Get Mystery Box with random crypto!

የኛ ሳይኮሎጂ||🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ yegna_psychology — የኛ ሳይኮሎጂ||🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ yegna_psychology — የኛ ሳይኮሎጂ||🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @yegna_psychology
ምድቦች: የልጅ እንክብካቤ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 17.15K
የሰርጥ መግለጫ

የተለያዩ አስተማሪ እና አዝናኝ አስተሳሰባችንን የሚያሳድጉ የሳይኮሎጂ እና የፓለቲካ ፅሁፎች ይቀርቡበታል።
የኛ ሳይኮሎጂ ይተነተናል እንዲሁም ታዋቂ የሥነ-ልቦና ሊሂቃን (theory) ይዳሰሳል።
🌟ማሳሰብያ ለውድ ተከተዮቻችን:➪አባላትን ለማብዛት በምናደርገው #የማስታወቂያ ልውውጦች እንዳትሰላቹብን ለማለት እንወዳለን።

[ ራሳችንን በመቀየር ድርሻችንን እንወጣ! ]

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-29 05:42:52 ለሰው ልጅ ግን በምድር ላይ ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም።
***
ከዚያም ከኮረብታው ወረደ፤ እኛም ተከተልነው። ይሁዳም ከሩቅ ተከተለ። ቆላማው ቦታ ላይ ስንደርስ ሌሊት ሆኖ ነበር።
ቶማስም እንዲህ አለው፡- "መምህር ሆይ አሁን ጨለማ ነው፤ መንገዱንም ወደ ፊት ማየት አንችልም። ፈቃድህ ከሆነ ምግብና መጠለያ ወደምናገኝበት ወደዚያኛው መንደር ምራን"
ኢየሱስም ለቶማስ መለሰ፤ እንዲህም አለ፡- "በተራባችሁ ጊዜ ወደ ከፍታው ይዣችሁ ወጣሁ፡፡ እጅግ በተራባችሁ ጊዜ ወደ ሜዳው ይዣችሁ ወረድኩ።

ነገር ግን ዛሬ ማታ ከእናንተ ጋር መቆየት አልችልም። ብቻዬን ልሆን ይገባኛል”
ስምዖን ጴጥሮስም ወደ ፊት በመውጣት ‹‹መምህር ሆይ በጨለማ መሀል ትተኸን አትሂድ። በእዚህም ቦታ ቢሆን ከአንተ ጋር እንድንቆይ ፍቀድልን። ሌሊቱ እና የሌሊቱ ጥላ አይዘገይም፣ ከእኛ ጋር ከቆየህ ንጋት በቅርቡ ያገኘናል"
ኢየሱስም መልሶ፡- ‹‹በዚች ሌሊት ለቀበሮዎች ጕድጓድ፣ ለሰማይ ወፎችም ጎጆ ይኖራቸዋል፥ ለሰው ልጅ ግን በምድር ላይ ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም።

እናም በእርግጥ አሁን ብቻዬን እሆናለሁ፤ ከፈለጋችሁኝ እናንተን ቀድሞ ካገኘሁበት ሐይቅ አጠገብ ታገኙኛላችሁ›› አለ፡፡
በከባድ ሀዘን ውስጥ ሆነን ከእርሱ ራቅን። ደጋግመን እየቆምን ፊታችንን ወደ እርሱ አዙረን ተመለከትነው፤ እናም በብቸኝነት ግርማ ወደ ምዕራብ ሲንቀሳቀስ አየነው።
ከመካከላችን እርሱን ለማየት ፊቱን ያላዞረው ሰው የአስቆሮቱ ይሁዳ ብቻ ነበር።
ይሁዳም ከዚያ ቀን ጀምሮ ደነገጠ፥ ራቀም። እኔም በፊቱ አደጋ እንዳለ አሰብኩ
- Khalil Gibran

THANK YOU FOR READING.
ELODIA READING
ኤሎድያ ንባብ

@Elodia_G ንባብ @Elodia_G
READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G
READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G
READING
2.5K views€£phâ (SânTos), 02:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-26 20:18:42 እውነት ከውሃ ጉድጓድ ሥር !!"

