Get Mystery Box with random crypto!

የኛ ሳይኮሎጂ||🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ yegna_psychology — የኛ ሳይኮሎጂ||🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ yegna_psychology — የኛ ሳይኮሎጂ||🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @yegna_psychology
ምድቦች: የልጅ እንክብካቤ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 17.15K
የሰርጥ መግለጫ

የተለያዩ አስተማሪ እና አዝናኝ አስተሳሰባችንን የሚያሳድጉ የሳይኮሎጂ እና የፓለቲካ ፅሁፎች ይቀርቡበታል።
የኛ ሳይኮሎጂ ይተነተናል እንዲሁም ታዋቂ የሥነ-ልቦና ሊሂቃን (theory) ይዳሰሳል።
🌟ማሳሰብያ ለውድ ተከተዮቻችን:➪አባላትን ለማብዛት በምናደርገው #የማስታወቂያ ልውውጦች እንዳትሰላቹብን ለማለት እንወዳለን።

[ ራሳችንን በመቀየር ድርሻችንን እንወጣ! ]

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-06 20:04:16
ለእቤቶ በምን ማሳመር አሳሰቦታል እንጊዲያው ወደኛ ይምጡ!!!
እኛጋ አሪፍ አሪፍ የስፖንጅ ድጋፎች በተመጣጣኝ ዋጋ አሰሩ
በሜትር ከ 2800 ጀምሮ እስከ 4000 ብር ያገኛሉ
አሁኑ ይዘዙን ።
በእነዚህ +251922764176 ይደውሉ ።

+251922764176
+251922764176
+251922764176
አድራሻ; - አዲስ አበባ መርካቶ እንገኛለን

https://t.me/mejilse
https://t.me/mejilse
https://t.me/mejilse
8.3K viewsAbuki, 17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 15:18:49 እውቀት ያለ ተግባር ብክነት ነው ተግባር ያለ እውቀት ሞኝነት ነው።
     Ali Ghazali
6.5K viewsABDU, edited  12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 08:38:14 ለሰው ምን ያህል መሬት ይበቃዋል?
(በሌቭ ቶልስቶይ)


ከረዥም ዘመን በፊት በአንድ ትንሽ የደቡብ ኤዥያ አገር የሚኖሩ ብልህ ንጉሥ ነበሩ። ግዛታቸውን ለመገንጠል የተነሳ አንድ የውስጥ ወንበዴ ቡድን አስቸግሯቸው ስለነበር በጦርነት ሊያጠፏቸው ወሰኑ፤
ለጦር አዛዡም ይህን ጦርነት በድል ፈፅሞ ከተመለሰ ከፍተኛ የሆነ ሀብትና መሬት እንደሚሰጡት ቃል ገቡለት። በዚህም የተነሳ የንጉሡ ጦር በከፍተኛ ቆራጥነት ተዋግቶ የወንበዴው ጦር ተደመሰሰ። የሞተው ሞቶ የቀረው ቆስሎም ተማረከ፤
ንጉሡ ቃል እንደገቡት ለጦር አዛዡ ብዙ ሀብት ከመደቡለት በኋላ "በእግሩ ቀኑን ሙሉ ፀሀይ እስክትጠልቅ የሄደበትን የግዛቴን መሬት ለክታችሁ ስጡት።" ብለው ሸለሙት።

የጦር አዛዡም ተደሰተ፤ ብዙ ለም የሆነ መሬት መያዝ ይፈልግ ስለነበር በተዘጋጀበት ቀን በጣም በማለዳ ተነስቶ ስንቅ አዘጋጅቶ መጓዝ ጀመረ። በመጀመሪያ ጉልበቱ የቻለውን ያህል በለሙ መሬት ላይ ሮጠ። መሬት ለኪዎችም በፈረስ ይከተሉት ነበር፤
ከዚያም በፍጥነት ቀኑ ሳይመሽ ይራመድ ጀመር። ብዙ ከሄደ በኋላ ወደ ከሰአት ምሳውን ሳይቀር እየሄደ በላ።

