የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
5.64K
የሰርጥ መግለጫ
ጥቆማ‼️
በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ፣ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ፈጣሪ ይባርክ
ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ
በውስጥ መስመር ከፈለጉን 👉 @Sulamen14
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
3
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-08-30 23:50:22
የቻይና ወታደሮች ለጋራ ወታደራዊ ልምምድ ሩሲያ ገቡ
በዚህ ሳምንት ሩሲያ በሚካሄደው የቮስቶክ 2022 ስትራቴጂካዊ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ የሚሳተፉ አገራት ወታደራዊ ቡድኖች ወደ ሩሲያ መድረሳቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ሰኞ ዕለት አስታውቋል።
ከሩሲያ ጦር ኃይሎች በተጨማሪ የቻይና, ቤላሩስ, አዘርባጃን, አርሜኒያ, ሶሪያ, ህንድ እና ሌሎች ተባባሪ አገራት ወታደሮች ይሳተፋሉ፡፡
በልምምዱ ከ50,000 በላይ ወታደሮች እና ከ5,000 በላይ የጦር መሳሪያዎች የሚያካትት ሲሆን 140 አውሮፕላኖች እና 60 የጦር መርከቦች, ጀልባዎች እና የድጋፍ መርከቦች በልምምዱ ይሳተፋሉ፡፡
ቮስቶክ-2022 የሚካሄደው እ.ኤ.አ በ1996 ሩሲያ፣ ካዛክስታን፣ ኪርጊስታን፣ ታጂኪስታን እና ቻይና በወታደራዊ ዘርፍ ያላቸውን በራስ መተማመን ለማሳደግ በገቡት ስምምነት መሰረት ነው፡፡
ANN
በቴሌግራም ይከተሉኝ
https://t.me/SuleimanAbdellaNews14
ሱሌማን አብደላ
411 views20:50
2022-08-30 23:37:01
ለጥንቃቄ ያህል ነው፥
ወልዲያ ከምሽት 1:20 ጀምሮ መብራት ጠፍቷል። መብራት የጠፋው ከደሴ ወደ ወልዲያ ኤሌክትሪክ የሚያስተላልፈው ከፍተኛ ተሸካሚ ችግር ስላጋጠመው እንጅ በሌላ ነገር አይደለም። መብራቱን ለማስተካከል ባለሙያወች እየታገሉ እንደሆነ ሰምተናል።በዩቲዩብና በተለያዩ የፌስቡክ ገፆች ብዙ ወሬ እየተወራ ስለሆነ ትክክለኛው ነገር ይህ መሆኑ ታውቆ ለወዳጅ ቤተሰብ እንዳይረበሹ ብለን ነው። በተረፈ መከላከያ ስራዊቱን ልዩ ሀይሉን ፋኖዉን እናግዝ። እንተባበር፣ መከራው ይበዛ ይሆናል እንጅ በርግጠኝነት ግን ኢትዮዽያ ታሸንፋለች
ሱሌማን አብደላ
516 viewsedited 20:37
2022-08-29 22:20:55
ሱዳን ያለው የኢትዮዽያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ የህወሓትን ማንነተና የኢትዮዽያን ፍላጎት ሱዳን የሚገኙ አለማቀፍ ሚዲያዎችን ጠርቶ አብራርቶላቸዋል። ትክክለኛ ስራ ማለት ይሄ ነው።
ሱሌማን አብደላ
2.4K viewsedited 19:20
2022-08-29 08:57:58
ይቺን ጥሬ ሀቅ መንግስት ይቀበላት። አገራችን በደሀ መቀነቷ በዶላር የምትከፍላቸው ዲፕሎማቶችን በተመለከተ አቶ ነአማን ዘለቀ የፃፈው ጥሬ ሀቅ አለ። ለሀገራቸው 24 ሰአት የሚሰሩ ትንሽ ዲፕሎማቶች አሉ። በዛው ልክም ግን ስራቸውን ትተው ለመንግሥት እያሸበሸቡ አገር አደጋ ላይ ወድቀው የጦፈ ንግድ ውስጥ ያሉ ዲፕሎማቶች አሉ። ምናልባት በጉዳዮ ዙሪያ መንግስት አስቸኳይ የማስተካከል ስራ ከሰራ ብለን ነው የለጠፍነው።
በጉዳዩ ዙሪያ ይህ አሰራርና ኋላቀር አመለካከት እንዲቀየር ኢትዮጵያን የሚመጥን ተቋምና አሰራር እንዲፈጠር የመጀመሪያ ትግላችን የምናደርግበት ግዜ ቅርብ ነው።
