Get Mystery Box with random crypto!

ኖኅ Book Delivery

የቴሌግራም ቻናል አርማ noahbookdelivery — ኖኅ Book Delivery
የቴሌግራም ቻናል አርማ noahbookdelivery — ኖኅ Book Delivery
የሰርጥ አድራሻ: @noahbookdelivery
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.84K
የሰርጥ መግለጫ

The first and the only book delivery service in Ethiopia. Order books all over the world with fair price & fast delivery
Free delivery
ለአስተያየትና መፅሐፎችን ለማዘዝ ከታች ባሉት አድራሻ መልዕክት ያስቀምጡልን
@Noahbook7

"ማንበብ ፋሽን ነው"
Join us @noahbookdelivery

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-05-07 18:48:46
መጽሐፍ ጥቆማ
" መቅደላ "
የቴዎድሮስ ዕጣ

በሄነሪ ሞርተርን ስታሊን
ትርጉም ፦ ገበዩሁ ተፈሪ (ዶ/ር)

በጥሩ ጥራት ከሃገር ውጪ የታተመ ጥቂት ቅጂዎች አሉን። ተርጓሚው ከዚህ በፊት የተደበቀው ማስታወሻ እና ኢትዮጵያ በአውሮፓ ዲፕሎማሲ እንዴት ተረፈች? የሚል ግሩም መጽሐፍ ተርጉሞ አስነብቦናል።

ከዙላ እሰከ መቅደላ ከእንግሊዝ ጦር ጋር የተጓዘ አሜሪካዊ ጋዜጠኛ የዘገበው ታሪከ፡፡

በአፄ ቴዎድሮስ የመጨረሻዋ ሰአት በቦታው የነበረ የአይን ምስክር፡፡

አንድ ጊዜ ተወዳጅ ሀይለኛና ገናና የነበሩትን ንጉሥ የመጨረሻ ምዕራፍ ግልፅና ጥልቅ በሆነ ሁኔታ ያስገነዝባል፡

ከመቅደላ በፊት የነበሩ ሁኔታዎችን ይነግረናል።

መቅደላ እንደዚህ በዝርዝር ቀርቦ አያውቅም፡፡

ስለ አፄ ቴዎድሮስ መነበብ የሚገባው ጽሑፍ።

ሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ማንኛውንም መፅሐፎች ከልዩ ቅናሽ ጋር ይዘዙ።
Order the book all over the world with fair price and fast delivery

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

   @Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
953 viewsኖኀ መፅሐፍ, 15:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 17:55:10
እንግሊዛዊው አንቶኒ በርገስ በ42 ዓመቱ በጭንቅላት ካንሰር ምከንያት በህይወት የሚቆየው ለአንድ አመት ብቻ እንደሆነ ዶክተሮች ይነገሩታል።
በጊዜው በጣም ያዝናል፣ይሁን እንጂ ሚስቴ ከሞትኩ በኋላ እንዳትቸገር በማለት በቀረችኝ ጊዜ ስራ መስራት አለብኝ፣ለሚስቴ ጥሪት ማስቀመጥ አለብኝ ብሎ ወሰነ።

አንቶኒ በርገስ ኘሮፌሽናል ደራሲ አልነበረም።ነገር ግን በዉስጡ የተዳፈነ የመፃፍ ችሎታ እንደነበረዉ ያዉቅ ነበርና ወረቀቱን ከጽሕፈት ማሽኑ ጋር አወዳጅቶ መፃፍ ጀመረ።
በሚገርም ሁኔታ በቀረችዉ አንድ አመት ውስጥ 5 መፃሕፍትን አሰናድቶ ጨረሰ።ይህም ታዋቂዉ ደራሲ Em foster በህይወቱ ሙሉ ከፃፈዉ በላይ እሱ በአንድ አመት ዉስጥ የፃፈዉ ይበልጥ ነበር ።እንዲሁም J.D.stelenger የተባለዉ ደራሲ በህይወት ዘመኑ ከፃፈዉ  መፅሐፍ በላይ በእጥፍ ፃፈ።

በካንሰር ለመሞት አንድ አመት ቀረህ የተባለው አንቶኒ በርገስ  ይህን የአንድ አመት ጊዜ በለንደን ሆስፒታል ውስጥ አሳልፏል።ነገር ግን ከበርካታ የሴሬብራል ምርመራዎች በኋላ ምንም አይነት በሽታ ወይም ዕጢ አልተገኘበትም።በዚህ ጊዜ ነበር የሙሉ ጊዜ ጸሐፊ ለመሆን የወሰነው።

