2022-09-23 19:10:44
#ቲንክአቢሲኒያ_የመክሰስ_መረጃዎች
1፤የኢትዮጵያ አየር መንገድ አራት የዓለም አየር መንገድ ሽልማቶችን አሸነፈ።የኢትዮጵያ አየር መንገድ በስካይትራክስ 2022 የዓለም አየር መንገድ ሽልማት ላይ አራት ሽልማቶችን አሸንፏል። በዚህም አየር መንገዱ ለአምስት ተከታታይ ዓመታት የ2022 የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ፣ ለአራት ተከታታይ ዓመታት የአፍሪካ ምርጥ የቢዝነስ ደረጃ አየር መንገድ፣ ለአራት ተከታታይ ዓመታት የአፍሪካ ምርጥ የምጣኔ ሀብት ደረጃ አየር መንገድ እንዲሁም በአፍሪካ ውስጥ ምርጥ የቢዝነስ ክላስ ምግብ አቅራቢነትን አሸንፏል፡፡
2፤ከአፋር ክልል ህዝብ 75 በመቶው የምግብ እጥረት አለበት ተባለ።75 በመቶ ያህሉ የአፋር ሕዝብን የምግብ እጥረት ያለበት ተብሎ መለየቱን የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤትን ጠቅሶ ዶቼቬሌ ዘግቧል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ መሐመድ ሁሴን ለዶቼ ቬለ እንደተናገሩት ዳግም ባገረሸው ጦርነት ሰለባ የሆኑ ከ120 ሺህ በላይ ዜጎች ተፈናቅለው በአራት መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ይገኛሉ ብለዋል።
3፤ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ በአውሮፓ ፓርላማ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ጋር ተወያዩ።የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በአውሮፓ ፓርላማ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዴቪድ ማካሊስተር የተመራውን ልዑክ በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና በአፍሪካ ሕብረት ስለሚመራው የሰላም ንግግር ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡ የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ እንዳመላከተው የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሮናልድ ኮቢያ ከልዑኩ ጋር ተገኝተው በውይይቱ ተሳትፈዋል፡፡
4፤ሩሲያ አውሮፓንና አሜሪካን በሀይፐርሶኒክ ሚሳኤል ልትመታ እንደምትችል አስጠነቀቀች።ለአዲሱ ተልዕኮዋ እንዲረዳትም 300 ሺህ ተጠባባቂ ጦሯን የጠራችው ሩሲያ ብሄራዊ ደህንነቷ ስጋት ውስጥ ከገባ ደግሞ የኑክሌር ጦሯን ጨምሮ ማንኛውንም መንገድ እንደምትጠቀም ፕሬዝዳንት ፑቲን ተናግረዋል። ለዚህ ጉዞዋ እንቅፋት ከሆኑ አውሮፓን እና አሜሪካን በሀይፐርሶኒክ ሚሳኤል ልትመታ እንደምትችል አስጠንቅቃለች።
5፤ዛሬ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካን ዶላር በ52 ብር ከ5646 ሳንቲም ሲገዛ ውሏል።እንዲሁም መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ6159 ሳንቲም መሆኑን ከድረገጹ ተመልክተናል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋው 56 ብር ከ7402 ሳንቲም እንዲሁም መሸጫው 57 ብር ከ8750 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ51 ብር ከ2028 ሳንቲም እየተገዛ በ52 ብር ከ2269 ሳንቲም የተሸጠ ሲሆን፣ አንድ የቻይና ዩዋን ደግሞ በ6 ብር ከ7172 ሳንቲም ተገዝቶ በ6 ብር ከ8615 ሳንቲም ሲሸጥ እንደነበር ቲንክአቢሲኒያ ተመልክቷል።
6፤ቅዱስ ጊዪርጊስ በመለያያ ምት ኢትዮጵያ ቡናን በማሸነፍ ለፍፃሜ አለፈ።ዛሬ በ 16ተኛው የአዲስ አበባ ሲቲ ካፕ ለዋንጫ ለማለፍ በሸገር ደርቢ ኢትዮጵያ ቡናና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተገናኝተው ጨዋታው በመደበኛው 90 ደቂቃ 1 አቻ በመጠናቀቁ ወደ መለያ ምት ያመሩ ሲሆን በመጨረሻም በ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለዋንጫው ፍፃሜ ማለፉን አረጋግጧል። የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ከንቲባ አዳነች አበቤ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ለሁለቱም የመዲናዋ ክለቦች በድምሩ ሀያ ሚሊዮን ብር መስጠታቸውን ገልፀዋል።
• @ThinkAbyssinia •
8.1K views16:10