ምድር በመጀመሪያው ወር መባቻ መታየቷን ይመሰክራል፡፡ /ኩፋሌ ምዕ 7፥1/ ከዚህ በተጨማሪ ሄሮድስ የቅዱስ ዮሐንስን ጭንቅላት ያስቆረጠበትን፤ በዚህም የቅዱሱን ሰማዕትነት ለመዘከር ነው የሚሉ ሀሳቦች ናቸው፡

በሌላ በኩል ከባህላዊ ዳራ አንጻር የምንመለከታቸው ሲሆኑ ጭፈራው፣ ምርቃቱ፣ ችቦ ማብራቱ፣ ድግሱ ወዘተ. ናቸው፡፡ ዝናቡ የምህረት፣ እህሉ የበረከት እንዲሆን፣ ሰላም እንዲወርድ ይጸለያል፡፡ “እህል ይታፈስ ገበሬ ይረስ፤ አራሽ ገበሬውን ሳቢ በሬውን ይባርክ...” እየተባለ በሽማግሌዎች ይመረቃል፡፡ ጭፈራዎቹም የባህሉ አንድ አካል ናቸው፡፡ ለአብነት ያህል የተወሰኑ ስንኞች ወስደን እንመልከት፡፡

የጎመን ምንቸት ውጣ፣
የገንፎ ምንቸት ግባ፡፡
አይዞሽ ነፍሴ ፣
ደረሰልሽ ገብሴ፡፡
አትኩራ ገብስ፣
ጎመን ባወጣው ነፍስ፡፡


ገበሬው የአመት ቀለቡ የሚሟጠጥበት፣ ለዘር ያስቀመጣትን እህሉን ለመሬት አደራ ሰጥቶ /የዘር እህል አይበላም/ ቶሎ የሚደርሱትን እነጎመንን እየተመገበ ይከርማል፡፡ መስከረም ጥቅምት ላይ በተለይ የገብስ ዘሮች ይደርሱና ገንፎም በሶም ይበላል፡፡ ስለዚህ በዘመን መለወጫ ጊዜ ጎመን ሲቀቅልበት የከረመውን ምንቸት ውጣ እያለ በአዲስ ተስፋ የገንፎ ምንቸቱን ግባ ሲልና፤ ወደዚህኛው ምግብ የሚዞርበትን ሁኔታ ሲገልጽ እንሰማለን፡፡ በሽታውን፣ ችግሩን፣ ተንከሊሱን ሁሉ በችቦ የተስፋ ብርሃን እንጎሮጎባሽ እያለ በመተርኮስ ያባርራል፡፡

እዚህ ላይ ለነፍሱ ገብስ እንደደረሰለት ያስገነዝብና ተመልሶ ገብስ በዚህ እንዳይኮራ፣ የጎመንም ውለታ እንዳይረሳ “ገብስ፤ ነፍሴን አትርፎ ለአዲስ ዘመን ያደረሰኝ ጎመን ነውና አትንቀባረር” ለማለት “አትኩራ ገብስ፣ ጎመን ባወጣው ነፍስ” ብሎ ሸንቆጥ ያደርገዋል፡፡

ችቦም ድቅድቁን ጨለማ የሚሰነጥቅ ብርሃን ስላለው፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን የመሄዳችን ትዕምርት ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል፡፡

መልካም አዲስ አመት!

Welcom 2015

በየቀኑ የምንለቃቸው ጽሑፎች እንዲደርሷችሁ ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.3K viewsedited  09:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 23:50:48 ኢትዮጵያዊነት

ኢትዮጵያዊነት ብዙ የተለያዩ ኅብረተሰቦች የተዋኅዱበት አካል ክፍል መሆን ነው። ኢትዮጵያዊነት ከጎሠኝነት በላይና ውጭ የሆነ አጠቃላይ ማንነት ነው።

ኢትዮጵያዊነት የዚች ውጥንቅጥ መሬት ባለቤትነት ነው፣ ኢትዮጵያዊነት የደጋው ብርድና የቆላው ሙቀት የሚገናኙበት፣ የደጋው ዝናብም ከቆላው ወንዝ ጋር የተዛመደበት ኃይል ነው።

ኢትዮጵያዊነት በቄጤማ ጉዝጓዝ ላይ የሚታየው መተሳሰብና መፈቃቀር ነው።

ኢትዮጵያዊነት የአስተዋይነት፣ የሚዛናዊነት የጨዋነት ባሕርይ ነው።

ኢትዮጵያዊነት ረዢምና ተጽፎ ያላለቀ ታሪክ ነው፤ ብዙ ሰዎችም የተሰዉለት ስሜት ነው።

ኢትዮጵያዊነት ስቃይና መከራ ነው፤ ኢትዮጵያዊነት ኩራትና ክብርም ነው።

ኢትዮጵያዊነት ጭቆናና ጥቃት ነው፤ ኢትዮጵያዊነት አሻፈረኝና እምቢ ባይነትም ነው።

የኢትዮጵያዊነት ዓላማ ያለችውንና የኖረችውን ኢትዮጵያን እንደገና ለመፍጠር አይደለም። የኢትዮጵያ ዓላማ ለኢትዮጵያዊያን በሙሉ የሚስማማ እድገታቸውንም የሚያፋጥንና፣ ኅብረታቸውን የሚያጠነክር ሥርዓትን መፍጠር ነው።