በኖረበት  ቀሪ እድሜ በ76 ዓመቱ ይችን አለም እስከተሰናበተበት ጊዜ ድረስ 70 መፅሃፍቶችን ለአንባቢያን አበረከተ።በተለይ 'clock work orange' በሚል ያሳተመዉ መፅሐፍ ታላቅ እዉቅናን ያስገኘለት ስራው ነበር።

አንቶኒ በርገስ ‘ለመሞት አንድ አመት ነዉ ያለህ’ ባይባልና ሚስቱ እንዳትቸገር 'ጥሪት አስቀምጬ ልሙት' በሚል ሀሳብ ባይነሳ፣ይህን ያህል ቁጥር ያለው መፅሐፍ ባልፃፈ ነበር።

ከዚህ ታሪክ የምንማረው:-የተሰጠን ዛሬ እንደሆነ አውቀን የተዳፈነውን ችሎታችንን አውጥተን ለሌሎች የብርሃን ችቦን እንለኩስ።

ምንጭ፦የስኬት አካዳሚ

Join us @noahbookdelivery
1.2K viewsኖኀ መፅሐፍ, 14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 07:08:37
አዲስ መጽሐፍ ጥቆማ
" ጠመንጃና ሙዚቃ "
ይነገር ጌታቸው (ማዕረግ)

ማህበራት ሲመሰረቱ እራሳቸውን በገንዘብ/በገቢ መደጎማቸው የተለመደ ነው። እናም የሀገር ፍቅር ማኅበር የገቢ ችግሩን ለሟሟላት ያልፈነቀለው ፣ ያልሞከረው ጉዳይ አልነበረም።
በ1940'ዎቹ መባቻ ላይ ግን አንድ እድል ገጠመው። እርሱም አዲስ አበባ ውስጥ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ጠንቋዮች አቤቱታ ማቅረብ ጀመሩ።

ጥያቄአቸውም ጥንቁልና ሥራ ሆኖ ሳለ መንግስት ስለምን ትኩረት አልሰጠውም የሚል ነበር። ይነገር ጌታቸው ደሞ ጠመንጃና ሙዚቃ በሚለው መጸሐፉ ላይ እንዲህ አሰፈረው ጉዳዩን...ገጽ 53

  "በወቅቱ ጥንቆላ ሥራ መሆኑን የተረዱ አንዳንድ ነዋሪዎች ጠንቋይ በመሆን የገቢ ምንጭ ለማግኘት ይሯሯጡ ነበር"። መንግስትም ሁኔታውን አየና የሥራ ፈቃድ አውጥተው እንዲንቀሳቀሱ አሳሰበ።

ይህን የፈቃድ የመስጠት አላፊነት ደግሞ ለሀገር ፍቅር ማኅበር ተሰጠ። አስተዳደሩም ፍቃዱን ለመውሰድ 10 ብር እንደሚያስፈልግ በመደንገግ ወደ ሥራው ገቡ። በዚህ በፊት የኢትዮጵያ ሕዝብ ያገር ፍቅር ማኅበርን የጥበብ ሰዎች የደሞዝ ክፍያ ለማሳደግ ከተሞከሩት ሙከራዎች ሁሉም ይህ የላቀው ሆኖ ተገኘ።

በየዓመቱም ጠንቋዮች ፍቃዳቸውን ለማሳደስ ሲመጡ የሚገኘው ገቢ ከፍ አለ። ነገር ግን በከተማው ውስጥ አዝማሪዎች ስለበዙ ያ ደሞ ወደ ሀገር ፍቅር የሚመጣውን ሰው ስለሚቀንስ ያለ ፍቃድ እንዳይሰሩ ድንጋጌ አወጣ።

ያም ቢሆን ማኅበሩ እጅ እያጠረው በመምጣቱ 33 ያህል አባላቱን በገቢ ምክንያት አሰናበተ። እንዲህ እንዲህ እያለ እዚህ ደርሷል ....

