Get Mystery Box with random crypto!

Think Abyssinia

የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia T
የቴሌግራም ቻናል አርማ thinkabyssinia — Think Abyssinia
የሰርጥ አድራሻ: @thinkabyssinia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 157
የሰርጥ መግለጫ

➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የምሁራን እይታዎችና መጽሐፈቶች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ ➥ @Contact_Thinkabyssinia

🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-09-22 18:36:54 #ቲንክአቢሲኒያ_የመክሰስ_መረጃዎች

1፤የጉሙዝ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ፓርቲ  የታጠቁ ወጣቶች ወደ ሰላም መንገድ እንዲመጡ ጠየቀ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚንቀሳቀሰው የጉሙዝ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ፓርቲ በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመጡ ጥሪ ማቅረቡን ዶቼቬሌ ዘግቧል። የፓርቲው ሊቀ መንበር ታጣቂዎቹ እና መንግሥት እርቅ ካደረጉበት ካለፈው ከመጋቢት ወር ጀምሮ በካማሺ እና መተከል ሰላም መፈጠሩን ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል።

2፤አቶ ደመቀ መኮንን ከአረብ ኢምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአረብ ኢሚሬትስ የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ሼክ አብደላህ ቢን ዛይድ ቢን ሱልጣን አል ናያን ጋር በኒዉዮርክ ተገናኝተው መወያየታውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በወቅቱም የጋራ ተጠቃሚነትን የበለጠ ለማጠናከር ግንኙነታቸውን ማሳደግ እንዳለባቸው ሚኒስትቴሮቹ ተወያይተዋል።

3፤ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን በመሰረተ ልማት ግንባታና የምጣኔ ሃብት ትስስር በጋራ ለመስራት ተስማሙ።

የደቡብ ሱዳን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ታባን ዴንግ ጋይ የተመራው ልዑክ ከኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ጋር በሁሉቱ ሀገራት የመሰረተ ልማት ዝርጋታና ተጠቃሚነት ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ውይይቱን በማስመልከት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ሁለቱ አገሮች በተለይም የመሰረተ ልማት ዝርጋታና ተጠቃሚነት ዙሪያ በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ምክክር ማድረጋቸውን ገልጸዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

4፤የኤርትራ ወታደሮች ወደ ትግራይ ገብተዋል መባሉ ግጭቱን የበለጠ እንዲባባስ ያደርጋል ሲል የአውሮፓ ሕብረት አሳሰበ።

የኤርትራ ወታደሮች በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ወደ ትግራይ ገብተዋል መባሉ ግጭቱን የበለጠ እንዲባባስ ያደርጋል ሲል የአውሮፓ ሕብረት አስቧል። የሕብረቱ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ቦሬል ሁሉም ተፋላሚ ኃይሎች ማንኛውንም ወታደራዊ መፍትሄ ወደ ጎን በመተው ለሕዝቦቻቸው ጥቅም ሲሉ ወደ ሰላም ጥረት እንዲመጡ ሕብረቱ በድጋሚ ያሳስባል ብለዋል።

5፤ዛሬ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካን ዶላር በ52 ብር ከ5609 ሳንቲም ሲገዛ ውሏል።

እንዲሁም መሸጫ ዋጋው 53 ብር ከ6121 ሳንቲም መሆኑን ከድረገጹ ተመልክተናል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋው 56 ብር ከ9269 ሳንቲም እንዲሁም መሸጫው 58 ብር ከ0654 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ52 ብር ከ1562 ሳንቲም እየተገዛ በ53 ብር ከ1993 ሳንቲም የተሸጠ ሲሆን፣ አንድ የቻይና ዩዋን ደግሞ በ6 ብር ከ7499 ሳንቲም ተገዝቶ በ6 ብር ከ8849 ሳንቲም ሲሸጥ እንደነበር ቲንክአቢሲኒያ ተመልክቷል።

6፤የሊባኖስ ባንኮች ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቆሙ።

የሊባኖስ ባንኮች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች አስፈላጊውን ጥበቃ አላደረጉልንም በሚል ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ የአገሪቱ ባንኮች ማኅበር መግለፁን ቢቢሲ ዘግቧል። ደንበኞች ባለፈው ሳምንት እንዳይንቀሳቀስ የተደረገውን የቁጠባ ሂሳባቸውን ለማግኘት በኃይል ታግዘው ገንዘባቸውን የመውሰድ ድርጊቶች መበራከታቸውን ተከትሎ ነው የሊባኖስ ባንኮች ማኅበር አገልግሎት መቆሙን ያስታወቀው።