  የኢትዮጵያዊነት ችግር ኢትዮጵያ አይደለችም፣ ችግሩ የሥርዓት ችግር ነው። የቤቴ መቃጠል ለትኋኑ በጀኝ እንዳለው ቂል እንዳንሆን።

  ኢትዮጵያዊነትን መካድ የራስን ማንነት መካድ ብቻ አይደለም። አባቶችንና እናቶችን፣ ቅድም አያቶችን ከነቅርሳቸው መካድ ነው። በእንደዚህ ዓይነቱ ክህደት ላይ የተመሰረተ ማንነት የት ይደርሳል? ከበሽታ በቀርስ ትርፉ ምን ይሆናል? ክህደት ራሱን የቻለ በሽታ ሲሆን ማስካድ ደግሞ የባሰ ነው። ክዶ ማስካድ ታምሜያለሁኝ፣ ታመሙ እንደማለት ነው።

አስታማሚ እንኳን እንዳይገኝ የማድረጉ ጥረት የበሽታውን ምልዓትና ጽናት ያመለክታል።

ሆኖም የኢትዮጵያ ታሪክ ሊያስተምረን እንደሚችለው ኢትዮጵያዊነት እንደ ላስቲክ ነው። ሲስቡት ይሳባል፣ሲለቁት ይሰበሰባል። ማለት-ይሳብና ይሳሳል እንጂ አይበጠስም።

ከፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

በየቀኑ የምንለቃቸው ጽሑፎች እንዲደርሷችሁ ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.6K views20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 08:39:01 የምሥጢሩ ቁልፍ
    
  በ1900 ከክርስቶስ ልደት በፊት አሐሜኔስ የተባለ ኢትዮጵያዊ ለመጀመሪያ ጊዜ ፕላኔቶች እንዳሉ የተናገረ ሰው ነው። ይህ አሐሜኔስ የተባለው ኢትዮጵያዊ 16 ፕላኔቶች እንዳሉ የተናገረ ሲሆን፤ ፀሐይን ለመዞር ስንት ጊዜ እንደሚፈጅባቸው፤ በስንት ምህዋር እንደሚዞሩና በውስጣቸው ያሉትን ፍጥረታትን
ጽፏል።

NASA እንኳን አስካሁን እርገጠኛ የሆነው ዘጠኝ ፕላኔቶች እንዳሉ ነው ነገር ግን ገና 7 ፕላኔቶች ይቀራሉ።

አሐሜኔስ መዝገበ ሰማያትና አውደ ከዋክብት የተባለው መጽሐፍ በታወቀው ቦታ ዋልድባ የሚገኝ ሲሆን ይኸው መጽሐፍ ደግሞ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ ፈረንሳይ እና አሜሪካ ውስጥ በስርቆት ተወስዶ በምሥጢር ተቀመጦ ይገኛል።

በእነዚህ ፕላኔቶች ውስጥ ያሉ ፍጥረታትን በተለየ ቋንቋ እየሳቡ የምሥርን /የግብጽ/ ፒራሚዶችን የተሰሩ ሲሆን። የምሥር /የግብጽ/ ፓራሚዶች የተሰሩት በሰው ልጆች ሳይሆን ከነዚህ ፕላኔቶች በመጡት ፍጥረታት እንደሆነ መጽሐፈ ምሥጢር ዘአዶናይ ራፉኤል በተባለው መዝገብ ላይ ተጽፏል። እዛው ፒራሚዱ ውስጥ በምስጢርም ተቀርጾ ይገኛል።

እነዚህም ባለ ሥስት ማዕዘን ድንጋይ ያለስሚንቶና ያለጭቃ ሰው ሊሸከመው በማይችል በትልልቅ ድንጋይ ተነባብሮና ተደራርቦ በሚያስደነቅ ሁኔታ ታንጿል። የጥንት ስሟም ምሥር የተባለችውም ግብጽ ኢትዮጵያኖች ለመጀመሪያ ጊዜ ምሥርን ስላበቀሉባት ምሥር እየተባለች ትጠራ ነበር።

ኢትዮጵያ ውስጥም እንደ ምሥር /ግብጽ/ሀውልቶች/ ከብዙ ድንጋዮች ሳይሆን ከአንድ ወጥ ድንጋይ የተሰሩ 700 ፒራሚዶች 600 የአክሱም አይነት ሀውልቶች ከነ ቤተ-መንግስታቸው እና ብዙ የላሊበላ አይነት ሀውልቶች ይገኛሉ። ይህም አንድ ግዙፍ ከተማ ማለት ነው።

ነገር ግን እነዚህን ሀውልቶች ኢትዮጵያኖች አስቀብረዋቸዋል። እነዚህም ከተማዎች የጥንቷን ኢትዮጵያ ጥበብ ሸክፈው ይዘዋል። እነዚህን ሀውልቶች የት እንደሚገኙና በስንት ሜትር እርቀት ቆፍሮ ማውጣት እንደማቻል ዋልድባ ባለው መዝገብ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ ነገር ግን ጊዜው እስኪደርስ በምስጢር ተይዟል።

ለምሳሌ ያህል ደግሞ በቅርቡ በቁፍሮ የወጣውን የዳግማዊ ላልበላን ሀውልት ማየት ይቻላል። ዮሐንስ በራእዩ ሲከፈት ያየው ቤተ-መቅደስ እነዚሁ የላልበላን ሀውልቶች እንደሆኑ አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ ያስረዳሉ።

