2022-09-30 20:10:55
ብዙ ሰዎች ህመማቸውን መከፋታቸውን የሚያወሩለት ወዳጅ አጥተው ሶሻል ሚዲያ ላይ ነው ሚገልፁት። እንዲህ አይነት ፖስቶችና መልእክቶች ስታዩ ረጋ ብላችሁ ምላሽ ስጡ። ቀልድ ነው ብላችሁ በምታላግጡበት ሰአት ያ ሰው ወደሞት እየቀረበ ይሆናል።
በተለይ በአፍላው እድሜ በሚገኙ ወጣቶች ዘንድ ራስን ማጥፋት በጣም እየጨመረ ነው።
እባካችሁ ራሴን ላጠፋ ነው ወይም መሮኛል ብሎ ለፖሰተ ሰው ብታቁትም ባታውቁትም አብሮነታችሁን ድጋፋችሁን አሳዩ እንጂ ቀልድ አትቀልዱ። ለቀልድና ጨዋታ ብዙ የተሻለ ቦታ አለ።
በቅርብ የምናቃቸው ሰዎች መሞታቸው ሲገለፅ የአብዛኛው ጓደኞቻቸው ምላሽ "እኔ መች ጠረጠርኩ... ደብሮኛል እያለኝ.. " ምናምንም በሚሉ ፀፀቶች የተሞላ ነው።
በዙርያችሁ ላለ ሠው ሁሉ ትኩረት ስጡ!
ራስን ማጥፋት የቀልድ ርእስ አይደለም!
Tesfa G Neda
--------------------------------------------------------------
በዓመት እስከ 800,000 ሰዎች ራሳቸውን እንደሚያጠፉ የWHO ሪፖርት ያመለክታል፡ ከዚህ ቁጥር በላይ ያሉ ሰዎች ደግሞ ራሳቸውን የማጥፋት ሙከራ ያደርጋሉ ።
እድሜያቸው ከ 15 እስከ 29 ዓመት በሆኑ ወጣቶች ሁለተኛው ከፍተኛ ሞት የሚመዘገብበት ችግር ነው ፡ እንዲሁም 79% ያህሉ በዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሃገራት ላይ የሚስተዋል ነው ። ሰዎች ራሳቸውን ለማጥፋት መርዝ መጠጣት መታነቅ ፣የጦር መሳሪያ መጠቀም፣ በዋናነት ይጠቀማሉ ።
አጋላጭ ሁኔታዎች
-----------------------------------------------------------------
የተለያዩ የአዕምሮ ህመሞች በተለይም ድባቴ (Depression) ከፍተኛ የአልኮል መጠጥ ችግር ፣ከባድ አካላዊ ህመም ፣ የኢኮኖሚ ቀውስ፣ ጭንቀት፣ ድንገተኛ ግጭትና ብቸኝነት ዋና ዋና በአጋላጭ ችግሮች ናቸው ። እንዲሁም ቀደም ባለ ጊዜ ያልተሳካ ራስን የማጥፋት ሙከራ ከነበረ ዋነኛ አጋላጭ ችግር ሊፈጥር ሊሆን ይችላል ።
መከላከያ መንገዶች
-----------------------------------------------------------------
ራስን የማጥፋት ችግር በሚገባ መከላከል ይቻላል
በተለይም ራስን ለማጥፋት የሚረዱ ምቹ ሁኔታዎችን መቀነስ፣ ተደጋጋሚ የሆነ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በመገናኛ ብዙሃን በመስጠት፣ ትምህርት ቤቶችን መሰረት ያደረገ ማዕከል በማደራጀት ለመምህራን ለወላጆች እንዲሁም ለትምህርት ቤት ማህበረሰብ በቂ የቅድመ ጥንቃቄ መረጃና ትምህርት መስጠት እንዲሁም ለተማሪዎች የማማከር አገልግሎት ማመቻቸት፣ የአልኮል መጠጥ አጠቃቀም ላይ ጥንቃቄ ማድረግ ፣ የአእምሮ ህመሞችን ቶሎ መለየትና በቂ ህክምና ማድረግ እንዲሁም ተገቢውን ክትትል ማድረግ፣በቂ የሱስ ማገገሚያ ማዕከላትን ማቋቋም።
================================
ማጣቀሻ ፡- WHO report
ዮሴፍ ሳህለ
ባላችሁበት የቴሌግራም ግሩፖች #share አድርጉ @psychoet
1.7K views17:10