ሆኖም ከበላ በኋላ ጥቂት መሬት ሄዶ ስለደከመው እየተራመደ ውሃ ጠጣ። ዘጠኝ ሰአት ያለእረፍት ተጉዞ በመጨረሻ እገሩ በጣም ዛለ፤
ቢሆንም አንድም እርምጃ ቢሆን ለም መሬት ነውና መራመዱን ቀጠለ። ሲል ሲል እግሩ መራመድ አቅቶት ዝሎ ወደቀ።
አሁን ለኪዎቹ ምልክት ሊያደርጉ ሲሉ "ቆዩ ... ቆዩ" ብሎ መዳኽ ጀመረ። ከዚያም ጥቂት ሄዶ በልቡም መሳብ ጀመረ፤
በመጨረሻ ፀሃይ ገና ሳትጠልቅ የቻለውን ተንጠራርቶ ሲሳብ ልቡ ቀጥ አለችና ትንፋሹ ቆሞ ሞተ። የንጉሡ ቦታ ለኪዎችም ደነገጡ።

የጦር አዛዡን ከሞተበት ሳያነሱ በፈረስ መልእክተኛ ወደ ንጉሡ ቤተ መንግሥት ላኩ፤
መልክተኞቹም የአዛዡን ሲጓዝ ውሎ ልቡ ደክሞ መሞቱን ነግረው "ምን ያህል መሬት እንስጠው?" ብለው ጠየቁ። ንጉሡም እጅግ አዝነው "ለሰው ምን ያህል መሬት ይበቃዋል?" ብለው ተከዙ፤
"እንግዲህ ይህ ሰው የወደቀበትን ቦታ ብቻ ከእግሩ ጫፍ እስከ ራሱ ጫፍ ብቻ ለክታችሁ ስጡት። ሬሳውንም እዚያው ቦታ ቆፍራችሁ በክብር ቅበሩትና የጀግና ሃውልት አቁሙለት።" አሏቸው፤
በተባለው መሰረት የጦር አዛዡ በመጨረሻ በሞተባት ቦታ በክብር ተቀበረ። በመቃብሩም ሀውልት ላይ

"ለሰው የሚበቃው መሬት ይህ ነው።" ተብሎ ተፃፈ።

ከንባብ ዳርቻ ለህይወት ጠኣም
#share and join for more
@KenibabDaricha
@KenibabDaricha
7.3K views€£phâ (SânTos), 05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-03 15:40:29 የመስጠት ትርጉም

የአለማችን ቀዳሚ ባለጠጋ በአንድ ኢንተርቪው እንዲህ ተጠየቀ ከአንተ የሚበልጥ ባለጠጋ ማን ነው ?
ከአንተ የሚበልጥህ ባለጠጋ አለ ?

‹‹አዎ የሚበልጠኝ ሰው አለ፡፡ የሚበልጠኝ አንድ ሰው ብቻ ነው፡፡ ከብዙ ዓመት በፊት ወደ ኒውዮርክ መሄድ ነበረብኝ፡፡ ወደ ኒውዮርክ ለመሄድ አየር መንገድ ላይ ሳለሁ የተለያዩ ጋዜጦችን የጋዜጣ አዟሪዎች እጅ ላይ አየሁ፡፡ ካየኋቸው ጋዜጦች መካከል አንዱን ወደድኩት ለመግዛት አስቤ ኪሴ ስገባ ዝርዝር ስላጣሁ ሳልገዛው መልሼ ተውኩት፡፡

በድንገትም አንድ ጥቁር ጋዜጣ አዟሪ ልጅ መጣና ጋዜጣውን ሰጠኝ፡፡ ዝርዝር የለኝም አልወስደውም አልኩት እርሱም ችግር የለውም በነጻ ውሰደው አለኝና በነጻ ሰጠኝ፡፡

ከሦስት ወር በኋላ ተመልሼ በዚያው አየር መንገድ ማለፍ ነበረብኝና በዚያ አየር መንገድ ሳልፍ አሁንም አጋጣሚ ሆነና ያንን ጋዜጣ አዟሪ ጥቁር ልጅ አገኘሁት፡፡ አሁንም በነፃ ጋዜጣ ሰጠኝ፡፡ እኔም በነፃ አልቀበልህም አልኩት እርሱም ግድየለም ከትርፌ ላይ እቀንሳለሁ ውሰድ አለኝና በነጻ ሰጠኝ፡፡

