Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2022-09-23 12:02:06
ምንም አይንት ቤት ፤ መኪና ፤  ወ.ዘ.ተ መሸጥ መግዛት ማከራየት ከፈለጉ ከታች ባለው ስልክ በመደውል ለንብረቶ የሚገባውን ዋጋ  ያገኛሉ  ፤ አዋጭ ግብይት ይፈፅሙ፡፡                      ስልክ 0916410815 / 0970751841
ለተጨማሪ መረጃ ሊንኩን ይቀላቀሉ                         https://t.me/balemoyagebeyet
7.2K views09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 10:21:58
ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል አሉ

በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መስከረም 11 አንድ ግለሰብ ከሚስቱ እጅ ሞባይል መንትፎ ሲሮጥ በቁጥጥር ስር ውሏል።

ጉዳዩ እንዲህ ነው የአካባቢያቸውን ጸጥታ ለመጠበቅ የተሰማሩ አካላት (ሮንድ ጠባቂዎች) በምሽት አንድ ግለሰብ ከተበዳይ እጅ ሞባይል መንትፎ ሲሮጥ ተመልክተው ግለሰቡን ተከታትለው በቁጥጥር ስር በማዋል ለፖሊስ ያስረክባሉ።

በዚህን ግዜ ታዲያ ጉድና ጅራት ከወደኋላ ነው እንዲሉ አበው ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ሞባይሉን የዘረፈው ከራሱ ሚስት ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

• @ThinkAbyssinia •
7.9K viewsedited  07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 10:18:57
ኪያድ ዳቦ እና ኬክ
Kiyad Bakery and Coffee

ለልደት፣ ለሰርግ እና ለምርቃት በፈለጉት ዲዛይን እና መጠን እናዘጋጃለን።

Bring us your cake designs! We prepare cakes for every occasion!

0911467026
0913911679

የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይችላሉ

https://t.me/kiyad_bakery

አድራሻ: ልደታ ፍሊንት ስቶን አካባቢ
      የልደታ የፍታብሔር ምድብ ችሎት ፊት ለፊት

https://maps.app.goo.gl/4hYtermcawkxksDH7
6.8K viewsedited  07:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 09:57:04 #ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች

1፤የዓለም ቱሪዝም ቀን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ይከበራል።

የዓለም ቱሪዝም ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ከመስከረም 13 እስከ 15፣ በተለያዩ ኸነቶች ደምቆ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በአሶሳ ከተማ  ይከበራል፡፡ በኢትዮጵያ ለ35ኛ ጊዜ ‘’አዲሥ እሳቤ ለቱሪዝም’’ በሚል መሪ ሃሳብ የባሕላዊ ፣ታሪካዊ፣ ሰዉ ሰራሽና ተፈጥሯዊ መስህብ ሐብቶች ጉብኝት የሚደረግ ሲሆን፥ በተጨማሪም በዓሉ በኤግዚቢሽንና ሲምፖዚየም በአሶሳ ከተማና አካባቢዉ እንደሚከበር ከክልሉ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል፡፡

2፤በሱዳን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ችግር እንዳይገጥማቸው በትኩረት እየተሠራ ነው ተባለ።

በሱዳን የኢፌዴሪ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ከሱዳን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሌተናል ጄኔራል አናን ሃሚድ ሞሃመድ ኦማር እና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስር ያሉ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሱዳን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተመለከተ ባደረጉት ውይይት በሱዳን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ችግር እንዳይገጥማቸው ጥያቄዎቻቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱ የሀገራቱ መሪዎች ጭምር በትኩረት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል፡፡

3፤አዲስ አበባ 8ኛውን የኢትዮ-ሩሲያ የጋራ መድረክ ለማስተናገድ ዝግጅት እያደረገች ነው።

ኢትዮጵያ ለምታስተናግደው የ8ኛው የኢትዮ-ሩሲያ የጋራ የምጣኔ ሃብት የምክክር መድረክ ዝግጅት የሚያግዝ ውይይት በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተካሄዷል። ውይይቱ ከዚህ ቀደም በፒተርስበርግ በተካሄደው 7ኛው የኢትዮ-ሩሲያ የጋራ መድረክ የተወሰኑ፣ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል፡፡ሚኒስትሩ የመንግስት አካላት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

4፤አዲሱ የኬንያ ፕሬዝዳንት ለአፍሪካ ሀገራት የእዳ ስረዛ እንዲደረግ ጠየቁ።

አዲሱ የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የበለጸጉ ሀገራት እና አለምአቀፍ አበዳሪዎች በድሃ የአፍሪካ ሀገራት ላይ ያሉ የዕዳ ጫናዎችን እንዲገመግሙ ጠይቀዋል። ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በኒውዮርክ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ነው ይህንን ጥሪ ያቀረቡት። በተለይ የአፍሪካ ሀገራት በግጭት እና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ከፍተኛ ጫናዎች እንደነበሩባቸውም ተናግረዋል።