7፤ብሔራዊ ቡድኑ የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታውን በአቻ ውጤት አጠናቀቀ።

በአፍሪካ ከ23 ዓመት በታች ዋንጫ ማጣርያ ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዛሬ በአበበ በቂላ ስታዲየም ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ባደረገው የማጣሪያ ጨዋታ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይቷል። ብሔራዊ ቡድኑ የመልስ ጨዋታውን መስከረም 27 ቀን 2015 ዓ.ም በኪንሻሳ ያደርጋል።

• @ThinkAbyssinia •
9.6K views15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 17:52:14
#Update

ፍርድ ቤቱ በዘመነ ካሴ ላይ ለፖሊስ የ10 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ሰጠ

ትላንትና በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር የዋለው ዘመነ ካሴ ፍርድ ቤት ቀርቦ የአስር ቀናት ቀጠሮ የተሰጠው ሲሆን ምርመራውን የያዘው የክልሉ ፖሊስ ዘመነ ካሴን "ህገ ወጥ ቡድን በማደራጀት እና "ኬላ ዘርግቶ ገንዘብ በመሰብሰብ" እንዲሁም "በፌስ ቡክ ቅስቀሳ ማድረግ" በሚሉ ወንጀሎች ጠርጥሬዋለሁ በማለት ለፍርድ ቤቱ ማስረዳቱን አዲስ ዘይቤ ዘግባለች።

• @ThinkAbyssinia •
9.4K views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 16:42:00
ሩሲያና ቻይናን ጨምር በርካታ ሀገራት የኮሚሽኑን ሪፖርት እንደማይቀበሉት ገለጹ

የተመድ የሰብዓዊ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት በ11ኛ ቀን ውሎው በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ መብት ሁኔታ እንዲያጣራ ያቋቋመውን የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት የባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርትን ያደመጠ ሲሆን በርካታ ሀገራት የኮሚሽን ሪፖርት እንደማይቀበሉት ገልፀዋል።

በስብሰባው ላይ የተሳተፉ በርካታ ሀገራት ሪፖርቱ ገለልተኛ አይደለም እንዲሁም ፖለቲካዊ አንድምታ የያዘ ነው ሲሉ አጣጥለውታል። ሪፖርቱን ከተቃወሙ ሀገራት መካከል፤ ቻይና፣ ሩሲያ፣ ኩባ፣ ቤላሩስ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ቬንዙዌላ እንዲሁም የአፍሪካ ሀገራት ይገኙበታል።

• @ThinkAbyssinia •
10.0K views13:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 15:06:51
ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ለአፍሪማ የሙዚቃ ውድድር  ታጨ

ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) እና ሔዋን ገብረወልድን ጨምሮ ስድስት የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች በየዓመቱ በሚካሄደው የመላው አፍሪካ የሙዚቃ ሽልማት (አፍሪማ) ላይ እጩ መሆናቸው ታውቋል። ቴዲ አፍሮ ከጥቂት ወራት በፊት የለቀቀው ‘ናዕት‘ የተሰኘው ነጠላ ዜማ በአፍሪማ አዋርድ በአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ የሬጌ እና ዳንስሆል ሙዚቃ ዘርፍ ታጭቷል።

በተጨማሪም ድምፃዊት ቤቲ ጂ በ‘አዲስ ሰማይ’ ፤ ድምፃዊት ሔዋን ገብረወልድ በ‘ሼሙና’ ፤ ድምፃዊ አዲስ ለገሰ በ‘እንጃ’ ስራዎቻቸው በተለያዩ ዘርፎች ለአፍሪማ የታጩ ሲሆን ለእጩ ድምፃውያን በኦንላይን ድምፅ መስጠት የሚቻልበት ስርዓት እሁድ መስከረም 15 እንደሚጀምርም ተገልጿል።

• @ThinkAbyssinia •
10.5K views12:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 13:05:47
ሠሞኑን የዶላር ምንዛሪ ባልተጠበቀ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ ጭማሪ ማሳየቱ ተነገረ

የውጭ ምንዛሪ ፍላጎት በመጨመሩ የጥቁር ገበያ ግብይት በሚካሄድባቸው አንዳንድ የከተማዋ አካባቢዎች በሳምንቱ አንድ የአሜሪካ ዶላር ከ90 እስከ 92 ብር ይሸጥ ነበር ያለው ካፒታል ጋዜጣ ይህ ከመደበኛው የምንዛሪ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር ከ70 እስከ 75 በመቶ ልዩነት ነበረው ብሏል።