እንደ ምንጭነት የተጠቀሰውም የምሥጢሮች ሁሉ ቁልፍ  የሆነው መጽሐፈ ምሥጢር ዘአዶናይ ራፉኤል ሲሆን ይህም መጽሐፍ እጅግ በጣም ብዙ ምሥጢሮችን የያዘ ሲሆን መጽሐፉ ሙሉ በሙሉ ቢተረጎም እጅግ በጣም የሚያሥፈራና አስደንጋጭ ታይቶና ተስምቶ የማይታወቅ ከሰው ልጆች በላይ የሆነ ምሥጢር አለው፤ ሁሉም ነገር እንደ ፈጣሪ ፍቃድ በጊዜው ይሆናል። የተለየ መንፈሳዊ አይን ያለው ሰው ግን አሁንም እነዚህን የፒራሚድ ከተሞች መመልከት ይቻላል።

ምንጮቸ ፦ የሊቁ አባ ተስፍ ሥላሴ ሞገስ   you tube video

ሔኖክ ዘአዶናይ

በየቀኑ የምንለቃቸው ጽሑፎች እንዲደርሷችሁ ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.6K viewsedited  05:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 18:59:16 ከፈላስፋዎች ጉያ

ያለምጥ መልካም ነገር አይወለድም

የሰው ልጅ ለአምላኩ ያለው ጥያቄ ብዙ ነው። አንደኛው ዛሬ ዝናቡን አዝንብልን ሲለው ሌላኛው ዛሬ መንገድ አስቤያለሁና አደራህን ያን ዝናብ ያዝልን ይለዋል። ታድያ አንድ ቀን አንድ ጎበዝ ገበሬ እግዚአብሔርን ሃሳቡን እንዲህ ሲል አማከረው ፦ "ይኸውልህ ጌታዬ እኔ እድሜዬን ሙሉ የግብርና ስራ የሰራሁ ብዙ ልምድ ያለኝ የታወቅኩ ጎበዝ ገበሬ ነኝ። ብዙ ጊዜ እንደዚህ አስባለሁ ፦ አምላካችን ስንዴ ከዘራን በኋላ በተገቢው ሰዓት ዝናብ ቢያዘንብልን ሃይለኛ ንፋስ ባይነፍስ እና የስንዴ ሰብላችንን በሐይል እየነቀነቀ ባይሰባብርብን ባያስቸግርብን ፤ አንዳንዴም ውርጭና ብርዱ ሰብላችንን ባያበላሽብን በአንድ አመት የምንሰበስበው ብቻ ለሚቀጥሉት አስር ዓመታት አለስጋት ያኖረን ነበር።  ታድያ ደጉ ጌታ ሰብላችንን እስክንሰበስብ ሁሉን ነገር ምቹ ለምን አታደርግልንም " አለው

እግዚአብሔርም የገበሬውን ንግግር አዳምጦ "እሺ እንደፈለግህ ይሁን " አለው። አመቱን ሙሉ የተዘራው ስንዴ ዝናብ ሳያጣ ንፋስ ሳያስቸግር ሁሉ ነገር እንደተደላደለ ሰብሉ በምቾት አደገ። ገበሬው እንዳለው ስንዴው ረጃጅም እና በጣም ብዙ ሆኗል እርሻው ላይ የሚያጓጉና ለዓይን ያማረ ነው ። ገበሬውም ይኸው ያልኩት ደረሰ አለ ።

በመጨረሻ የመሰብሰብያው ጊዜ ደርሶ ገበሬው ሰብሉን መሰብሰብ ሲጀምር በተመለከተው ነገር ከፉኛ ደነገጠ። ስንዴው ምንም ዘር የለውም። ገበሬው ግራ ተጋባና እግዚአብሔርን ጠየቀ "እንዴት ሊሆን ቻለ ?" እግዚአብሔርም እንዲህ ሲል መለሰለት፦ "አንተ አኮ በጭራሽ ስለ ንፋስ ስለውርጭ ስለማዕበል አልጠየክም ፤ አንተ የጠየከው ምቾትን ብቻ ነው ፤ የትኛውንም ነገር ፍሬ እንዲያፈራ የሚያደርጉት ጠንክሮ ዘርን አንዲይዝ የሚያደርጉት ተግዳሮቶች ናቸው ። መከራ ነው ስሩን ጠንካራ የሚያደርገው መነቅነቅ ነው ግንዱን የሚያፀናው በምጥ ነው ያማረ ነገር ሀሉ የሚወለደው"  አለው።

ወርቅ ተፈላጊነትን ያገኘው በእሳት ተፈትሎ ነው። እናም ፈተና ህይወታችንን ያጠነክረዋል እንጂ አያላላውም ተስፋችንን ያገዝፈዋል እንጂ ህልማችንን አያጨናግፍም ስለዚህ በህይወታችን ውስጥ የሚገጥሙን ፈተናዎች ፍሬያማ ሊያደርጉን ነውና ትኩረታችንን ዓላማችን ላይ ማድረግ ያስፈልጋል።

በየቀኑ የምንለቃቸው ጽሑፎች እንዲደርሷችሁ ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.5K viewsedited  15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:30:57 ከብራና ገጾች

