Get Mystery Box with random crypto!

ቀለማት

የቴሌግራም ቻናል አርማ qelemaat — ቀለማት
የቴሌግራም ቻናል አርማ qelemaat — ቀለማት
የሰርጥ አድራሻ: @qelemaat
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 27.43K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል ሀገርኛ ቀለም ያላቸው ስነ ልቦናዊ ረጢብ ስንቆች፣ ከህይወት ሰበዝ የተመዘዙ ጎምቱ ልምዶች፣ በአስተውሎት የጎለመሱ ሰብዓዊ ሃሳቦች፣ የህይወት ክህሎት ስልጠናዎች እንዲሁም ስነ ልቦናዊ ምክክሮች በድምፅ እና በጹሑፍ ወደ እናንተ የሚቀርቡበት የእናንተው ቀለመ-ብዙ ቻናል ነው !
Addis Ababa, Ethiopia

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-05-09 19:38:08 To Do List የንባብ ልምዳችሁ እንዳይቀንሰው እፈራለሁ ፣ በራሳችሁ ተሰፋ እየቆረጣችሁ ያላችሁት በዚህ ምክንያት ይሆን? የተሻለ መፍትሄ :-

https://vm.tiktok.com/ZM2162WgE/
2.4K viewsቻLu, 16:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-04 19:51:57 መጓዝ የሚመስል አቋቋም ቆመን ይሆን

Written by: Getachew. M

“ሲጀመር የሌለህን ነገር ምን እንዳይሆን ብለህ ነው የምጠብቀው? ከማንስ ነው የምጠብቀው?" መልሳ ለጥያቄየ ጥያቄ አነሳችልኝ። “አንዳንዴ እራሳችንን ለመከላከል ብለን ማንም ከጀርባ መጥቶ ሳይጥለን በራሳችን ጥላ የምንወድቅበት ጊዜ አለ!" አለችኝ።

“እኔ አሁን በዚህ ሰዓት፣ በዚች ቅጽበት የምፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው ነኒ፤....... ሰላም! የት ጋር እንዳለሁ፣ የት ደርሸ እንደቆምኩ፣ የቱ ጋር እንደጠመምኩ ማወቅ ነው የምፈልገው። ልክ አዲስ አበባን ሙሉ ገጽታዋን በቴሌስኮፕ ለማዬት እንጦጦ እንደ ሚወጣው የኔንም ፍርስራሽ ገጽታ ለማዬት የሆነ ከፍታ ላይ መውጣት ብችል ብዬ ነው የምመኘው" አሁን ግን አዲስ አበባ(እኔ) ውስጥ ካለ አንዱ ፍርስራሽ ሰፈር(አሁን ላይ እኔ) ውስጥ ነኝ እና አዲስ አበባን(እኔን) እያየኋት አይደለም። አንዳንዴ ራሳችንን ከራሳችን ወጥተን ከፍ ብለን ማዬት ብንችል እናውቀው ይሆን? እላለሁ።" ቀጠል አድርጌ “መረጃ የሚሰጠኝ ሰው አይደለም ደግሞ የምፈልገው፤... መንገድ የሚያሳየኝ፣ ከዚህ ጨለማ እጀን ይዞ የሚያወጣኝን አካል ነው የምፈልገው።" አልኳት ጠንከር ብዬ።

“አንተ ሰዎችን አይተህ እንዲሁ በማየት ብቻ ማንነታቸውን፣ ያሳለፉትን ህይወት፣ አሁን ላይ ምን እያሰቡ ምን እየተሰማቸው እንደሆነ ማወቅ ትችላለህ? መገመት አላልኩም።"

“አልችልም!" መለስኩላት። የምርም አልችልም።

“ስለዚህ ራስህን ልታውቀው ከፈለግህ እንጦጦ ወጥተህ ሳይሆን እዚህ 6 ኪሎ ግቢ (አሁን ላይ እኔ) ውስጥ ሆነህ ብትፈልገው ነው የተሻለ ልታውቀው የምትችለው። ስለዚህ ልክ ነው። ውስጥ መግባት እንፈራለን ግን ልክ ነው ብዬ አምናለሁ" አለችኝ።