በተለይ መኪና የሚያስገቡ አስመጪዎች አንድ የአሜሪካ ዶላር እስከ 100 የኢትዮጵያ ብር እየገዙ መሆኑና በባንኮች ካለው ምንዛሪ ልዩነት እስከ 90 % እንደሚደርስ አመልክቷል። መንግስት የጥቁር ገበያን የምንዛሪ ልውውጥ ለመቆጣጠር እየታገለ ሲሆን ጥረቱ ግን የተሳካ አይመስልም ሲል ካፒታል ጋዜጣ አስነብቧል።

• @ThinkAbyssinia •
10.7K views10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 15:01:39
በብልሹ አሰራር ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቁሞ የነበረው የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ መሬት እና  ልማት አስተዳደር ጽህፈት ቤት በዛሬው እለት ስራ ጀመረ

በአዲስ አበባ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ መሬት እና  ልማት አስተዳደር ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች እና አመራሮች ህብረተሰቡን ጎንበስ ብለው ይቅርታ በመጠየቅ ያለምንም መማለጃ እና ጉቦ በቅንነት እና በተቀላጠፈ አሰራር ለመካስ ቃል ገብተው ዛሬ ስራ መጀመራቸውን የጽህፈት ቤቱ ምክትል አስተዳደር አቶ ሀብታሙ ዋናያ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

• @ThinkAbyssinia •
928 views12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 14:01:04
ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ምርጫውን ራይላ ኦዲንጋ ባለማሸነፋቸው ማዘናቸውን ገለጹ

የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ሥልጣናቸውን ለቀጣዩ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በደስታ እንደሚያስረክቡ ቢናገሩም የመረጧቸው ተተኪ ራይላ ኦዲንጋ አገሪቱን ለመምራት የተሻሉ ነበሩ ብለዋል። ለኔ መሪዬ ባባ ናቸው።" ሲሉ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ራይላ ኦዲንጋን በቅፅል ስማቸው በመጥራት አሞካሽተዋቸዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

አክለውም “ አገሪቱን ወደ አንድነት ለማምጣት የነበረውን ዕድል ነው የተከላከላችሁት እንጂ ራይላን አይደለም የከለከላችሁት” በማለት በምርጫው ውጤት የተሰማቸውን ኃዘን ገልጸዋል። ተመራጩ የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በምርጫ ማሸነፌን ተከትሎ እንኳን ደስ ያለዎት አላሉኝም ሲሉ መናገራቸውም ይታወሳል።

• @ThinkAbyssinia •
2.8K views11:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 12:05:58
አፕል ከሳተላይት ጋር መገናኘት የሚያስችለውን አይፎን 14 ስልኩን ይፋ አደረገ

አፕል ድንገተኛ የሳተላይት ግንኙነት እና የመኪና አደጋን የመለየት ቴክኖሎጂ የተገጠመለትን አይፎን 14ን በአሜሪካ በነበረው ዝግጅት ላይ ይፋ ማድረጉን ቢቢሲ ዘግቧል። ኩባንያው አራት አይነት የአይፎን 14 አዳዲስ ስልኮቹን ነው ያስተዋወቀው። በዚህ ዝግጅት ላይ በቴክኖሎጂ የላቁትን ቀጣዮቹን የአይፎን ስልኮች፣ ሰዓት እንዲሁም የማዳመጫ ምርቶቹን አሳይቷል።

ኩባንያው መጠናቸው የተለያየ አይፎን 14 እና አይፎን 14 ፕላስን ለገበያ ይቀርባሉ ብሏል። አዲሶቹ የተንቀሳቃሽ ስልኮች የአደጋ ጊዜ ጥሪ በሳተላይት መላክ የሚችሉ ናቸው። ስልኮቹ የሚያልፉ ሳተላይቶች የት እንዳሉ የሚያሳዩ ሲሆን በነሱም ላይ እንዴት በትክክል መጠቆም እንደሚቻል የሚያሳይ ቴክኖሎጂ ተገጥሞላቸዋል።

• @ThinkAbyssinia •
4.8K views09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 11:19:16
ከዑራዔል ወደ ወሎ ሰፈር የሚወስደው መንገድ “የሰላም ጎዳና” ተብሎ ተሰየመ