#አንድ ቀን እውነት እና ውሸት ይገናኛሉ። "ውሸት ለእውነት ማዛሬ አስደናቂ ቀን ነው” ትላታለች። እውነት ወደ ሰማይ ቀና ብላ ትመለከትና እውነትም ቀኑ እጅግ ውብ መሆኑን ታስተውላለች። ከዚያም ቀኑን ሙሉ አብረው ያሳልፉና በመጨረሻ በአንድ የውኃ ጉድጓድ አጠገብ ይደርሳሉ ፡፡ ውሸት እውነትን በድጋሚ “ውሃው በጣም ጥሩ ነው፤ አብረን እንታጠብ!” ትላታለች። እውነትም የጉድጓዱን ውሃ ባየች ጊዜ ጥሩ መሆኑን ተገነዘበች፡፡ በዚህም፣ እውነት የአብረን እንታጠብ ግብዣውን ተቀብላ ልብሳቸውን ከጉድጓዱ ዳር አስቀምጠው መታጠብ ይጀምራሉ።

#መታጠቢያ ጉድጓዱ ውስጥ እያሉ ውሸት ከውሃው በድንገት ትወጣለች፤ የእውነትንም ልብስ ትለብስና ትሸሻለች፡፡ በሁኔታው በጣም የከፋት እውነት ከጉድጓዱ ትወጣና ውሸትን ለማግኘት እና ልብሷን ለመቀበል በየቦታው ትሯሯጣለች፡፡ በየመንገዱ የምታገኛቸው ሰዎች እውነትን እርቃኗን በማየታቸው በንቀት እና በንዴት ይመለከቷታል፡፡ ውሸትን ሮጣ መያዝ ያልቻለችው ምስኪኗ እውነት ወደ ጉድጓዱ ተመልሳ የውሃው ጉድጓድ ውስጥ በመደበቅ ለዓለም ስትል እርቃኗን ለዘላለም ትሸፍናለች፡፡

#እነሆ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ውሸት እንደ እውነት ለብሶ በዓለም ዙሪያ በመዘዋወር የኅብረተሰቡን ፍላጎቶች በማርካት ላይ ይገኛል። ዓለምም እውነትን የመፈለግ በጭራሽ ፍላጎት የለውምና የእውነት ለዘለዓለም በጉድጓዱ ውስጥ መቅረት አያስጨንቀውም፡፡ ዓለም፣ እውነት እርቃኗን ስትሆን የሚሸከምበት ሞራልም ስለሌለው በመደበቋ ደስተኛ ነው።

THANK YOU FOR READING.
ELODIA READING
ኤሎድያ ንባብ

#share and join for more

@Elodia_G ንባብ @Elodia_G
READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G
READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G
READING
3.5K views€£phâ (SânTos), 17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-24 15:48:21 የመስጠት ትርጉም

የአለማችን ቀዳሚ ባለጠጋ በአንድ ኢንተርቪው እንዲህ ተጠየቀ ከአንተ የሚበልጥ ባለጠጋ ማን ነው ?
ከአንተ የሚበልጥህ ባለጠጋ አለ ?

‹‹አዎ የሚበልጠኝ ሰው አለ፡፡ የሚበልጠኝ አንድ ሰው ብቻ ነው፡፡ ከብዙ ዓመት በፊት ወደ ኒውዮርክ መሄድ ነበረብኝ፡፡ ወደ ኒውዮርክ ለመሄድ አየር መንገድ ላይ ሳለሁ የተለያዩ ጋዜጦችን የጋዜጣ አዟሪዎች እጅ ላይ አየሁ፡፡ ካየኋቸው ጋዜጦች መካከል አንዱን ወደድኩት ለመግዛት አስቤ ኪሴ ስገባ ዝርዝር ስላጣሁ ሳልገዛው መልሼ ተውኩት፡፡

በድንገትም አንድ ጥቁር ጋዜጣ አዟሪ ልጅ መጣና ጋዜጣውን ሰጠኝ፡፡ ዝርዝር የለኝም አልወስደውም አልኩት እርሱም ችግር የለውም በነጻ ውሰደው አለኝና በነጻ ሰጠኝ፡፡