የBlack Hole ምሥጢር

በምእራባውያኑ የሥነህዋ የምርምር ተቋማት black hole በመባል ስለሚጠሩት ምሥጢራዊ ቦታዎች NASAን ጨምሮ የተለያዩ የፊዚክስ ምሁራን የራሳቸውን መላ ምት በመዘርዘር የቦታውን ምሥጢራት ለመፍታት የሞከሩ ሲሆን አልበርት አንስታይን በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡

በዚህ ጽሑፍ ላይ የምእራባውያኑን ምሁራን ንድፈ ሃሳብ ከማየታችን በፊት በቀጥታ ቀደምት ኢትዮጵያውያን አባቶች እና የጽሑፍ ዶክመንቶች ስለነዚህ ምስጢራዊ ቦታዎች የተናገሩትን የተለያዩ እውቀቶች በአንድ በማጣመር ለማየት እንሞክራለን፡፡ አንባብያን ይህን የኛን ንድፈ ሃሳብ ከእምራባውያኑ ጋር በማገናኘት እና በማነጻጸር አንድ ነጥብ ላይ ለመድረስ መንደርደሪያ እንደሚሆናችሁ እናምናለን፡፡

ቀደምት ኢትዮጵያውያን አባቶች እንደሚያስተምሩት አለማት አራት ሲሆኑ የእሳት የምድር የንፋስ እና የውሃ ዓለማት ይባላሉ፡፡ የእሳት ዓለማት የሚሰኙት ዘጠኝ ዓለማት ሲሆኑ የምድር ዓለማት የሚባሉት ደግሞ አምስት ዓለማት ናቸው፡፡ በነዚህ ሁለት ዓለማት ውስጥ በሚገኙት አስራ አራት ዓለማት ውስጥ የተለያዩ ፍጥረታት ይኖራሉ፡፡ እነዚህ የአስራ አራት ዓለማት ፍጥረታት ማለትም የእሳት ዓለማት የሆኑት ዘጠኝ ዓለማት እና አምስቱ ምድራዊ ዓለማት ውስጥ የሚገኙት ፍጥረታት አንዳቸው ከአንዳቸው ግንኙነት የሚፈጥሩባቸው አስራ ሁለት የተለያዩ ቦታዎች አሉ።

ምእራባውያኑ የስነህዋ ምሁራን black hole ብለው የሚጠሯቸው ከነዚህ አስራ ሁለት ቦታዎች ስድስቱን ቦታዎች ነው። ይህን ከማብራራቴ በፊት ስለ አስራ አራቱ ዓለማት ፍጥረታት እና ስለ ዓለማቱ ባህርያት ማብራራት ተገቢ ነውና በቀጥታ ወደዛ አመራለሁ፡፡ የእሳት ዓለማት የሚባሉት ጽርሃ አርያም ( ኢትዮጵያ እና ቤተክርስትያን የጽርሃ አርያም ተምሳሌት ናቸው) (መንበረ መንግስት) (ሰማየ ውድውድ)( ኢየሩሳሌም ሰማያዊት) (ኢዮር) (ራማ) (ኤረር) ምጽናተ ሰማይ( ባህረ እሳት) (ገሀነመ እሳት) ናቸው፡፡ በዓለመ እሳት ከሚገኙት ሰማያት ሶስቱ ቅዱሳን መላእክት የሚኖሩባቸው የመላእክት ከተሞች ሲሆኑ ኢዮር ራማ ኤረር ይባላሉ፡፡ ኢዮር በተሰኘው የመላእክት ከተማ አራት የመላእክት ነገዶች ይኖራሉ፡፡ እነርሱም አጋእዝት ኪሩቤል ሱራፌል እና ኃይላት ይሰኛሉ፡፡ የአጋእዝት ነገድ አለቃ ሳጥናኤል ይባላል እንዲሁ የኪሩቤል አለቃ ገጸ ሰብ እና ገጸ አንበሳ ሲሆን የሱራፌል ነገደ መላእክት ገጸ ንስር ሲሆን በስተመጨረሻም የኃይላት ነገደ መላእክት አለቃ መልእኩ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ በራማ በሚገኘውም የማላእክት ከተማ ሶስት ነገደ መላእክቶች ይኖራሉ የነገዳቸውም ስም መናብርት አርባብ እና ሥልጣናት ይባላሉ፡፡ የመናብርት አለቃ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ሲሆን የአርባብ ነገደ መላእክት አለቃም እንዲሁ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ነው በመጨረሻ የሚገኘው የስልጣናት ነገደ መላእክት አለቃ መላእኩ ቅዱስ ሱርያል ነው። በሶስተኛው የመላእክት ከተማ ኤረር ሶስተ ነገደ መላእክት ይገኛሉ የነገድ ስማቸው መኳንንት ሊቃናት እና መላእክት ይሰኛሉ፡፡ የመኳንንት አለቃ መልአኩ ቅዱስ ሰዳካኤል ሲሆን የሊቃናት መልአኩ ቅዱስ ሰላትኤል በስተመጨረሻም የመላእክት ደግሞ መልአኩ ቅዱስ አናንያኤል ነው፡፡  ምድራዊ ሰማያት የሚባሉት ገነት ብሔረ ሕያዋን ብሔረ ብጽአን መሬት እና ሲኦል ሲሆኑ ሰማያት እኛ የምንኖርባት ምድር ከመሃል የምትገኝ ሲሆን ገነት በምስራቅ በኩል ብሔረ ሕያዋን በሰሜን ብሔረ ብጹዓን በስተደቡብ ይገኛል ሲኦል በምእራብ በኩል ይገኛል፡፡