ከ19 አመትም በኋላ ባለጠጋ ከሆንኩ በኋላ ያንን ልጅ ፈልጌ ለማግኘት ወሰንኩና ፈለኩት ከአንድ ወር ተኩል ፍለጋም በኋላ አገኘሁት፡፡ ከዚያም አወቅከኝ ብዬ ጠየኩት ፡፡ አዎ አውቅሃለሁ ዝነኛው ቢልጌት አይደለህም አለኝ፡፡ ከብዙ አመት በፊት ሁለት ጊዜ ጋዜጣ በነጻ ሰጥተኸኛል፡፡ ያንን ውለታህን አካክሼ መመለስ እፈልጋለሁና የፈለከውን የትኛውንም ነገር እሰጥሃለሁ ጠይቀኝ አልኩት፡፡

ያም ጥቁር ሰው በምንም መካካሻ ልትሰጠኝ አትችልም አለኝ
እኔም ለምን አልኩት
እኔ የሰጠሁህ ደሃ በነበርኩ ጊዜ ከድህነቴ ነው፡፡ አንተ ግን ልትሰጠኝ የመጣኸው ባለጠጋ በሆንክ ጊዜ ነው፡፡ እነዚህን ሁለቱን እንዴት አካክሰህ ልትሰጠኝ ትችላለህ፡፡

ቢልጌትም ያጥቁር ወጣት በርግጥም ከእኔ የሚበልጥ ባለጠጋ ነው፡፡
ለመስጠት ባለጠጋ መሆንህን ወይም ባለጠጋ እስክትሆን ድረስ አትጠብቅ ፡፡ መስጠት የልብ ጉዳይ ነው እንጂ የአቅም ጉዳይ አይደለም፡፡

ከንባብ ዳርቻ ለህይወት ጠዓም
#SHARE & JOIN FOR MORE
@KenibabDaricha
@KenibabDaricha
7.1K views€£phâ (SânTos), 12:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-26 18:21:44 ልጆች ለማሀበረሰቡ የሚሰጡት የሰጣቸውን ነው!
      -- Marcus Aurelius --

JOIN US
https://t.me/Yegna_Psychology
https://t.me/Yegna_Psychology
https://t.me/Yegna_Psychology
9.3K viewsABDU, edited  15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-24 20:03:43
#ማስታወቅያ

የመጅሊስ ዲዛይነር
በአስደናቂ አጨራረስ
ጥንካሬ በተለያየ አይነት ዲዛይን የተሰሩ ዓረቢያን መጅሊስ፣ የፓተርን ፈርኒቸር፣ መጅሊሶች፣ በ HD የተሰሩ የስፓንጅ ድጋፎች አቅምን ባገናዘበ መልኩ እናዘጋጃለን #ከ3900 ብር ጀምሮ አሉን!!!
ትክክለኛ #ዋጋ ለማወቅ የሚፈልጉትን አይነት መጅሊስ መርጦ ፎቶ በዚህ ቦታ መልክቶን ይላኩልን ፈጣን መልስ እንሰጣለን።
@Abuki93
አሁን ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉን https://t.me/mejilse
https://t.me/mejilse
https://t.me/mejilse
9.8K viewsAbuki, edited  17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 13:41:52 እወነት

ጥያቄ፦ኦሾ ፣የምትነግረን ነገር በሙሉ እውነት ሆኖ ሳለ ስለምን ብዙኃኑ ይቃወሙሃል?

መልስ፦ትክክለኛ ምክንያት -የምናገረው እውነት መሆኑ ነው።እውነት አደገኛ ናት።

በተለይ ሐሰተኛ የሆነ ተምኔታዊ ሕይወታቸውን በተዋቡ ሕልሞች ሐሰቶች እና አስደሳች በሆኑ ሀሳባዊ ሕልሞች በመኖር ላይ ለምገኙ በሙሉ እዉነት በርግጥም አደገኛ ናት።
እነዚህን መሰል ሰዎች እውነትን በጠላትነት ይመለከቷታል።