“እዚህ ሆኘ መፈለጌ እኔን ጨርሶ ለማወቅ ባይበቃስ?" ጠየኳት።

“በመጀመሪያ ጨርሶ ማወቅ እንዴት ያለ ነው? ይሁን እንኳን ብንል ጨርሶ ማወቁን በምን ያውቃል ሰው? ጨርሶ ማወቅ ሚባል ነገር የለም። እዚህ ጋ ጨርሶ ስለማወቅ አይደለም ቁም ነገሩ። የተሻለ ስለማወቅ ነው።
አዲስ አበባ ኮ አስራ አንድ ክፍለ ከተሞች ነው ያሏት። ስድስት ኪሎ ቁጭ ብሎ አዲስ አበባን አውቃታለሁ ማለት የለም። እንደምታዬው (በእጇ ከድንጋይ ወደ ተሰራው የአንበሳ ቅርጽ እየጠቆመችኝ) ስድስት ኪሎ ስትሆን አንበሳ ግቢን ታውቃለህ፤ አራት ኪሎ ወረድ ብትል ደግሞ ፒኮክን ታያለህ (የሹፈት ሳቋን እየሳቀች)። “ምን ልልህ ነው እንጦጦ ላይ ሆኖ ማዬት አይደለም ቁም ነገሩ። ይሄን ከውጭ የመጣ እንግዳም ያደርገዋል። እዛ ሆኖ ስላያት ከተማዋን ያውቃታል ማለት አይደለም። ማወቅ ከፈለገ ከተማው ውስጥ መግባትና መኖር አለበት።" ምናምን ብላ ልታስረዳኝ ሞከረች።

“አሁን የምትይው ኮ ይገባኛል። እኔ የምለው ነው እማይገባሽ ነኒ። አሁን አዲስ አበባ ምናምን ብሎ ምሳሌ ማምጣት ምን ሚሉት ነው" ከልቤ ነበር ይሄን ያልኳት። (ሰው የፈለገ ሊረዳችሁ ቢሞክር የማይረዳላችሁ የሆነ ክፍል አለ።) (አንድ የልቡን ያጣ ሰው ግን ምን አግኝቶ ይደሰታል? አንዳንዴ ከቤት ወጥቶ የማያውቅን ሰው መንገድ አሳየን ብላችሁ አትጠይቁት። ጭሱን ከጠላችሁት እናንተ ራሳችሁ ከኩሽናው ውጡ።)

“ልክ ነህ።" አለችኝ ራሷን እየወዘወዘች።

“ከቅድሙ አሁን የተረዳችኝ መሰለኝ።"

“ለምን ለአሉታዊ ሃሳቦች የቀረብክ ይመስልሃል? አስበኸው ታውቃለህ?" ጠየቀችኝ።

“እናንተም ታዝዛችሁ ከሆነ ታስታውሻለሽ... ‘ኢለመንተሪ' እያለን የሳይንስ አስተማሪያችን የሆነ እጽዋት አብቅሉና የፀሀይ ብርሃን በሌለበት ቦታ አስቀምጡት ተብለን የሰራነው experiment ነበር... ያ እጽዋት ከበቀለ በኋላ እንደምንም የፀሀይ ብርሃን ወዳለበት አቅጣጫ ተጣሞ ያድጋል፤ አሊያ ይሞታል። ለምን ተጣመመ አይባልም...ከመጣመም ውጭ ያለው አማራጭ መሞት ነዋ። የሰው ልጅ ህይወት ላይም ተመሳሳይ ነገር አለ። ሰው ትናንት ያላገኘውን ብርሃን ነገ ለማየት፣ በልጅነት የጎበጠ እድገቱን ለማቅናት ሁልጊዜ ምርጫ ላይኖረው ይችላል። አየሽ ብርሃን ለማግኘትም ተጣሞ ማደግ አለ። ምናልባት ይሄ ይሆናል ምክንያቴ አልኳት።

“ጌችዬ አንተ ኮ ተስፋ ያለህ ልጅ ነህ። ተመልከተው እስኪ ዙሪያህን... ያንተ መኖር ብቻ የሚያስደስታቸው ብዙ ሰዎች አሉ። ደግሞ ለመዳን ስትነሳ ቁስልህን ለማድረቅ አትሞክር፤ ዝም ብለህ ሽረቱን ኑረው። መልቀቅ ያቃተህ ብዙ ነገር እንዳለ ይሰማኛል። እስኪ ትተህ እየው ደሞ።" ማለት ስላለባት ሳይሆን የምርም እኔን ተረድታ ለመርዳት እየሞከረች ነበር። ደስ አለኝ።

“እሽ... አንችን ይዤ አያቅተኝ ይሆናል!" አልኳት። (እንደ ሰው ሰው ያስፈልገናል።)
“ብሉይ ታሪኬን ሳልጥል ወደ አዱሱ ፍስሃ የምሸጋገርበትን ኪዳን የሚጠቁመኝ ሰው ያስፈልገኛል....."