ከላይ የጠቀስናቸው አስራሁለት ቦታዎች በእሳት ዓለማት ውስጥ የሚገኙት ሰማያዊ ሃይላትና በምድራዊ ሰማያት እና በንፋስ ዓለማት ውስጥ በሚገኙ የሰዎች ፍጥረታት እና የስማዝያ እና የሳጥናኤል ጭፍሮች ግንኙነት የሚፈጠርባቸው ምስጢራዊ መንፈሳዊ ቦታዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ቦታዎች ለሁለት የሚከፈሉ ሲሆን የመጀመርያው ስድስቱ ቦታዎች ክፉ መናፍስት ከአንደኛው ዓለም ወደሌላኛው ዓለም ግንኙነት የሚፈጥሩባቸው እና የሃይላቸው ማረፊያ የሆኑ ቦታዎች ሲሆኑ እንደ ምእራባውያኑ አገላለጽ black hole የሚባሉት ቦታዎች ናቸው፡፡ የተቀሩት ስድስቱ ደግሞ ቅዱሳን የሆኑ ሰማያዊ ኃይላት ለመልእክት እና ለአገልግሎት የሚወጡባቸውና የሚወርዱባቸው ብሎም ማደሪያቸው የሆኑ ቅዱሳን ቦታዎች ናቸው ስለዚህ ለመረዳት እንዲያመቸን በነጮቹ አገባብ እኛ እነዚህ ቦታዎች WHITE HOLE ብለን ልንሰይማቸው እንችላልን፡፡

በዚህ black hole ምስጢራት ላይ ለሚደረገው ጥናት ለምእራባውያኑ ፍንጭ የሰጠው Einstein's general relativity (GR) ንድፈ ሃሳብ ቢሆንም ከአልበርት አንስታይን ንድፈ ሃሳብ በተሻለ ግን ስለቦታዎቹ ማብራራት የሚቻለው መጽሐፈ ራዚኤል ወይም ህይወት መጽሐፍ ብለን የምንጠራው መጽሐፍ ሲሆን ይህ መጽሐፍ በአራቱ ሰማያት መካከል ያለውን የኃይል የጊዜ እና የግዝፈት ልዩነት ያስረዳል፡፡ ይም መጽሐፍ አዳም የጻፈው መጽሐፍ ሲሆን አዳም የእሳት ዓለማት ውስጥ የሚገኙት ቅዱሳን መላእክት ያስተማሩትን ጥበብ ያሰፈረበት ነው፡፡  አዳም እኛ በምንኖርባት ምድር እና በገነት መካከል ያለውን የኃይል የጊዜ እና የግዝፈት ልዩነት ውጭ ሆኖ በሁለቱም ዓለማት ላይ መኖር የቻለው መላእክቱ ባስተማሩት ጥበብ፡፡ ይህም አዳም ገነት በኖረበት ሰባት ዓመት እና በምድር 2555000 ሚሊየን ዓመት መካከል ያለውን የኃይል የግዝፈት እና የጊዜ ልዩነት አስማምቶ መኖር ችሏል፡፡ በዛም መሰረት አዳም ወደ ምድር ሲመጣ ሰባት አመት እንዳሳለፈ ሰው እንጂ በምድራዊ የጊዜ አቆጣጠር 2555000 ሚሊየን ዓመት እንዳሳለፈ ሰው ሆኖ አይደለም ወደ ምድር የመጣው፡፡

እንደ ኢትዮጵያውያን አባቶች አስተምህሮት ከላይ በሁለት ምድብ በከፈልናቸው black hole(የክፉ መናፍስት የኃይል ማደርያ) እና WHITE HOLE( የእሳት ዓለማት ውስጥ የሚገኙት የቅዱሳን መላእክት ማደርያ) የሆኑት እነዚህ ቦታዎች በአራቱ ዓለማት ውስጥ ከሚገኙት የኃይል የጊዜ እና የግዝፈት ልዩነት ውጭ ናቸው፡፡ በዚህ የተነሳም እነዚህ ቦታዎች ከመሬት ስበት ሕግ ውጭ የሚሆኑበት እድላቸው ሰፊ ነው፡፡

የእሳት ዓለም ፍጡራን የሆኑት ቅዱሳን መላእክት ከሰው ልጆች ጋር ግኑኙነት የሚፈጥሩባቸው እና የኃይላቸው ማደርያ የሆኑት ስድስት ቦታዎች በምድር እና በእሳት ዓለም ብሎም በብሔረ ሕያዋን ሰማያት መካከል ካለው የኃይል የጊዜ እና የግዝፈት ልዩነት ውጭ ሲሆኑ እነዚህ ቦታዎች ለተቀደሰ መንፈሳዊ ስራ የሚተጉባቸው ቦታዎች (WHITE HOLE) ናቸው፡፡ ከዚህ በተቃራኒው ስድስቱ የክፋት ቦታዎች ከጊዜ ከኃይል እና ከግዝፈት ውጭ የሆኑት ቦታዎች ክፉ መናፍስት የሆኑት የስማዝያ እና የሳጥናኤል ጭፍሮች አንዳቸው ከአንዳቸው ብሎም የክፉ ስራቸው አባሪ ከሆኑ የሰው ልጆች ጋር ግንኙነት የሚፈጥሩባቸውና የክፋት የመንፈስ ስራ የሚሰሩባቸው ( black hole) ቦታዎች ናቸው፡፡