ከሦስት ወር በኋላ ተመልሼ በዚያው አየር መንገድ ማለፍ ነበረብኝና በዚያ አየር መንገድ ሳልፍ አሁንም አጋጣሚ ሆነና ያንን ጋዜጣ አዟሪ ጥቁር ልጅ አገኘሁት፡፡ አሁንም በነፃ ጋዜጣ ሰጠኝ፡፡ እኔም በነፃ አልቀበልህም አልኩት እርሱም ግድየለም ከትርፌ ላይ እቀንሳለሁ ውሰድ አለኝና በነጻ ሰጠኝ፡፡

ከ19 አመትም በኋላ ባለጠጋ ከሆንኩ በኋላ ያንን ልጅ ፈልጌ ለማግኘት ወሰንኩና ፈለኩት ከአንድ ወር ተኩል ፍለጋም በኋላ አገኘሁት፡፡ ከዚያም አወቅከኝ ብዬ ጠየኩት ፡፡ አዎ አውቅሃለሁ ዝነኛው ቢልጌት አይደለህም አለኝ፡፡ ከብዙ አመት በፊት ሁለት ጊዜ ጋዜጣ በነጻ ሰጥተኸኛል፡፡ ያንን ውለታህን አካክሼ መመለስ እፈልጋለሁና የፈለከውን የትኛውንም ነገር እሰጥሃለሁ ጠይቀኝ አልኩት፡፡

ያም ጥቁር ሰው በምንም መካካሻ ልትሰጠኝ አትችልም አለኝ
እኔም ለምን አልኩት
እኔ የሰጠሁህ ደሃ በነበርኩ ጊዜ ከድህነቴ ነው፡፡ አንተ ግን ልትሰጠኝ የመጣኸው ባለጠጋ በሆንክ ጊዜ ነው፡፡ እነዚህን ሁለቱን እንዴት አካክሰህ ልትሰጠኝ ትችላለህ፡፡

ቢልጌትም ያጥቁር ወጣት በርግጥም ከእኔ የሚበልጥ ባለጠጋ ነው፡፡
ለመስጠት ባለጠጋ መሆንህን ወይም ባለጠጋ እስክትሆን ድረስ አትጠብቅ ፡፡ መስጠት የልብ ጉዳይ ነው እንጂ የአቅም ጉዳይ አይደለም፡፡

THANK YOU FOR READING.
ELODIA READING
ኤሎድያ ንባብ!

    #share and join for more

@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
5.0K views€£phâ (SânTos), 12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 21:56:30 #አልዘገየህም_አልቀደምክም

* አንድ ሰው በ22 ዓመቱ ተመረቀ፣ ነገር ግን ጥሩ ሥራ ሳይሰራ 5 ዓመት ጠበቀ።

* አንድ ሰው በ25 ዓመቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነ፣ በ50 ዓመቱ ሞተ።

* ሌላው በ50 ዓመቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሲሆን፣ 90 ዓመት ኖሯል።

* አንድ ሰው እስካሁን ያላገባ ነው፣ ከትምህርት ቤቱ ጓደኛ የሆነ ሰው ግን አያት ሆኗል።

* ኦባማ በ55 ዓመቱ ጡረታ ወጣ፣ ትራምፕ በ70 ዓመቱ ጀመረ፡፡

በዚህ አለም ላይ ሁሉም ሰው የሚሰራው የጊዜ ክልሉን መሰረት አድርጎ ነው። በዙሪያህ ያሉ ሰዎች ከፊትህ ያሉ ሊመስሉ ይችላሉ፣ አንዳንዶች ደግሞ ከኋላህ ያሉ ሊመስሉ ይችላሉ። ሁሉም ግን የራሱን ሩጫ በራሱ ጊዜ እየሮጠ ነው። እነሱ በራሳቸው የጊዜ ክልል ውስጥ ናቸው፣ አንተ ደግሞ በራስህ ውስጥ ነህ።

አልዘገየህም አልቀደምክም፤ ባለህ ጊዜ ተጠቀም!