“Promise!" አለችኝ ቀድማ ፈቃድኝነቷን በፈገግታ እየገለጸችልኝ።

“አመሰግናለሁ ነኒ!" አልኳት። ተለያይተን ብሉይ ጥያቄየን እያወጣሁ እያወረድኩ ሳለሁ በመሃል... መጀመሪያ ላይ “ለውጥ ትፈራለህ ልበል?....። ንግግሮችህ መሃል መቆም ይታየኛል... በትናንት መታሰር። ለውጥም አልመለከትም። ራስህን ሌሎች ውስጥ እየፈለከው ነበር እንዴ ይሄን ሁሉ ጊዜ? ሰዎች ስላንተ የሚያስቡት ሙሉ ውሸት ነው። አንተ ያቆምከውን ጣኦት ነው ብዙ ጊዜ የሚያውቁት።" ያለችኝ አዕሞሮዬ ላይ ጫር አለብኝ። አሁን ጣፉ ተለኩሷል!

ለማት | ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ መድመቂያ ቀለም አለው!

Join us 
@qelemaat@qelemaat
4.0K viewsGech, edited  16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-04 19:03:50 የንባብ ልምድን ለማምጣት ስልችት የሚለን ሰዎች - Motivation እና Discipline በአንድ ላይ ተጠቅመን አንባቢ የሚያደርገን Study Tip እንሆ :-

https://vm.tiktok.com/ZMYEJA9yA/
3.3K viewsቻLu, 16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 23:23:05 Written by: Getachew.M
Reviewed by: lu.M

በአዕምሮ ማሰብ vs በብሶት ማሰብ

ሰው በብሶት ውስጥ ሲኖር በአዕምሮው ልክ ሳይሆን በብሶቱ ልክ ነው የሚያስበው። በአቅማችን ልክ ሳይሆን በብሶታችን ልክ የምናስብበት ብዙ ጊዜ አለ። ባለን ሳይሆን በጎደለን ነገር ብቻ ህይወት እና ዓለምን የምንዳኝበት ጊዜ። ይሄንን በትራንስፖርት ታሪፍ እንመስለውና ላሳያችሁ። አንድ ቦታ ተነስታችሁ ሌላ ቦታ ለመድረስ ሙሉ ታሪፉ 10 ብር ነው እንበል። እናንተ ግን የያዛችሁት 9 ብር ቢሆን መሳፈር ላትችሉ ነው (ልክ የ10 ብር ካርድ ተከራክረን 9 ብር መግዛት እንደማችለው)። ስለዚህ 9 ብር ኖሮን ግን በ1 ብር መጉደል ምክንያት ያሰብነው ቦታ ለመድረስ አልቻልንም። ሁሌም የምንረሳው ነገር.. ዘጠኝ ብር ስለሌለን አይደለም መሳፈር ያልቻልነው..፤ አንድ ብር ስለጎደለን ነው ። ህይወት ላይም ተመሳሳይ ነገር ነው የምናስተናግደው። ያሰብነው የህይወት ግብ ላይ መድረስ ያልቻልነው ምንም እውቀት፣ ምንም ልምድ ስለሌለን ላይሆን ይችላል። የጎደለን አንድ ነገር ነው ምናልባትም ያለንን ብዙ በዜሮ አባዝቶ በቁም ሽባ እንድንሆን ያረገን (በአዕምሯችን አስበን ካልተራመድን እግራችን የሚራመደው እርምጃ ደመነፍሳዊ ነው የትም አያደርሰንም.. ይሄንን እንስሳትም ያደርጉታል)።