በየቀኑ የምንለቃቸው ጽሑፎች እንዲደርሷችሁ ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.6K viewsedited  15:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:43:24 አይሁድና አእምሮው

ከመላው ዓለም ሕዝብ ረገድ አይሁድ የዓለምን 0.2 በመቶ ብቻ የሕዝብ ድርሻ አለው፡፡ በእውነቱ እጅግ አነስተኛ ቍጥር ነው። ይኹን እንጂ ከ1901 እስከ 2020 ዓ/ም ባሉት 119 ዓመታት ውስጥ 900 የሚያኽሉ ሰዎች የኖቤል ሽልማትን አሸናፊነት ሲቀዳጁ ከእነዚያ ተሸላሚዎች ውስጥ 204 የሚኾኑቱ አይሁድ ናቸው፡፡ እንግዲህ ከሕዝባቸው አነስተኛ ርቢ አንጻር ለዚህች ዓለም ያበረከቱት አስተዋፅኦ ሲታሰብ (ሲብሰለሰል) ከሚጠበቀው በላይና በእጅጉ የላቀ ነው ያሠኛል፡፡

በሰላም 9 ፥ በኬሚስትሪ 36 ፥ በኢኮኖሚክስ 33 ፣ በሥነ ጽሑፍ 15 ፥ በፊዚክስ 55 ፣ በሥነ ሕይወትና በሕክምና 56 ፤ በጥቅሉ 204 አይሁድ በየዘርፉ የኖቤልን ሽልማት አሸንፈዋል፡፡ ለምሳሌ ያኽል በአያሌው የሚታወቁቱ፡— አልበርት አንስታይን (ፊዚክስት) ፥ ኔልስ ቦህር (ፊዚክስት) ፥ ሲግመን ፍሬድ (ሳይካትሪስት) ፣ ፍሪትዝ ሐበር (ኬሚስት) ፣ ሮሳሊንድ ፍራንክሊን (ባዮሎጂስት) እንዲሁ በሰላም ዘርፍ ያሸነፉት የእሥራኤሉ ጠ/ሚር ሚናሒም ቤጊንና ሺምዖን ፔሬትዝ የሚጠቀሱት ናቸው።

የአይሁድ ሳይንስ አዋቂያን ጭንቅላታቸውን (ጭንቅ—አልላት) በአግባቡ አውጠንጥነው በዓለም ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ በመፍጠር በተለይም ደግሞ የኹሉ በኾነው በሳይንሱ መስክ ላይ ያበቀሉት ሳይንሳዊ ዘር ፥ የሰው ልጅ የሚኖርባት ዓለም ረቂቅ ጥበብን እንድትጐናጸፍና የኋላ ቀር ኑሮ ቅዝቃዜ ዐጥንቷን እንዳይቈረጥመው አድርገዋል። በአንጐላቸው አብላልተው ካመጠቋቸው አይጠገቤ ሳይንሳዊ ዕውቀቶችም የተነሣ ሳይንስን ለአፍታ ሳይምሩ እንደ ኳስ አንዴ ወዲህ ፥ አንዴ ወዲያ እያንከባለሉ ምስጢሩን ኹሉ አዘርግፈውታል ቢባል የሚጋነን አይኾንም !

የአዳም ልጅ ኹሉ የአውሬ ባሕርይ በተላመደበት በክፉው ዘመን ዐይናችኹን አልያችኹ የተባሉት አይሁድ ኑሯቸው የኢትዮጵያ አበው (አባቶች) እንደሚተርቱት ያለ ኾኖባቸው ነበር። አበው ኢትዮጵያውያን ሲተርቱ “ብዕር ዘኢተፈጸመ ዐጸባሁ ወእምድኅረ ዘሞተ ይጠፈር ቍርበቱ ለከበሮ” ይላሉ። “መከራው ያላለቀለት በሬ ከሞተም በኋላ ቆዳው ለከበሮ ይጠፈራል” ማለታቸው ነው። ምንም እንኳ የዓለም ልጆች ኹሉ በየአጽናፉ ‘አክ ፥ እንትፍ’ ቢሏቸው የአእምሯቸው ውጤት የኾነውን ብስል ፍሬ አላምጠው ወደ ከርሣቸው ለመዶል ግን አሻፈረኝ ማለት አልቻሉም ! እጅጉን ይጣፍጣልና።

እንሆ በዓለም ብረት (ብሌን) ሲታዩ እንደ ሕዋስ እጅጉን ንኡሳን የኾኑ እኚህ ምስኪናን አይሁድ አስደማሚ ግብር የገበሩ የዕውቀት አለቃ በመኾናቸው እንደ አገር ፈርጣማና ጕልበታም ኾነው እንዲታዩ አብቅቷቸዋል።

ምንጭ:- መጽሐፈ ገጽ (ፕኒኤል)

በየቀኑ የምንለቃቸው ጽሑፎች እንዲደርሷችሁ ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.5K viewsedited  15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 20:13:55 አልበርት አንስታይን እና ስራዎቹ