ምክንያታቸው ደግሞ ዕድሜያቸውን በሙሉ ያመኑበትን ፣የኖሩበትን ሐሰተኛ አመለካከቶች ስለሚያፈርስባቸው ነው።
እውነት ማለት የሐሰቶች ሁሉ ሞት ናት።በተዋቡ ቃላት የተናገሩትን ሐሰቶች ጨምሮ የምትገድል ናት።
ብዙኃኑ ለምን ነበር ሶቅራጠስ ላይ የተነሡበት? ሃይማኖተኞችስ ለምን ነበር ኢየሱስን የተቃወሙት? የሁለቱም ጥፋት የብዙኃኑን እንቅልፍ እና ያማረ ሕልም መረበሻቸው ነበር።ማንም ከምቹ እንቅልፉ መቀስቀስ አይወድም።
              osho

ከንባብ ዳርቻ ለህይወት ጠኣም
#Share and join for more
@KenibabDaricha
@KenibabDaricha
10.1K views€£phâ (SânTos), 10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 18:14:18 "አንተ ከምታውቀውና ከምታምነው በላይ ሌላ ማንነት አለህና እሱን ፈልገህ አግኝ"
ሀይለጊዮርጊስ
(ጵላጦስ)

በርካታ አሳባውያን የሚስማሙበት አንድ የሰው ልጅ የማንነቱ እውነት ቢኖር የፈፀመውን ማንኛውንም ድርጊት አምኖበትና ፈቅዶ መሆኑን ከመቀበል ይልቅ እንደስህተትና ኃጢአት በመቁጠር በንስሀና ይቅርታ ራሱን ቀፍድዶ በሌሎች ፊት የመቆሙ ጉዳይ ነው:: ይኸ ብቻም አይደለም:: የሰው ልጅ መከራ ምንጩም ሆነ ምክንያቱ ይኸው ስህተት ወይም ኃጢአት በማለት የሚፀፀትበትን ድርጊት በኃላፊነት ከመሽከም ይልቅ ወደሌላው ትከሻ ማሽጋገሩ ነው:: ነገር ግን የአንተን (የሰው ልጅ) ኃጢአትም ሆነ መከራ አልያም ጭንቀት የሚሽከም (የሚወስድ) ሌላ ማንም እንደሌለ ደግሞ ብትረዳ ጭንቀትህን ለማስወገድ የመጀመሪያውን እርምጃ እንደወሰድህ ይቆጠራል::

ከአንተ ከራስህ በቀር አንተን ተክቶ ፃድቅ ወይም ቅዱስ የሚያደርግህ ሊኖር አይችልምና:: ነገር ግን በድርጊትህ ምክንያት ከሚፈጠርብህ የኃጢአተኛነት ጭንቀት ወይም የቅድስና እርካታ ይልቅ ኃላፊነቱን ራስህ ብትወስድና ሕይወትን እንደነበረች በማስቀጠል (ወደኋላ ዞረህ ሳትመለከታት) በጉዞህ ብትቀጥል ያን ጊዜ በእውቀት መንቃት ለመጀመርህ ማረጋገጫ ይሆናል:: ኃጢአትም ሆነ ቅድስና ብለህ የምትጠራውን ነገር አንተ ለብቻህ እንደፈፀምከው ካመንክ ስለምን ምህረትም ሆነ በረከትን ፍለጋ ወደሌላ ትመለከታለህ?

እዚህ ላይ የሰው ልጅ የዘወትር ሃሣቡ፣ ጭንቀቱና ፍርሃቱ በሕይወት ውስጥ በአንዳች አጋጣሚ አምኖበት ከፈፀመው ድርጊቱ የሚመነጭ ለመሆኑ የሚካድ አይደለም:: በመሆኑም ዛሬ የሚያጋጥምህን መከራ ትናንት ተሳስቼ ፈፀምኩት ከምትለው ድርጊት (በአንተ ቋንቋ 'ኃጢያት') የተነሣ እንደመጣብህ እያሰብክና ይኸው ምክንያትህ በሚያተርፍልህም ጭንቀት ሕይወትን አስቀያሚ አድርገህ በመመልከት ልትቀጥል አይገባም:: ኃላፊነትና ነጻነት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው! የሰው ልጅ ለማናቸውም ድርጊቱ ሌሎች ኃላፊነቱን ወስደው የሚቆሙለትና የሚሸከሙለት እንዳሉ በማመኑ ዘወትር የሚከተላቸውን "አዳኞቹን" (saviors) በፀፀት፣ በልመናና በንስሀ ከፊታቸው መቅረቡን ተለማምዶታል።