አንድ ሰው ከፍቅረኛው ጋር ሲጣላ፣ ይመካበት የነበረውን ነገር ሲያጣ፣ ባመነው ሲካድ፣ ቤተሰቡን አሊያም ወዳጁን በሞት ሲያጣ ዓለም በሱ ላይ የተደፋችበት መስሎ ሊሰማው ይችላል። እንደዛ መሰማቱ ስህተት አይደለም.. ሰብዓዊነት ነው። ነገር ግን ያጣነው ነገር ብቻ አይደለም መጀመሪያ ላይ የነበረን። ችግሩ ያለው በሰዓቱ ያጣነው ነገር የነበረንን እና አሁን ላይ ያለንን ነገር እንዳናይ በእምባ ይከልለናል። ያኔ ነው እጃችን ላይ ባለው ማጣት የህይወትን ትርጉምና የዓለምን ፍትህ ልንዳኝ የፍርድ ሰገነት ላይ የምንወጣው። በከበባድ ውጥረቶች ውስጥ ስናልፍ የሚሰሙን ስሜቶች ልክ ናቸው። ግን ስሜቶችን ማወቅ እንጅ ማመን የለብንም። ሁልጊዜም ቢሆን ህይወት ትርፍ ስጦታ ይኖራታል። ያጣነውን ነገር ያጣነው በዛ ነገር እንድንማር፣ ጉድለታችንን እና ድካማችንን አውቀን እንድንሞላው እንዲሁም እንድንጠነክርበት እንጅ እንድንፈርስበት እና በዛ ቅንፍ ውስጥ ተቀንፈን በቅንፍ ውስጥ ሃሳባችን ስለነገሩ የተደመደመ ውሳኔ እንድንሰጥ አይደለም።

ለማት | ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ መድመቂያ ቀለም አለው!

Join us 
@qelemaat@qelemaat
4.2K viewsGech, edited  20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 23:18:09
3.2K viewsGech, 20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 06:00:18
እንደዚህ ተሰምቷችሁ ያውቃል
ከፍ ያላችሁ መስሏችሁ ግን ከመቼምውም ጊዜ በበለጠ ራሳችሁን ያጣችሁበት ጊዜ...። ሞልተነው ያልሄድን ሽንቁር ካለ እሱ ወደኋላ ይመልሰናል። እናንተን ወደኋላ የሚመልሳችሁ ምንድን ነው

መልካም ቀን

ለማት | ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ መድመቂያ ቀለም አለው!

Join us 
@qelemaat@qelemaat
3.7K viewsGech, 03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 17:35:35 አለመቀበልን መቀበል

Written by: Getachew - Promising Psychologist at AAU

ክፍል-2
....መሆንህን ስትቀበለው ደግሞ ሙሉ በሙሉ ነፃ ሰው ነህ። እየህ እስር የብረት ወይም የአጥር አሊያም የገመድ አይደለም። በራሳችን አስተሳሰብ እና እምነት ነው ከውስጣችን የታሰርነው" ዝም ብዬ በትኩረት ሆኘ እያደመጥኳት ነበር። ቀጥላም

“የሰው ልጅ በብዙ ምክንያቶች በከባባድ ስሜቶች ውስጥ ያልፋል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ራስን ካለመቀበል የሚመጡ የበታችነት ስሜቶች አሉ። እነዚህ ስሜቶች በጣም ገዳይ ናቸው። እንዳልኩህ በሌላ ጊዜ ደግሞ እውነትን ሽሽት ወጥተን የቆምንበት የእንቧይ ካብ ሲናድ የምንገባበት እናጣለን። መቆሚያ የለ መቀመጫ ሁሉንም እናጣለን። መቼም ሰውን እንዳይወድቅ ደግፎ የያዘው የጀርባ አጥንቱ ብቻ አይደለም። እንደዛ ብቻ ቢሆን አከርካሪው ምንም ሳይሆንበት ግን ራሱን ማጥፋት የሚፈልግ፣ ህይወት የሰለቸው፣ በሁለት እግሩ መቆም አቅቶት የሚንገዳገድ ብዙ ሽህ ሰው ዓለም ባልኖራት ነበር። ስለዚህ አካላዊ ስጋችን ራሱን ችሎ መቆምና መራመድ እንዲችል ሃይል የሚሰጠው ነገር ያስፈልገዋል። ልክ መኪና ለመንቀሳቀስ፣ አግልግሎትም ለመስጠት ነዳጅ እንደሚያስፈልገው"