ተጽእኖ ፈጣሪው አልበርት አንስታይን በማርች 14 በ1879 አ.ም ከአይሁዳዊ ቤተሰብ ነበር የተወለደው። አልበርት አንስታይን ከፈጠራቸው ፈጠራዎች መካከል ዋናዎቹ E=mc2, Relative theory, እና Gravity wave ናቸው። በልጅነቱ ደካማ የነበረው አልበርት አንስታይን በአእምሮው ጉብዝና ነበረበት። ይህ አልበርት አንስታይን የ2ኛ ደረጃ ትምክህቱን ባያጠናቅቅም በኤሌትሪክ ምህንድስና ትምህርት በዲግሪ ለመመረቅ ማመልከቻ አስገባ። ምንም እንኳን የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን ባያጠናቅቅም ካለጸ መማር እንደሚችል የተገለፀለት። በውጤቱም በሒሳብ እና በፊዚክስ ውጤቱ አሪፍ የነበረ ቢሆንም በሌላው ትምህርት ዝቅተኛ በመሆኑ ማለፍ አልቻለም ነበር። ለማለፍም ብቸኛ አማራጭ የነበረው እንደገና የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን ማጠናሸቀቅ ነበር። በትምርትቤቱም ታይቶ በማይታወቅ ነጥብ ነበር ያለፈው። (ለዚህም ነው 'ከትላንት ተማር, ዛሬን ኑረው, ነገን ተስፋ አድርግ, ግን ከዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ መጠየቅህን አታቁም')

E=mc2 የሚለው ቀመር ሰው ሁሉ ያውቃል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህ ያልተወሳሰበ የሚመስለው ይህ ቀመር የአልበርት አንስታይንን አስገራሚ ጭንቅላት ያሳያል። ይህ ፎርሙላ በአጭሩ በአንድ ነገር ውስጥ ያለ የታመቀ ኃይል (energy) መጠኑ የነገሩ ክብደት (mass) ሲባዛ ከብርሀን ፍጥነት እርስ በርሱ ሲባዛ (the speed of light squared) ማለትም Energy= mass (M) × Speed of light (C) × Speed of light (C). ክብደትን ወደ ሀይል ወይንም ሀይልን ወደ ክብደትን በመቀየር ነው። ይህንን ቀመር አልበርት አንስታይን ለአለም ቢያስተዋውቅም በዚህ ቀመር ተጠቅመው የኒውክለር ኃይልን ለአለም ያስተዋወቁት ሁለት ጀርመናዊ ሳይንትስቶች ናቸው።

ይህም በሌላ አገላለፅ አንድ ቁስ በብርሀን ፍጥነት መጓዝ ቢችል የቁሱ ክብደት በዚያው መጠን ይጨምራል። ስለዚህም አንድን ነገር (the speed of light squared) ማስኬድ ብንችል እቃው ግዙፍ ይሆናል ማለት ነው። ይህንን ስንል ሌላ ክብደት ይጨምርለታል ማለት አይደለም። apparent mass እና በጉዞ ላይ ያለው ክብደት (relativistic mass ) ስለሚለያይ ነው።

የብርሀን ፍጥነት በላይ መጓዝ ማለት ሽጉጥን ሳንተኩስ እንደ መተኮስ ማለት ነው። ማለትም የብርሀን ፍጥነት በሰኮንድ 300ሺ ኪ.ሜ ይጓዛል ማለት ነው። ይህንን ስንል ስለ እምነት ነው የምናወራው። በፊዚክስ ህግ ፀጉራችንን በሚሊየኖች እጥፍ ቢቆራረጥ ያቺ አንዷ ፀጉር (matter) ተብሎ ነው የሚጠራው። ልክ እንደ ዚች matter ካልሆነ በቀር በብረሀን ፍጥነት መጓዝ አይችልም።

ይቀጥላል ...

በየቀኑ የምንለቃቸው ጽሑፎች እንዲደርሷችሁ ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.0K viewsedited  17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 06:34:42 ከብራና ገጾች

መጽሐፈ አክሲማሮስ እና አልበርት አንስታይን

የአልበርት አንስታይን (E=mc^2) ቀመር በኢትዮጵያን መጻሕፍት ላይ ተገኘ!!!

አልበርት አንስታይን ሁለት ቲዎሪዎችን አስቀምጧል። አንደኛው general relativity እና spiale relativity ሲሆኑ አጠቃላይ ሀሳቡ በብርሀን ፍጥነት በምንኖርበት ሁኔታ ላይ የጊዜ ልዩነት እንደሚኖር ያስረዳበት ነው። ይህ ቲዎሪ አልበርት 1905 እ.አ ነበር ያገኝው ነገር ግን የኛ አባቶች በአራተኛው ክፍለ ዘመን ከአልበርት 1600 አመታት በፊት ነበር በመጽሐፈ አክሲማሮስ ላይ እንዲህ በማለት አባቶቻችን የጻፉት"

በላይ ሰማይ ሳይ መላእክት ሲሰግዱ አየሁ እነሱ አንድ ሰዓት ሰገዱ በምድር ደግሞ 83 አመት አለፈ " ብርሀን ባለበት ቦታ ጊዜ ይፈዛል ማለት ብርሀን ያለበት ቦታና ብርሀን የሌለበት ቦታ ሰዓት የተለያየ ነው። እንዲሁም speed (ፍጥነቱ) ይለያያል። አንስታይ "time dilution and speed" የሚለው ይህን ነው።

black hole ምሥጢራት ላይ ለሚደረገው ጥናት ለምእራባውያኑ ፍንጭ የሰጠው Einstein's general relativity (GR) ንድፈ ሃሳብ ቢሆንም ከአልበርት አንስታይን ንድፈ ሃሳብ በተሻለ ግን ስለቦታዎቹ ማብራራት የሚቻለው መጽሐፈ ራዚኤል ወይም የሕይወት መጽሐፍ ተብሎ በሚጠራው መጽሐፍ ሲሆን ይህ መጽሐፍ በአራቱ ሰማያት መካከል ያለውን የኃይል የጊዜ እና የግዝፈት ልዩነት ያስረዳል፡፡