5፤ሰሜን ኮሪያ ለሩሲያ ያደረኩት ምንም አይነት የጦር መሳሪያ ድጋፍ የለም አለች።

ሰሜን ኮሪያ ለሩሲያ የጦር መሳሪያ ድጋፍ አድርጋለች መባሉን ያስተባበለች ሲሆን አሜሪካ የሀገሪቱን ስም ከማጠልሸት እንድትቆጠብም አስጠንቅቃለች። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ቃል አቀባይ ቬዳንት ፓቴል "ሰሜን ኮርያ ለሩሲያ በሚሊየን የሚቆጠሩ ሮኬቶችን እና መድፎችን ግዥ እየፈጸች ነው" በማለት ከሳምንት በፊት መናገራቸውን ተከትሎ ነው ሰሜን ኮሪያ ማስተባበያ የሰጠችው፡፡

6፤ኢትዮጵያና ሱዳን የወዳጅነት ጨዋታቸውን ዛሬ ያካሂዳሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሱዳን አቻው ጋር ከሚያደርጋቸው ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎች መካከል የመጀመሪያውን ዛሬ ረፋድ ሲያካሂድ ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታውን ደግሞ መስከረም 16 ቀን 2015 ዓ.ም በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከቀኑ 10 ሰአት ያደርጋል። በፊፋ ወርሃዊ የአገራት የእግር ኳስ ደረጃ ኢትዮጵያ 138ኛ፤ ሱዳን ደግሞ 130ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

• @ThinkAbyssinia •
6.5K views06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 09:52:50
ሱቅ ለሱቅ መሄድ ሳይጠበቅቦት ባሉበት ቦታ ሆነው ውስን  እቃዎችን በማይታመን ዋጋ ሚገኙበትን ማወቅ ዪፈልጋሉ ፤ እንግዲያውንስ ይሄን ሊንክ ይጫኑ፡፡ከላይ ያሉትን የጫማዎች ዋጋ እና ብዙ አማራጮችን ለማግኘት  ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ


https://t.me/joinchat/AAAAAElITjwlFLHHO8h7Sg


ይዘዙ በውስጥ መስመር የመረጡትን ፎቶ  ይላኩልን በቀላሉ እናስተናግዳለን ግዜዎን ቆጥበን።
inbox 1         inbox2
    @businesslidu   @businesslidu2

online shopping is always a good idea!!
አድራሻ አዲስ አበባ ቦሌ መ/ም ኤድናሞል አደባባይ ዞሮ ሬድዋን ህንጻ ጎን ራክሲም ህንጻ 3ኛ ፎቅ በስተቀኝ ዞር ሲሉ ያገኙናል።

0919998383
በውስጥ መስመር ለመፃፍ    @businesslidu & @businesslidu2
6.4K views06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 08:45:24
የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ተሞክሮ ለ10 የአፍሪካ አገሮች ሊያጋራ ነው ተባለ

በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 77ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን ዩኤንዲፒ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት እየተተገበረ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር  ተሞክሮ ላይ የውይይት መድረክ አካሂዷል። ዩኤንዲፒ የመርሐ ግብሩን ተሞክሮ በቀጣይ በ10 የአፍሪካ አገሮች እንደሚያጋራ አሳውቋል።

በመድረኩ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሩ ኢትዮጵያ ለተወሰኑ ጎረቤት አገሮች ችግኝ ማቅረቧን አስታውሰው፤ ቀጣናዊ ትብብሩን ለማጠናከርና የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽዕኖን ለመቋቋም ችግኝ የማቅረቡ ተግባር እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

• @ThinkAbyssinia •
6.9K views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 06:56:58
#ቲንክአቢሲኒያ_እለታዊ_የአየር_ትንበያ_መረጃ

ጤና ይስጥልን እንደምን አድራችኋል ውድ ቤተሰቦች ወቅቱ ክረምት ነውና ለውሎዎ ጠቃሚ የሆኑ እለታዊ የአየር ትንበያ መረጃዎችን እናድርስዎ

ዛሬ በአንዳንድ የሀገራችን ከተሞች ያለውን ያየር ሁኔታ ስንመለከት መዲናችን አዲስ አበባ ዝቅተኛው 12 ከፍተኛው 21 ድግሪ ሲልሽየስ ቀላል ዝናብ ታስተናግዳለች።