በዛሬው ዕለት የሰላም ቀንን በማስመልከት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዑራዔል ወደ ወሎ ሰፈር የሚወስደውን አዲስ መንገድ “የሰላም ጎዳና” በሚል ተሰይሟል፡፡

• @ThinkAbyssinia •
5.3K views08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 10:31:45 #ቲንክአቢሲኒያ_የቡናቁርስ_መረጃዎች

1፤ታላቁ የኅዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 60 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተባለ።

የታላቁ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ሲሆን በጉባኤው ላይ ተገኝተው የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ያቀረቡት ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 88 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው ፕሮጀክቱን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 60 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

2፤በኢትዮጵያ የመጀመርያ የሆነው የሰላም ፖል በአዲስ አበባ ይፋ ሆነ።

ዛሬ ጳጉሜ 3 እየተከበረ ያለውን የሰላም ቀንን ምክንያት በማድረግ የሰላም ፖሉን ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱአለም በተገኙበት ይፋ ሆኗል። በስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ሰንደቅአላማ የመስቀል ስነስርዓትም ተከናውኗል።

3፤ኢትዮጵያና ጂቡቲ ድንበራቸውን ከየትኛውም የሽብር እና ከሌሎች የወንጀል ተግባራት የማጽዳት ሥራ በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን አስታወቁ።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የጅቡቲ ብሔራዊ ፖሊስ ከዚህ ቀደም ድንበር ዘለል ወንጀሎችን በጋራ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው የሚታወስ ሲሆን በዚህም መሠረት የሁለቱ ሀገራት ፖሊስ ተቋማት የጋራ የፀጥታ ግብረ ኃይል በማቋቋም በድንበር አካባቢ የጋራ ጥበቃ በማድረግ የጀመሩትን ተግባራት ገምግመዋል። እስከአሁን የተገኙ ውጤቶችን አጠናክረው ለማስቀጠልም ተስማምተዋል።

4፤የኬንያው አዲሱ ተመራጭ ፕሬዝዳንት ለበዓለ ሲመታቸው ኢትዮጵያ ጨምሮ ከ40 በላይ ለሚሆኑ የአገራት መሪዎች ጥሪ አደረጉ።

የኬንያው ተመራጭ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ለበዓለ ሲመታቸው ከ40 በላይ የአገራት መሪዎችን እንደጋበዙ ደይሊ ኔሽን ዘግቧል። በበዓለ ሲመቱ ላይ እንዲገኙ ከተጋበዙት መካከል፣ የኢትዮጵያ፣ ኡጋንዳ፣ ናይጀሪያ፣ ጋና፣ ደቡብ አፍሪካና ግብጽ መሪዎች ይገኙበታል። ሩቶ በመጭው ማክሰኞ በናይሮቢ በሚካሄድ ስነ ሥርዓት የኬንያ 5ኛው ፕሬዝዳንት በመሆን መንበረ ሥልጣኑን ከፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ይረከባሉ።

5፤ግሪክ የቱርክ ዛቻ ስጋት ፈጥሮብኛል ስትል ለኔቶ እና ለተመድ ደብዳቤ ላከች።

ሰሞኑን የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ግሪክ በኤጂያን የአየር ክልል ላይ በሚንቀሳቀሱት የቱርክ አውሮፕላኖች ላይ የምትፈጥርው “የማስጨነቅ ድረጊት” የማታቆም ከሆነ አጻፋው ከባድ እንደሚሆን ማስጠንቀቃቸው የሚታወስ ሲሆን የፕሬዝዳንቱ ዛቻ ስጋት ውስጥ የከተታት አቴንስም እየደረሰብኝ ያለው ዛቻ ስጋት ፈጥሮብኛል ስትል ዓለም የአንካራን ባህሪ እንዲያወግዝ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለኔቶ እና ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት መላኳን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

6፤በሐረሪ ክልል የሰላም ቀንን በማስመልከት የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር ተካሄደ።

“ሰላም ለኢትዮዽያ” በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው የአምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር የክልሉ ነዋሪዎች፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የመንግስት ሰራተኞች፣ የጸጥታ አካላት፣ ወጣቶች፣ አትሌቶችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈውበታል። ለውድድሩ አሸናፊዎች የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ የሜዳሊያ ሽልማት አበርክተዋል።

• @ThinkAbyssinia •
5.6K viewsedited  07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