“ወደ አነሳነው ሃሳብ ስመጣልህ.... ቆይ እንዳውም አንድ ምሳሌ እናንሳ.... ሁሉም ሰው ማህበረሰቡ ወይም የፋሽን ኢንዱስትሪው ያወጣውን የቁንጅና መስፈርት አሟልቶ አይገኝም። መስፈርቱ ምንም ይሁን ግን ቆንጅና ባለበት ሁሉ ፉንጋነትም አለ። ቁንጅና በሚወደስበት ፋንጋነትን አዕምኖ መቀበል ስነ ልቦናዊ ህመም አለው። ይሄም ‘ውበት ውስጣዊ ነው' የሚለውን ጥቅስ ሳይገባን ራሳችንን ለመከላከል ከመጥቀስ ይጀምራል። ውበት ውስጣዊ ስላልሆነ አይደለም ችግሩ፤ እኛ የወሰድንበት አውድ የተንሻፈፈ ሲሆን ነው። ግን የሚያተርፈን ጥቅስ መጥቀሱ ሳይሆን እውነታው ነው- The Truth!" እዚህ ደረጃ ግን በቀላሉ አይደረስም"

“ሌላኛው ነገር ደግሞ የሰው ልጅ በባህሪው ፍርሃት አለበት። ውድቀትን፣ ሀዘንን፣ መገፋትን፣ አለመፈለግን፣ ማጣትን፣ አዲስ ነገር መሞከርን ብዙ ነገር ይፈራል። ፍርሃት ደግሞ ራስን ከመጠርጠር የሚመጣ ነው። ያ ፍርሃት ራስህን እንዳትቀበል ያደርግሃል። ይሄኔ ነው አለመቀበልህን መቀበል የሚኖርብህ። የመጨረሻው ግብ ጌታቸው ብቻውን መቆም፣ ማሰብ ሲችል፤ የራሱን ልዩ'ነት(uniqueness) ሲያውቅና ያን ልዩ'ነት ስጋ አልብሶ መግለጥ መቻል ነው። እዚያ ደረጃ ላይ ለመድረስ ግን መንገዱ አልጋ በአልጋ አይሆንም። ራስን መጠርጠር፣ የሆነውን አምኖ ለመቀበል መቸገር... ብዙ ነገር ሊከብደን ይችላል። እዚያ ለመድረስ በመንገዳችን የምናገኘው አንዱ ፌርማታ ነው እንግዲህ አለመቀበልን መቀበል። በሰዓቱ የገባህን እውነት መቀበል እንደከበደህ ማወቅ ማለት ነው። እስከ መጨረሻው ግን አይደለም። እንዳልኩህ መቀበል እስከምትችል ድረስ ነው" ብላኝ ስታበቃ....ሳልፈልግ ብዙ አስወራኸኝ ብላኝ ወደ ዶርም ለመሄድ ከተቀመጥንበት የስድስት ኪሎ ዩኒቨርስቲ ስታድዬም ተነሳች። ስታወራበት የነበረው እርጋታ እና በራስ መተማመን በየትኛው እድሜዋ ይሄን ሁሉ ነገር አስተዋለች ያስብላል። ይሄን ሁሉ ነገር ቁጭ ብለን ስናወራ አይኖቿ ወደ ውጭ አልነበረም የሚመለከቱት። ወደ ውስጥም አይመስለኝም። የሃሳቡ ድር ላይ የቆሙ ይመስለኛል።

ትንሽ በግራችን ተጉዘን ቻው ስንባባል “መች ነበር ነኒ ነኒን እንድትሆን መንገዱ ላይ ይሄ ፌርማታ እንዳለ ያወቅሽው? ማለቴ አለመቀበልሽን መቀበል እንዳለብሽ ያወቅሽው ወይም የነቃሽው?"ብዬ የምርም ማወቅ ፈልጌ ጥያቄ ወረወርኩላት።

“ምነው ነገ ምጽዓት ነው አልክሳ፤ እንገናኝ የለ' ዴ! ነገ ከክላስ መልስ የምርም ማወቅ ከፈልግህ እናወራለን ግን ያን ማወቁ አይደለም አንተን የሚጠቅምህ። በሃሳቡ አጮልቀህ እራስህን እንድታዬው እንጅ በእኔ እንድትደመም አይደለም የምፈልገው። ይሄን ታውቃለህ።"

“ነገ ምጽዓት አለመሆኑን በምን አውቃለሁ። የመዳን ቀን ዛሬ ነው..." ተሳስቀን ድጋሜ ቻው ተባብለን ተለያዬን።

ከመለያየታችን ገና “አለመቀበልህን ተቀበለው!" ብሎ አዕምሮዬ ተቀበለኝ።

ለማት | ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ መድመቂያ ቀለም አለው!