ከዚህም የተነሳ ፈጣሪውን ሳይሆን ፈጣሪውን ወክለው በምድር ላይ የተገለጡትን ሁሉ በመከተል የእነሱን ፈቃድና ትዕዛዝ ፈፃሚ ሆኖ በመቅረቡ አንድ ቀን በራሱ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ የፈፀመው ድርጊት "ኃጢአት" ቢኖር እንኳን ከእነሱ ምህረትና ይቅርታ ለማግኘቱ እርግጠኛ እስከሚሆን ድረስ ህይወቱን በጭንቀት መግፋቱ አይቀሬ ይሆናል:: በመሆኑም "የሰው ልጅ ይኸንና ያንን አታድርግ፤ እኔን ተከተል፤ እኔን እመን... እኔም አድንሃለሁ፤ እኔ ጠባቂህ ነኝ ወዘተ በሚለው የተስፋ ትዕዛዝና ቃላቸው የታመነባቸውን እየተከተለ የራሱን ማንነት ግን ለመጣል ይገደዳል ::

ይልቁንም ለፍቶና ደክሞ ያገኘውን ሀብት እየተመለከተ በነፃነት ከመደሰት ይልቅ ዘወትር ሀብቱን ሰጠኝ ብሎ የሚያምንበትን "አምላኩን" በፍርሀትና በጭንቀት ማመስገንን ይመርጣል:: እርግጥ ነው መከራ ከሌላ አምላክ የሚመጣ ቁጣ አድርጎ ሊቀበል የቻለ ሰው እንዲሁ የበረከት ምንጩን ሌላውን ቢያደርግ፤ በደስታውም ምትክ ጭንቀትና መከራን ቢያተርፍ የሚደንቅ አይሆንም:: ነገር ግን እዚህ ላይ የሚነሣው ጥያቄ "በመከራህም ሆነ በደስታህ የራስህን ኃላፊነት ወስደህ በነፃነት መቆም ካልቻልክ በሕይወት ውስጥ ድርሻ ምንድነው?" የሚለው ይሆናል::

ከንባብ ዳርቻ ለህይወት ጠአም!
#share and join for more
@KenibabDaricha
@KenibabDaricha
1.5K views€£phâ (SânTos), 15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 22:29:48 ኢጎ እና ደስታ

ብዙውን ጊዜ ደስታ ሠዎች የሚላበሱት ሚና እየሆነ ነው። ከሚስቅልህ ፊት ጀርባ ከፍተኛ ስቃይ አለ። የደስታ እጦት በፈገግተኛ ፊት እና በሚያምሩ ነጭ ጥርሶች ጀርባ ሲደበቅ ወይም ደስታ ማጣትህን ለራስህም ጭምር ሳትቀበል ስትቀር ድብርት ውድቀት ፣ጉስቁልና እና ግልፍተኝነት የተለመዱ ከስተቶች ይሆናሉ።

“ደህና ነኝ” የሚለው ኢጎ የሚላበሰው ሚና፣ "የተጎሳቆሉ መምሰል " የተለመደ በሆነባቸውና በማህበረሰቡም መደበኛ ከሆነባቸው ከሌሎች አገሮች ይልቅ በአሜሪካ ጎልቶ ይታያል። ምናልባት ግነት ሊሆን ይችላል፣ ነገር ግን በአንደኛው የኖርዲክ አገር መዲና ውስጥ መንገድ ላይ ለማታውቀው ሠው ፈገግ ካልክ፣ ሰከረሃል ተብለህ ልትታሰር እንደምትችል ሰምቻለሁ።

መከፋት በውስጥህ ካለ በመጀመሪያ መኖሩን ልትቀበል ይገባል። “ደስተኛ አይደለሁም” ግን አትበል። ደስታን ማጣት ከማንነትህ ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም። ይልቁንም “መከፋት በውስጤ አለ” ብለህ ከዚያ ነገሩን ለመመርመር ሞክር። ምናልባት ያለህበት ሁኔታ፣ ለዚያ ምክንያት ሊሆን ይችላል።