THANK YOU FOR READING.
ELODIA READING
ኤሎድያ ንባብ!

    #share and join for more

@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
5.4K views€£phâ (SânTos), 18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 15:48:55
አባትነት ክብር ነው!
አባትነት ፀጋ ነው!
አባትነት ጌጥ ነው!
አባትነት መመረጥ፣ መባረክ ነው!
አባቶች እንኳን አደረሳችሁ!

መልካም የአባቶች ቀን!

ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ!
ወደ ዩትዩብ ቻናላችን በመግባት አሁን ቤተሰብ ይሁኑ!

SUBSCRIBE NOW!
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel
6.9K views€£phâ (SânTos), 12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-17 13:05:47 #ሁሉንም ጠይቅ - ሶቅራጠስ

ለሶቅራጥስ “አለማወቅን ማወቅ” የፍልስፍና መጀመሪያ ነው፡፡ አለማወቃችንን ሳናውቅ የእውቀትን መንገድ መጀመር አንችልም፡፡

በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ “አላውቅም” ማለት የመሃይም ምልክት ሆኖ ቆይቷል። ልክ ኃጢአትን እንደሰራ ሰውም ትቆጠራለህ፤ ችግር እንዳለብህም ይታሰባል። መድኃኒትን ፍለጋም ወደ መምህራን ወይም አዋቂ ወደተባሉ ሰዎች እንድትሄድ ይነገርሃል።

ለሶቅራጥስ ሁለት አይነት አላዋቂነቶች አሉ።

1.አለማወቅን_አለማወቅ።
ይህ በሕይወትህ ላይ ምን እንደማታውቅ ሳታውቅ መኖር ማለት ነው። እነዚህ ራሳቸውን አይጠይቁም አውቃለሁ አላውቅም ብለውም አይመረምሩም፡፡ ሕይወታቸውንም በእንቅልፍ ውስጥ እንዳለ ሰው፣ ሁሉንም አውቃለሁ እያሉ ይኖራሉ፡፡ ሃሳባቸውን ለመመርመር ቆም ብለው አያስቡም፡፡

2.ሶቅራጥሳዊ አለማወቅ ።
ይህ ከእንቅልፋችን ነቅተን እና አይናችንን ገልጠን መጠየቅ ስንጀምር ያለውን ጊዜ ያመለክታል። የምናውቀውን ሁሉ እንጠረጥራለን::

ሁለተኛውን አለማወቅ ሶቅራጥስ የተቀደሰ አለማወቅ ይለዋል፡፡  የምናውቃት ጥቂት ናት፤ ከምናውቀውም የሆነ ጊዜ፣ የሆነ ቦታ ላይ ስህተት መኖሩን እንረዳለን፡፡
ሶቅራጥስ በዚህ አባባሉ ይታወቃል፤ “Unexamined life is not worth living' (ያልተመረመር ሕይወት ሊኖሩት ያልተገባ ነው።)

ምንጭ :- ፍልስፍና ከዘርዓ ያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ

THANK YOU FOR READING.
ELODIA READING
ኤሎድያ ንባብ!

    #share and join for more

@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
6.5K views€£phâ (SânTos), 10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-15 10:51:41 #የሰው ልጅ የአዕምሮውን እምቅ አቅም እንዲጠቀም ነገሮችን የመከወን ተነሳሽነት ይፈልጋል። ለስራ ያለን ተነሳሽነት ደግሞ የህይወት ግባችን ላይ ለመድረስና ደስተኛ ህይወትን ለመኖር ቁልፍ ሚና ይጫወታል።

አምሥቱ የስኬት ምስጢሮች ብለን ያስቀመጥነው

1ኛ. ትኩረተ አመክንዮ :-ጠንካራ የሆነ አመክንዮ ካለን ፡ ፈታኝ ሁኔታዎች ቢያጋጥሙን እንኳ መስመራችንን እንዳንስት ያግዘናል።

ምናልባት ፡ እኛ የምንፈልገውን ውጤት ለማሳካት ስንል የምናከናውናቸውን ተግባራት ላንወዳቸው እንችል ይሆናል። እንደተራራ የገዘፉና አይነኬ የሚመስሉ መሰናክሎች ሆነውብንም ይሆናል። ነገር ግን የምንፈልገውን የስኬት ማማ ስናስብ  በቀላሉ እናልፋቸዋለን።