Join us 
@qelemaat@qelemaat
3.7K viewsGech, 14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 22:55:21 አለመቀበልን መቀበል

Written by: Getachew - Promising Psychologist at AAU

“ሰላማዊ ህይወት መምራት የምትችለው ያለህን እና የሆንከውን አምነህ ከተቀበልክ ብቻ ነው" አለችኝ።

“አምኘ መቀበሌ ለምን ይጠቅመኛል?" ጠየኳት። “እራስህን ለመርሳት!" መለሰችልኝ።

“ያላወቅሁትን እኔን መርሳት እንዴት ይቻለኛል? ሳላውቀው የረሳሁት ማንነቴ በምንነቴ ጥያቄ የመፍረስ እጣ ሲጎበኘው ነው ያስተዋልኩት። ብፈልግ እንኳን ችዬ መርሳት የምችል አይመስለኝም።" አሁንም መለስኩላት።

“ራስህን ለማወቅ እየታገልክ ነው፥ ግን ገና ምንም ሳትጀምር ሰልችቶሃል። ከተገናኘን ቀን ጀምሮ ያስተዋልኩት ነገር ነው።" አለችኝ በፍጹም እርግጠኛነት ስለራሴ እየነገረችኝ። ቀጥላም “ በጣም ትፈራለህ! ለምን ማጣትን ትፈራለህ? ምክንያቱን ታውቀዋለህ? ምን አለህ? ያንተ የሆነን ነገር ስለማታውቅ ነው ማጣትን እያሰብክ እየፈራህ ያለኸው። አየህ ያለ ምክኒያት አይደለም ይሄን የም..."

“ራስሽን አውቀሽ ጨርሰሽ ነው?" አሁንም የምትለው ሰልችቶኝ መሃል ላይ ገብቸ ሃሳቧን አቋረጥኳት። “ሲጀመር ሰላማዊ ህይወት ምንድን ነው? ራሴን የማውቀው የት ገብቸ፣ የትስ ወጥቸ ነው? ራሱን ጨርሶ ያወቀ ሰው ግን ይኖራል?!" መልስ እንድትሰጠኝ ፈልጌ ሳይሆን እንዲሁ ለኔ በሚመስል ድምጸት ጥያቄውን አነሳሁ። ቀጥዬም
“ለሁሉም ዓይነት ህመሞች የሚታዘዝ መድሃኒት አለ። የህመሙ ምልክት ያለበት ሰው ምንም ይሁን ሃይማኖቱ፣ ዘሩ ነጭ ይሁን ጥቁር መድሃኒቱን መውሰድ ይችላል። ሰው የመሆን ጥያቄ ሰውነትን ሲያዝል ግን የሚዋጥ መድሃኒት የለም። የሌላን ሰው የህይወት ትርጉም ለመዋጥ መሞከርም የሚሆን አይደለም። ልኩ ይሰፋል አሊያም ይጠባል..."

ሃሳቤ መሃል ላይ ገባችና “ይሄውልህ ጌች..." ብላ አቋራጠችኝ። በመፈለግ ብቻ የምትባዝን ከሆንክ የመባዘን ታሪክ ብቻ ነው የሚኖርህ። ከማንም ጋር እንደ ተኳረፍክ ነው የምትኖረው። ከራስህ፣ ከፈጣሪህ፣ ከፍጡር፣ ከተፈጥሮ....። ከሪስህ ጋር እንኳን እንደ ባላንጋራ በክንብንብ ነው የምትተላለፈው። እናም ከራስህ ጋር ሰላም ፍጠር። በመጀመሪያ ራስህን ባለህ እና በሆንከው እንዲሁ ተቀበለው። አሁን ይሄን ማድረግ ካልቻልክ ደግሞ አለመቀበልህን ተቀበለው። ይሄ የለውጥ መጀመሪያ ነው። እራስህን ሳትቀበል የጀመርከው የትኛውም ነገር እስከመጨረሻው አይቀጠልም፤ ይቆማል።