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

@Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
1.2K viewsኖኀ መፅሐፍ, 04:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 15:30:38
መልካም ልደት!
ጋሼ ስብሐት ለአብ ዛሬ 87 ዓመታት ሞላው ። መልካም ልደት ጋሼ ! " የእኔን
ልደት መላው ኢትዮጵያ ነው የሚያከብረው" ይለኝ ነበር በህይወት እያለ።እለቱ ጀግኖች አርበኞቻችን ድል ያደረጉበት ቀን መሆኑን ልብ ይሏል። የድሉን ዓመት ጋሼ ስብሐት በአምስት አመት ታላቁ ነው ።ነገሩ እንዲህ ነው። ሚያዚያ 27 ቀን በ1928 የጣሊያን ሠራዊት አዲስ አበባ ገባ። የእዚያን እለት ጋሼ ርባገረድ በተባለች የገበሬዎች መንደሩ ውስጥ ተወለደ። ልክ አምስት አመት ሲሞላው የጣሊያን ፋሽት ተሸንፎ ከአገራችን ወጣ። የዛኑ እለት ግርማዊ ተቀዳሚ አፄ ኃይለሥላሴ ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም መናገሻ ዋና ከተማቸው አዲስ አበባ በድል አድራጊነት ገቡ። ስዚህም የጋሼ ስብሐት ልደት ማለዳ ላይ 21 ጊዜ መድፍ ተተኩሶ የሚከበር እለት ሆነ ።
via-ዘነበ ወላ - zenebe wola

ጋዜጠኛ ፦ አሁን በዓሉ በሕይወት ቢኖር ምን ሊሆን ይችላል ?
ስብሀት ፦ በዓሉ ድንቅ ደራሲ ነው። አሁን በሕይወት ቢኖር እኔ ጋር ሳይሆን እርሱ
ጋር ነበር የምቴሄደው። እግዜር ስለሚወደኝ ቀጨልኝ !!
ጋዜጠኛ ፦ አንዲት አድናቂህ አንተን ማግባት እፈልጋለሁ ..
ስብሀት ፦ የተፈቀደልን በጣታችን ቁጥር ልክ ነው ፣አምስት ግዜ። እኔ አምስት ግዜ አግብቻለሁ። ባይሆን ከሞት በኋላ ባለን ሕይወት የመጀመሪያ ሚስቴ ትሆኛለሽ በላት።
ጋዜጠኛ ፦ ታክሲ ስትጠቀም ከፍለህ አታውቅም ይባላል ?
ስብሀት ፦ ስብሀት በሚለው አድናቂዎቼ ይከፍሉልኛል። ነገር ግን ይከፈልልኛል
በሚል ገንዘብ ሳሊዝ ተሳፍሬ አላውቅም።
_ ጋሼ መልካም ልደት 87ኛ አመት _
via-Rama Gutema Olika

Free Delivery
መፅሐፎችን ለማዘዝ

@Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
1.2K viewsኖኀ መፅሐፍ, edited  12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 08:11:06 የአርበኞች ድል ቀን መታሰቢያ በዓል

አርበኝነት በኢትዮጵያ ታሪክ በደማቅ ቀለም የተጻፈው ከ1928 ዓ/ም በኋላ ነበር፡፡ በዘመኑ ጣሊያን በ1888ዓ/ም በዳግማዊ ምኒልክ የተመራው የኢትዮጵያ ጦር በዓድዋ ያደረሰባትን መራር ሽንፈት ለመበቀል 40 ዓመታትን ስትዘጋጅ ከርማ ለመላው የጥቁር ሕዝብ እንደ ነጻነት ምልክት ተደርጋ የምትታየውን ኢትዮጵያን ወረረች፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብም በአንድነት የጣሊያንን ወረራ ለመከላከል ጨርቄን ማቄን ሳይል ተነሳ፡፡ በሰሜን እና በምስራቅ በተካሄዱ ጦርነቶች ግን ኢትዮጵያዊያን እንደ ዓድዋው ድል አልቀናቸውም፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ በተሳተፉበት የማይጨው ጦርነትም ድል አልተገኘም፡፡

ያም ሆኖ ኢትዮጵያዊያን በመድፍ እና በአውሮፕላን መርዝ በታገዘው የጣሊያን ጦር ተሸነፍነ ብለው ተስፋ አልቆረጡም፤ እጅም አልሰጡም፡፡ የሀይማኖት አባቶች “እንኳን ሕዝቡ የኢትዮጵያ ምድር ለባዕድ እንዳይገዛ” አውግዘው ውድ መሰዋዕትነት ከፈሉ፡፡ ቆራጦችም የአርበኝነት ትግል ለማካሄድ ዱር ቤቴ አሉ፡፡

በዚህም እንደ እጃቸው መዳፍ ጠንቅቀው የሚያውቁትን የአገራቸውን መልክዓ-ምድር መመኪያ አድርገው ጣሊያንን ይፋለሙ ጀመር፡፡ ከመኳንንቱ እና ከመሳፍንቱ በተጨማሪ ብዙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን የአርበኝነት ትግሉን ተቀላቀሉ፡፡