ባህርዳር ዝቅተኛው 15 ከፍተኛው 26 ቀላል ዝናብ ሀዋሳ ዝቅተኛው 15 ከፍተኛው 25 ዝናባማ እንዲሁም መቀሌ ዝቅተኛው 12 ከፍተኛው 24 የአየር ሁኔታው ከፊል ደመናሜ ሆነው እንደሚውሉ ቲንክአቢሲንያ ከቤሄራዊ ሜትሮዎሎጂ ኤጀንሲ ድረገፅ ተመልክቷል።

ኤጀንሲው የዕለቱን የአየር ሁኔታ ትንበያ ባስቀመጠው መሠረት የሌሎቹን ከተሞች ዕለታዊ የሙቀት መጠን መረጃ በድግሪ ሴልሺየስ ከምስሉ ላይ ይመልከቱ።

         መልካም ቀን ይሁንልዎ
• @ThinkAbyssinia •
7.6K views03:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 22:54:13
ሲንቄ ባንክ አዲሱን ብራንድ በይፋ በማስተዋወቅ የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

ከሌሎች የሀገር ውስጥ ባንኮች በተሻለ መልኩ በ15 ቢሊየን ብር የተመዘገበና 7 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር የተከፈለ ካፒታል ይዞ የሀገሪቱን የባንክ ኢንዱስትሪ የተቀላቀለው ሲንቄ ባንክ የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በመግለጽ አዲሱን ብራንድ በይፋ አስተዋውቋል።

 ባንኩ የማይክሮ ፋይናንስ አገልግሎት ይሰጡ ከነበሩ 405 ቅርንጫፎቹ ውስጥ 250 ለሚሆኑት ቅርንጫፎቹ የባንክ አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ ያገኘ ሲሆን ቀሪዎቹ 155 ቅርንጫፎቹ ደግሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ባንክ ቅርንጫፍነት የሚሸጋገሩበት ስራ በሰፊው እየተከናወነ እንደሚገኝም ተነግሯል።

• @ThinkAbyssinia •
8.8K views19:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 20:44:22
#ልክ_በዛሬዋ_ቀን

ታሪክን የኋሊት ልክ በዛሬዋ ቀን ኢትዮጵያ ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚውል ገንዘብ ከውጪ ባንክ ተበደረች

ከ 62 ዓመት በፊት መስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም ልክ በዛሬዋ ዕለት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት የሥራ ሚኒስትር ከአሜሪካ ጉዟቸው ሲመለሱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁለት ቦይንግ (Boeing 720B) ጄት አውሮፕላኖች ለመግዣ እና ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚውል ከ (EXIM)Export Import Bank) ጋር የብድር የስምምነት ውል የተፈራረሙት ዕለት ነበር።

የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንዲገነባ ካስፈለገበት ምክንያት አንዱ አየር መንገዱ ከነበሩት አውሮፕላኖች በተሻለ መልኩ ለማዘመን ታስቦ ነበር። ነገር ግን በወቅቱ የነበረው ነባሩ የልደታ አውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ለሚገዙት Boeing 720B ጄት ኦፕሬሽን ምቹ ባለመሆኑ ማለትም ረጅም ማኮብኮቢያ የሚጠይቅ በመሆኑ ዋና መስሪያ ቤቱ ሙሉ በሙሉ በአዲስ መልኩ የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ላይ እንዲገነባ አድርጓል።

• @ThinkAbyssinia •
9.6K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 20:25:54
የኮሚሽኑን ሪፖርት መሰረት በማድረግ በትግራይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈፅሟል ሳይባል በመቅረቱ ሕወሃት ቅሬታውን ገለፀ

ሕወሃት ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ የተመድ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት የገለጻቸውን በትግራይ ላይ የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች "የዘር ማጥፋት ወንጀል ብሎ ሳይፈርጃቸው ቀርቷል' ሲል ቅሬታውን ገልጧል። "አሁን ለኮሚሽኑ አስፈላጊ ማስረጃዎችን ለመስጠት ነባራዊ ሁኔታዎች አልፈቀዱልኝም" ያለው ሕወሃት፣ በአጎራባች ክልሎች ወንጀሎችን የፈጸሙ ታጣቂዎቼን ግን ተጠያቂ አደርጋለሁ ብሏል።

የተመድ መርማሪ ኮሚሽን የተመድ ድርጅቶች ሁሉ በእጃቸው ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ማስረጃዎችን እንዲሰጡት እንዲጠይቅ ያሳሰበው ሕወሃት፣ የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤትም መርማሪ ኮሚሽኑ ትግራይ ገብቶ ምርመራ ማድረግ እንዲችል በመንግሥት ላይ ተጽዕኖ እንዲያርግ ጠይቋል።

wazema
• @ThinkAbyssinia •
9.2K views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