“አለመቀበልህን ተቀበለው!" ከሃሳቦቿ ውስጥ አዕምሮዬ ውስጥ የፈነዳው ይሄ ነበር። ከዛ በኋላ ምን እንዳለችኝ አላስታውስም። ሃሳቡን ይዤ እንደልማዴ መብሰልሰሉን ተያያዝኩት። አለመቀበልን መቀበል ምን ማለት ነው? ለምሳሌ:- እስካሁን ያስቀመጥኳቸውን ግቦች አንዱንም እንዳሰብኩት ማሳካት ያልቻልኩት በስንፍናዬ ምክንያት እንደሆነ አወቅሁ ልበል። ከዛ ግን አዕምሮዬ ውስጥ የሚፈጠረውን መሻከር (dissonance/inconsistency) ለመቀነስ ሰነፍ ሰው ነኝ ብዬ ራሴን ማሰብ አልፈለኩም። (መቼም ሰው ሰነፍ ከመሆኑ በላይ ሰነፍ መባሉን አይፈልገውም)። ምክንያቱም ሰነፍ ስለሆንኩኝ ነው፣ በጉዳዩ ላይ የተሻለ ግንዛቤ ስለሌለኝ ነው፣ ከእውቀት ወይም ከልምድ ማነስ የተነሳ ነው ብዬ ካመንኩኝ እነዚህን ጉድለቶች ካላሻሻልኩኝ አሁንም ያሰብኩትን ህይወት መኖር እንደማልችል አዕምሮዬ ይነግረኛል። ይሄ ደግሞ ለአዕምሮዬ ሰላም አይሰጠኝም። እና እኔ “ሰነፍ ሰው አይደለሁም" የሚለውን ውሸቴን ነው ምቀበለው?

በረጅሙ ተንፍሳ እይታዋን ቀጠለችልኝ። “ሁሌም'ኮ ስላ'ንተ እውነታውን መቀበል መቻልህ ነው የሚያተርፍህ፣ ወደፊትም የሚያስጉዝህ። እዚህ ደረጃ ላይ እስከምትደርስ ድረስ ነው ስላንተ ውሸቱን የምትቀበለው። ሃቅ ያሰኛል ቋቅ! አይደል የሚባለው። እንዲሁ በቀላሉ አይዋጥምና እውነት። ግን ስትቀበል እውነት ነው ብለህ አይደለም የምትቀበለው። እውነታውን መቀበል የሚችል ትክሻ እስክታሰፋ ድረስ ነው። አየህ እውነቱን መቀበል ስትችል ራስህንም መርሳት ትችላለህ። ያኔ የምንነት ጥያቄ ወደኋላ ቢመልስህም እንኳን መልስ ይኖርሃል። እናም አለመቀበልህን መቀብል የሚኖርብህ *መሆንህን* መቀበል ያቃተህ ጊዜ ላይ ነው። ይሄም ግን በራሱ እውን የሚሆነው የስቃይህ ምንጩ፣ የመቆምህ ምክንያት፣ የውድቀትህ ሰበብ ራስህን ባለማወቅ፣ ስለራስህ ያወቅኸውንም ባለመቀበል ሲጠቃለል ራስህን ባለመሆን የመጣ ችግር መሆኑን ስታውቅ ነው። ስለ ኑባሬ ወይም መሆን (being) አንድ ቀን አወራሃለው ከፈለክ። ያኔ ስቃይህ በትንሹም ቢሆን ይቀንስልሃል። መሆንህን ስትቀበለው ደግሞ ሙሉ በሙሉ ነፃ ሰው ነህ። እየህ እስር የብረት ወይም የአጥር አሊያም የገመድ አይደለም። በራሳችን አስተሳሰብ እና እምነት ነው ከውስጣችን የታሰርነው" ዝም ብዬ በትኩረት ሆኘ እያደመጥኳት ነበር። ቀጥላም....

ክፍል ሁለት ይቀጥላል

ለማት | ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ መድመቂያ ቀለም አለው!

Join us 
@qelemaat@qelemaat
3.5K viewsGech, edited  19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 22:55:05
3.0K viewsGech, 19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 21:08:09 ሌላኛው አማራጭ በሰዓታት የምትጨርሷቸው Certificate ያላቸውን የOnline አጫጭር Courses ከ Udemy በነፃ

https://vm.tiktok.com/ZMYTfoGq7/
3.8K viewsቻLu, edited  18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