2ኛ. ተግባራትን መከፋፈል :-አንድን ተግባር በትናንሽ የድርጊት ክፍሎች መበተን ለዚያ ተግባር ያለን አመለካከት እንዲለወጥ የሚያደርግና አስገራሚ ውጤቶችን እንዲናገኝ የሚያግዝ ጥሩ ዘዴ ነው::

3ኛ. እንደምንችል ለራሳችን ማረጋገጥ!

ለሌሎች ሰዎች ስለራሳችን የምንናገርበት መንገድ በህይወታችን ማድረግ በምንችላለውና በማንችላቸው ነገሮች ላይ ይልቅ ተፅእኖ አለው።

4ኛ. ስራዎችን እንደመዝናኛ ቆጥረን ማከናወን!

የሚያዝናናንን ስራ መስራት ያስደስተናል። ውጥረት ውስጥ የሚከተንንና የማያስደስተንን ስራ መስራት ደግሞ ውጤቱ በተቃራኒው ነው።

ለምሳሌ፡- እኔ አንድን ስራ ለማከናወን ከሚያስፈልገኝ ጊዜ 5 ደቂቃ ቀድሜ ተግባሩን ለመጨረስ ከጣርኩ ፡ ከስራው በኋላ ለመዝናናት የሚሆን ጊዜ እንደሚኖረኝ ስለማስብ ፡ ስራው ጫና ሳይሆን መዝናኛ ይሆንልኛል። ስራን እንደ መዝናኛ የሚመለከቱ ሰዎች አጋጥመዋችሁ ያውቁ ይሆናል። እነዚህ ሰዎች በስራቸው ደስተኞች ናቸው ፡ ምክንያቱን ስራቸውን እንደመዝናኛ ቆጥረውት እየተዝናኑ ስለሚሰሩ ፡ ስልቹ አይደሉም ፤ ከፍ ያለ ተነሳሽነትም አላቸው።

5ኛ. በራስ የመተማመን ስሜትን መገንባት!

ራሳችሁን በነዚህ ሁለት ሁኔታዎች ውስጥ አድርጋችሁ አስቡ፡፡ ለራሳችሁ የህይወት ግብ ለማስቀመጥ የተቸገራችሁበትን አጋጣሚ አስቡ። ምን ተሰማችሁ? ሽንፈት ፣ ድካም ፣ ተስፋ መቁረጥ ፣ መውደቅ ወዘተርፈ አይዴል? እስኪ አሁን ደግሞ የህይወት ግባችሁን ጥርት ባለ መልኩ አስቀምጣችሁ አስቡ፡፡ ይህ በራስ የመተማመን ስሜት ተነሳሽነታችንን በመጨመር ወደምንፈልገው ስኬት የሚያደርሱንን ተግባራት እንድናከናውን አቅም ይሰጠናል::

ELODIA READING
ኤሎድያ ንባብ!

    #share and join for more

@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
@Elodia_G ንባብ @Elodia_G READING
6.0K views€£phâ (SânTos), 07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 20:45:30 እውነት ጫማውን እስኪያጠልቅ ውሸት ዓለምን በግማሽ ይዞራል!
-- Mark Twain --
6.9K viewsABDU, 17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 17:53:45 የሰው ልጅ አዕምሮው ላይ ከሚሰራዉ ትልቅ ወንጀል አንዱ ነገሮችን ያለማስረጃ ማመን ነው!
    