ስለዚህ ሁኔታውን ለመቀየር ወይም ከሁኔታው ለመውጣት እርምጃ መውሰድ የማትችል ከሆነ ደግሞ ያለውን ነገር ተጋፍጠህ “ደህና፣ በዚህ ሰዓት ነገሩ እንዲህ ነው፤ ልቀበለው ይገባል ” በል። የደስታ እጦት ዋነኛ ምክንያቱ የተከሰተው ነገር ሳይሆን፣ ለሁኔታው ያለህ ሃሳብ ነው። ስለዚህም ሃሳብህን አስተውል። ሁልጊዜ ገለልተኛ እና እንደነበር ከሚሆነው ክስተት ሃሳብህን ለይተህ ተመልከት። ስለሁኔታው ሃሳቦች እየጨማመርክ ነገር ከማወሳሰብ፣ክስተቱ ወይም እውነታው ይሄ ሲሆን ለሁኔታው ያለኝ ሃሳብ ደግሞ ይሄ ነው፤ ብለህ በእውነታው ላይ አተኩር።

ለምሳሌ “አለቀልኝ” ካልክ አንተን የሚገድብና ተገቢ እርምጃ እንዳትወስድ የሚያደርግህ ታሪክ ነው። “በአካውንቴ የቀረኝ ሃምሳ ሳንቲም ብቻ ነው” ብትል ግን እውነታ ነው። እውነታውን መጋፈጥ ደግሞ ሁልግዜም ቢሆን ሃያል ያደርጋል። የምታስበው ነገር ስሜትህን ለማወክ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ልብ ብለህ አስተውል። በሃሳብህና በታወከው ስሜትህ መሃል የሚኖረውን ቁርኝት ተመልከት። ሁልጊዜ ታድያ፣ ሃሳብህንና ስሜትህን ከመሆን ይልቅ ከባሻገራቸው ያለውን አስተውሎ ሁን።

ደስታ ለማግኘት አታፈላልገው፤ ካፈላለግከው አታገኘውም፤ ምክንያቱም ማፈላለግ በራሱ የደስታ ጸር ነው። ደስታን ለመጨበጥ አዳጋች ነው። ከደስታ እጦት ነፃ መውጣት ግን፣ አሁኑኑ ማሳካት የምትችለው ነገር ነው።

ይህ የሚሆነውም ለሚፈጠረው ሁሉ፣ ታሪክ ከማበጀት ይልቅ ነገሩን እራሱን በመጋፈጥ ነው። የደስታ እጦት ተፈጥሮአዊውን የደህንነት፤ የውስጣዊ ሰላምንና የእውነተኛ ደስታን ምንጭ ይጋርዳል።
ኤካህርት ቶሌ

ከንባብ ዳርቻ ለህይወት ጠአም!
#share and # join for more
@KenibabDaricha
@KenibabDaricha
2.2K views€£phâ (SânTos), 19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 14:04:26 ወላጅነት

ብዙ ጎልማሶች ህጻናትን ሲያዋሩ ሚና ይላበሳሉ። አስቂኝ ቃላትና ድምፆችን ይጠቀማሉ። ህፃኑን ቁልቁል እያዩ ያወሩታል። ህፃኑን እንደ ሰው አይመለከቱትም ለጊዜው የበለጠ ማወቅህና የበለጠ ግዙፍ መምሰልህ ህፃኑ ጋር እኩል ያልሆንክ አያደርግህም። ብዙ ጎልማሶች በህይወታቸው የሆነ ውቅት ላይ አለማቀፋዊ የሆነውን የወላጅነት ሚና ይቀላቀላሉ።

መሰረታዊ የሆነው ጥያቄ ታዲያ፣ የወላጅነት ተግባርን ከተግባሩ ጋር ራስህን አንድ ሳታደርግ ወይም ሚናን ሳትላበስ ለመወጣት ብቁ ነህ ወይ? ልጁ የሚያስፈልገውን ነገር ማሟላት፣ ልጁን ከአደጋ መጠበቅ እንዲሁም አልፎ አልፎ ማድረግ ያለበትንና የሌለበትን መምከር ለልጁ ልታደርግላቸው ከሚገቡ ነገሮች ውስጥ የሚጠበቁ ናቸው፡ ነገር ግን ወላጅነት ራሱ ማንነትህ ሲሆን የማንነት ስሜትህ በጥቅሉ ወይም በዋናነት ከዚሁ ተግባር የተቀዳ ከሆነ፣ ተግባሩ በራሱ ከተገቢው በላይ ይሆንና ሙሉ በሙሉ ይቆጣጠርሃል::