የዚህችን ዓለም ምሥጢራትና ጥበባት እና በውስጧ ያሉትን የተለያዩ ስውር ሀብታት 12ቱን ወር ሦስት ሦስት ወር በመከፋፈል የሚጠብቁ መላእክት አሉ፡፡ የነገድ አለቃቸው ራዚኤል የተባለ መልአክ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አናንኤል ይባላል፡፡

ታዲያ አዳም በድሎ ወደ ምድር ሲመጣ ይህ መልአክ አዳም የምድርን ምሥጢራትና ጥበባት ይጠቀም ዘንድ በዚች ምድር ላይ ስለሚገኙት ምሥጢራትና ጥበባት በመጽሐፍ አዘጋጅቶ ቢሰጠውም ፈቃደ እግዚአብሔርን ባለመጠየቁ ሌሎች መላእክት ይህን መጽሐፍ ከአዳም ተቀብለው ወደ ምድር ይወረውሩታል። በቀጥታም ይህ መጽሐፍ ግዮን የተባለ ወንዝ ውስጥ ይወድቃል። ይህ ግዮን የተባለው ወንዝ የኛው አባይ ነው፡፡ ከወደቀ በኋላ መልአኩ ራዚኤል ከእግዚአብሔር ይቅርታን በማግኘቱ ይህን መጽሐፍ አዳም ተመልሶ ሊያገኘው ችሏል፡፡

መረጃዎች እንደሚያስረዱት ይህን መጽሐፍ ከአዳም ቀጥሎ ኖህ ከኖህ ሔኖክ ከሔኖክ ደግሞ ጠቢቡ ሰሎሞን እጅ የደረሰ ይህም መጽሐፍ በመላኩ አማካኝ ተጽፎ ለአዳም የተሰጠ መጽሐፍ ሲሆን አዳም የእሳት ዓለማት ውስጥ የሚገኙት ቅዱሳን መላእክት ያስተማሩትን ጥበብ ያሰፈረበት ነው፡፡

አዳም እኛ በምንኖርባት ምድር እና በገነት መካከል ያለውን የኃይል የጊዜ እና የግዝፈት ልዩነት ውጭ ሆኖ በሁለቱም ዓለማት ላይ መኖር የቻለው መላእክቱ ባስተማሩት ጥበብ ይህም አዳም ገነት በኖረበት ሰባት ዓመት እና በምድር 2555000 ሚሊዮን ዓመት መካከል ያለውን የኃይል የግዝፈት እና የጊዜ ልዩነት አስማምቶ መኖር ችሏል፡፡

በዚህም መሰረት አዳም ወደ ምድር ሲመጣ ሰባት አመት እንዳሳለፈ ሰው እንጂ በምድራዊ የጊዜ አቆጣጠር 2555000 ሚሊዮን ዓመት እንዳሳለፈ ሰው ሆኖ አይደለም ወደ ምድር የመጣው፡፡

ለዚህ ቻናል አዲስ የሆናችሁ Join በማድረግ ተቀላቀሉን።

ምንጭ:- ፩ መጽሐፈ አክሲማሮስ

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
1.9K views03:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 21:08:32 የብእር ትሩፋት

ምርኮኛ አለቃ እንጅ ፀባይ አይቀይርም?

አሌክስ አብርሃም እንደፃፈው

ዛሬ ላይ በተለይ የሬዲዮ ፋና ጋዜጠኞች ስለህወሀትና ብልፅግና ሲዘግቡ ትዝ የሚለኝ ደራሲ ተስፋየ ገብረዓብ ነው!ነፍስ ይማር! እንጀራ ሁኖበት ጦር ሜዳ ወርዶ ለደርግ ፕሮፖጋንዳ ሲሰራ "አገር ገንጣዩ ፣ በአረብ ፔትሮል ገንዘብ የጠገበው አገር ሻጩ ወያኔ ሰላማዊ ዜጎችን በጭካኔ በመጨፍጨፍ ..." እያለ ! ወዲያው ተማረከ ! ተማረከና በዛ በኩል ሁኖ ለህወሀት ፕሮፖጋንዳ መስራት ጀመረ! ምን እያለ? " ፋሽቱ ፣ ሰው በላው ደርግ የኢትዮጵያ ጠላት ከሆኑ አገራት በሚያገኘው የመሳሪያ እርዳታ ሰላማዊ ዜጎችን በመጨፍጨፍ... " ሁለቱም ውሸት ነበር ይለናል በኋለኛው ዘመኑ በፃፋቸው ድርሳናት

እና ፈገግ የሚያደርገው ...በደርግም በህወሀትም በኩል የነበሩት የተስፋየ አለቆች ሁለቱም ስማቸው አበበ ነበር ..(ጀኔራል አበበ ኃይለሥላሴ እና ጄኔራል አበበ ተክለሃይማኖት) በአበበዎች መሀል ስንት ሚስኪን በሶ አለቀ!

@yoniarts5
@yoniarts5
@yoniarts5
764 viewsedited  18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