Aldous Huxley
7.5K viewsABDU, 14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 21:11:18 ለሰው ምን ያህል መሬት ይበቃዋል?
(በሌቭ ቶልስቶይ)


ከረዥም ዘመን በፊት በአንድ ትንሽ የደቡብ ኤዥያ አገር የሚኖሩ ብልህ ንጉሥ ነበሩ። ግዛታቸውን ለመገንጠል የተነሳ አንድ የውስጥ ወንበዴ ቡድን አስቸግሯቸው ስለነበር በጦርነት ሊያጠፏቸው ወሰኑ፤
ለጦር አዛዡም ይህን ጦርነት በድል ፈፅሞ ከተመለሰ ከፍተኛ የሆነ ሀብትና መሬት እንደሚሰጡት ቃል ገቡለት። በዚህም የተነሳ የንጉሡ ጦር በከፍተኛ ቆራጥነት ተዋግቶ የወንበዴው ጦር ተደመሰሰ። የሞተው ሞቶ የቀረው ቆስሎም ተማረከ፤
ንጉሡ ቃል እንደገቡት ለጦር አዛዡ ብዙ ሀብት ከመደቡለት በኋላ "በእግሩ ቀኑን ሙሉ ፀሀይ እስክትጠልቅ የሄደበትን የግዛቴን መሬት ለክታችሁ ስጡት።" ብለው ሸለሙት።

የጦር አዛዡም ተደሰተ፤ ብዙ ለም የሆነ መሬት መያዝ ይፈልግ ስለነበር በተዘጋጀበት ቀን በጣም በማለዳ ተነስቶ ስንቅ አዘጋጅቶ መጓዝ ጀመረ። በመጀመሪያ ጉልበቱ የቻለውን ያህል በለሙ መሬት ላይ ሮጠ። መሬት ለኪዎችም በፈረስ ይከተሉት ነበር፤
ከዚያም በፍጥነት ቀኑ ሳይመሽ ይራመድ ጀመር። ብዙ ከሄደ በኋላ ወደ ከሰአት ምሳውን ሳይቀር እየሄደ በላ።

ሆኖም ከበላ በኋላ ጥቂት መሬት ሄዶ ስለደከመው እየተራመደ ውሃ ጠጣ። ዘጠኝ ሰአት ያለእረፍት ተጉዞ በመጨረሻ እገሩ በጣም ዛለ፤
ቢሆንም አንድም እርምጃ ቢሆን ለም መሬት ነውና መራመዱን ቀጠለ። ሲል ሲል እግሩ መራመድ አቅቶት ዝሎ ወደቀ።
አሁን ለኪዎቹ ምልክት ሊያደርጉ ሲሉ "ቆዩ ... ቆዩ" ብሎ መዳኽ ጀመረ። ከዚያም ጥቂት ሄዶ በልቡም መሳብ ጀመረ፤
በመጨረሻ ፀሃይ ገና ሳትጠልቅ የቻለውን ተንጠራርቶ ሲሳብ ልቡ ቀጥ አለችና ትንፋሹ ቆሞ ሞተ። የንጉሡ ቦታ ለኪዎችም ደነገጡ።

የጦር አዛዡን ከሞተበት ሳያነሱ በፈረስ መልእክተኛ ወደ ንጉሡ ቤተ መንግሥት ላኩ፤
መልክተኞቹም የአዛዡን ሲጓዝ ውሎ ልቡ ደክሞ መሞቱን ነግረው "ምን ያህል መሬት እንስጠው?" ብለው ጠየቁ። ንጉሡም እጅግ አዝነው "ለሰው ምን ያህል መሬት ይበቃዋል?" ብለው ተከዙ፤
"እንግዲህ ይህ ሰው የወደቀበትን ቦታ ብቻ ከእግሩ ጫፍ እስከ ራሱ ጫፍ ብቻ ለክታችሁ ስጡት። ሬሳውንም እዚያው ቦታ ቆፍራችሁ በክብር ቅበሩትና የጀግና ሃውልት አቁሙለት።" አሏቸው፤
በተባለው መሰረት የጦር አዛዡ በመጨረሻ በሞተባት ቦታ በክብር ተቀበረ። በመቃብሩም ሀውልት ላይ

"ለሰው የሚበቃው መሬት ይህ ነው።" ተብሎ ተፃፈ።

ከንባብ ዳርቻ ለህይወት ጠኣም
#share and join for more
@KenibabDaricha1
@KenibabDaricha1
9.7K views€£phâ (SânTos), 18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