Redwan Hussien
Demeke Mekonnen Hassen
Ethiopian Diasporaagency
Mohammed A. Endris
Birtukan Ayano Dadi
ሱሌማን አብደላ
2.9K viewsedited 05:57
2022-08-28 23:14:56
ቆቦን መልሰን መቆጣጠራችን ድላችን አይደለም፣ ድላችን ይህ አረመኔ ቡዳን ላንደየና ለመጨረሻ ግዜ ታሪክ ሆኖ ማየት ነው። ትናንት እንዳልኳችሁ በትንሽ ነገር አንቧርቅም። በትንሽ ነገርማ ኡኡታን አናቀልጥም። በርግጥ በዚህ ሰሞን አለምን ያስገረመ ነገር አብረን እንሰማለን። ይህ የመከላከያ ሀይሉን አሰላለፍና አዘገጃጀት በትንሹ መረጃ ስላለን ኮርተን የምንናገረው ሀቅ ነው። ለማንኛውም የውነት ሞት ለምትሞቱልን የኢትዮጵያ ሀይሎች ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው። ድልና ድምቀት ለናተ ይሁን።
ሱሌማን አብደላ
3.0K viewsedited 20:14
2022-08-28 22:08:19
አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የመከላከያ ሀይላችን ዋነኛ አላማ ወራሪውን ሀይል ራያ ላይ መቁረጥ አይደለም ። ከዚያ ይልቅ መከላከያ ሀይላችን ወራሪውን ሀይል ከኤርትራ በኩል ቆርጦ አጠቃላይ ትግራይን ከህወሀት ለማፅዳት የተራቀቀ እቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው ተብሏል ።
ከዚህ በተጨማሪ ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን ከሁመራ አቅጣጫ ከማይጠብሪ አቅጣጫ ወደ ማጥቃት እንደሚገባና የወራሪውን አማተር ሰራዊት ሳንዱች ለማድረግ እየተጣደፈ ይገኛል ።
ህወሀት ከወሎ ብቻ ሳይሆን ከትግራይም የሚፀዳበት ጊዜ በጣም የተቃረበ ይመስላል ። በዚህ ዘመቻ መከላከያ ሀይላችን ከመቀሌ ያነሰ ኢላማ የለውም ።
ኢትዮጵያ ታሸንፋለች !
በቴሌግራም ይከተሉኝ
https://t.me/SuleimanAbdellaNews14
ሱሌማን አብደላ
3.1K viewsedited 19:08
2022-08-28 17:49:59
ጀግናው ሁሉንም ሰማን ከበባውን ሰብሮ ታሪክ ሰርቷል።
ምሬ ወዳጆ በሮቢት የቃሊም ተራራ ምስክር ናት።
ጥምር ጦሩን ደግፉ መዘናጋት እንዳይኖር።
3.4K viewsedited 14:49
2022-08-28 17:24:54
አፋሮች ዛሬ የማረኩት ነው።
3.4K viewsedited 14:24
2022-08-28 12:20:40
ክንድ ተፈጥሮ ሰራሽ እጅ ነው። ተሰብሮ ይታረቃል፣ መልሶ ጠንካራ ክንድ ይሆናል። ለምን እንዲህ ሆንክ አይባልም። ሰትሮጥ መውደቅ አለ። መልሶ ተንስቶ መቆም አለ። የስራ ሰው እንሁን፣ እናግዝ ህወሓት የ11 አመት ልጅ አሰልፎ ነው የሚዋጋን።
ሱሌማን አብደላ
3.4K viewsedited 09:20
2022-08-28 09:32:15
ዋልድባ
አሸባሪዉ የህወሃት ቡድን አለም በቃኝ ብለዉ በዋልድባ ገዳም የሚገኙ የበቁ አባቶች ላይ ስቃንና እንግልት መፈፀሙንና ገዳሙን መዝረፉን ቀጥሏል ።
በትላንትናው እለት ወደ ገዳሙ በመግባት በርካታ ንዋያተ ቅድሳን ከመዝረፍ በተጨማሪ ስዕል አድኖዎችን ማቃጠላቸዉን አባቶችን ባገኙት ነገር መደብደባቸዉን ክብረ ነክ ድርጊቶችን መፈፀማቸዉን ከስፍራው ባገኘነው መረጃ ለማረጋገጥ ችለናል ።
ይህ ገዳም በጣም ሰፊ ሲሆን የአራቱ ገዳማት መገኛ ከሆኑ ከሰንሰለታማ ተራሮች በጀርባ በኩል ባሉ ተራሮች የሚመጣዉ የህወሃት ቡድን በተደጋጋሚ እያጠቃዉ ይገኛል ።
በቴሌግራም ይከተሉኝ
https://t.me/SuleimanAbdellaNews14
ሱሌማን አብደላ
3.4K views06:32