የወላጅነት ሚናን መጫወት ማንነታቸው አድርገው የያዙ እናቶች ወይም አባቶች፣ ምሉዕነታቸውን በልጃቸው በኩል ለማግኘት ይሞክራሉ። ኢጎ የጎዶሎነት ስሜቱን ለመሙላት ሲል ሌሎችን የመጠቀም ፍላጎቱን ወደ ልጆች ያነጣጥራል። ወላጆች የማያስቡትና የማይቆጣጠሩት ልጃቸውን የመዘወር ስሜት ቢገለጥና ሲናገር እንዲህ የሚል እንድምታ አለው፤ “እኔ ያላሳካሁትን እንድታሳካ እፈልጋለሁ፣ በሌሎች ዘንድ ሠው ሆነህ እንድትታይ እፈልጋለሁ፣ እኔም ባንተ በኩል የሚገባኝን ክብር አገኛለሁ፤ አታስቀይመኝ። ለአንተ ስል ብዙ መስዋዕትነት ከፍያለሁ። የምቆጣህም ሆነ የምቀየምህ ፀፀት እንዲሰማህና ወደ ራስህ ተመልሰህ ፍላጎቴን እንድትፈፅምልኝ ነው። የሚበጅህን አውቃለሁ”
ሲልም ይቀጥላል። “ለአንተ እንደሚበጅህ የማውቀውን ነገር እስከተገበርስ ድረስ እወድሃለሁ፤ እየወደድኩህም እኖራለሁ።”

ለነርሱ ከነበረህ የከረመ ልማድ እና ምላሽ ጀርባ ያለውን የእራስህን አላስፈላጊ ግምትና ፍላጎት ለማስተዋል ሞክር። “ቤተሰቦቼ የኔን ህይወት ሊቀበሉ ይገባል፣ ሊረዱኝና ማንነቴን ሊቀበሉ ይገባል።” የምርህን ነው?ለምንድን ነው የሚገባው? እውነታው ግን አያደርጉትም፤ ምክንያቱም አይችሉም። ገና እያበበ ያለው ማስተዋላቸው ይህን ለመረዳት የሚያበቃቸው አይደለም። ከሚናቸው ለመነጣጠል ገና ብቁ አይደሉም።

“አውቃለው ነገር ግን በእኔነቴ ካልተቀበሉኝና ካልተረዱኝ ደስተኛ መሆን አልችልም፤ ምቾትም አይሰጠኝም።” የምርህን ነው? እነሱ ተቀበሉህ አልተቀበሉህ በእውነተኛ ማንነትህ ላይ ምን ለውጥ ያመጣል? እነዚህ ሁሉ ያልመረመርካቸው ግምቶች፣ ትልቅ አሉታዊ ስሜትና የደስታ እጦት ያስከትሉብሃል።

ንቁ ሁን። “ዋጋ የለህም፣ አትረባም”ን የመሳሰሉት በአዕምሮህ ውስጥ የሚመላለሱ ሃሳቦች የእናትህ ወይም የአባትህ ድምፆች ናቸው። ወይም ደግሞ፣ ሌላ አይነት ግምቶች አልያም አዕምሮአዊ አቋሞች ናቸው። ማስተዋሉ ካለህ ጭንቅላትህ ውስጥ የሚመላለሰውን ድምፅ በትክክል ትረዳዋለህ፤ማለትም ያለፈውን ማመን ታቆማለህ። ያረጀ ሃሳብ ነው። ማስተዋሉ ካለህ በምታስበው በእያንዳንዱ ሃሳብ ማመን ታቆማለህ። ያረጀ ሃሳብ እንጂ ሌላ አይደለም። ማስተዋል ማለት አሁንን መኖር ማለት ነው። በውስጥህ ያለውንም የማታስተውለውን ሃሳብ የሚያከስመውም አሁንን መኖር ብቻ ነው።"

ከንባብ ዳርቻ ለህይወት ጠአም!!
#share and # join it
@KenibabDaricha
@KenibabDaricha
5.7K views€£phâ (SânTos), 11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