በበጌምድርና አካባቢው ራስ ውብነህ ተሰማና ቢትውደድ አዳነ፤ በጎጃም ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ፣ በላይ ዘለቀ(አባ ኮስትር)፣ ደጃዝማች ኃይለየሱስ ፍላቴ እና ራስ ኃይሉ በለው፤ በሸዋ ራስ አበበ አረጋይ፣ መስፍን ስለሺ ፀሐይ ዕንቁሥላሴ፤ የበሼ ቤተሰቦች ደጃች ተሾመና አበበ ሽንቁጥ፤ በወሎ እነ ኃይሉ ከበደ፣ ወሰን ኃይሉ እና በሌሎች የአገራችን ክፍሎች የሚገኙ አርበኞች ሕዝቡን በማስተባበር ጣሊያንን ለአምስት ዓመት የረገጣት የኢትዮጵያ ምድር ረመጥ እንድትሆንበት አደረጉ፡፡

ከአምስት ዓመት ተጋድሎ በኋላም ጣሊያን ድጋሜ የሽንፈትን ጽዋ ተጎነጨ፡፡ አርበኞች በዱር በገደሉ፣ የውስጥ አርበኞች በከተማ እና ንጉሠ ነገሥቱ በውጭ ባካሄዱት የዲፕሎማሲ ትግል ወድቃ የነበረችው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ተነሳች፡፡ ሚያዚያ 27/1933 ዓ/ም ድጋሜ በኢትዮጵያ ሰማይ በነጻነት ለመውለብለብ በቃች፡፡ ኢትዮጵያም ድጋሜ በነጻነት ደምቃ ታየች፡፡

ይህ የአርበኞች ድል መታሰቢያ በዓልም ሁሌም ሚያዚያ 27 ይከበራል፡፡ ዘንድሮም የአርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል በመጭው አርብ ለ82ኛ ጊዜ በድምቀት የሚከበር ይሆናል፡፡

ጃንሆይና ሚያዚያ 27 ቀን ያደረጉት ንግግር

አሁን በመጨረሻው ለናንተ ለህዝቤ የማስታውቃችሁ ዛሬ የሁላችን የደስታ ቀን መሆኑን ነው።ዛሬ ጠላታችንን ድል የመታንበት ቀን ነው።ስለዚህ በሙሉ ልባችን ደስ ይበለን ስንል ደስታችን በክርስቶስ መንፈስ እንጂ በሌላ አይሁን።

ለክፉ ክፉ አትመልሱ። ጠላት እንደ ወትሮው ልማድ እስከዚህ መጨረሻ ሰዓት ድረስ እንደሰራው ያለ የጭካኔና የግፍ ስራ አትስሩ።ጠላታችን መውቀሻ በሚሆነው ነገር የኢትዮጵያን መልካም ስም እንዳታሳድፉ  ተጠንቀቁ።

ጠላቶቻችን በእጃቸው ያለውን መሳሪያ እንዲያስረክቡና በመጡበት መንገድ ተመልሰው እንዲሔዱ እናደርጋለን።

**
ይህ ቃል ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሚያዚያ 27/1933 በድል አድራጊነት ወደ መናገሻ ከተማቸው ሲገቡ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ ነው።አፄ ሚንሊክ መቀሌ ላይ በጣይቱ መላ የማረኳቸውን በቅሎ ሰተው እንደሸኙት ሁሉ አፄ ኃይለስላሴም በዚህች ቀን ህዝባቸው ከበቀል ተግባር እንዲታቀብ አውጀው ነበር።ይህ አዋጅ ባይታወጅና ምድሪቱም የደግ ህዝቦች ምድር ባትሆን ከተሰራብን ግፍ አንፃር ኢትዮጵያ በነበሩት ጣሊያኖች ላይ ስንት ነገር በደረሰ ነበር።

ኢትዮዽያ የአስተዋይ ነገስታት እና የጨዋ ህዝብ ምድር።ክብር በደምና አጥንታቸው ዋጋ ነፃነትን ላወረሱን አባቶች።መልካም የአርበኞች ቀን  ።

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
1.2K viewsኖኀ መፅሐፍ, 05:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-04 22:01:32
አዲስ መጽሐፍ ጥቆማ
" ኦርቶዶክሲያ "
የመ/ር  ግርማ ከበደ ትምህርታዊ ስብከቶች ስብስብ

የእኛ ዘመን ሃይማኖትን ማስረዳት ከሥጋ ሥራም የውትድርና የመሰለበት ዘመን ነው ማለት ይቻላል። አንዳንዴስ ከዚያም የከፋ ይመስላል። ምክንያቱም በውትድርና ሳይንስ ውስጥ በጦርነት ላይ እጅ የሚሰጥ ወታደርን ማርኮ ማምጣት ያንንም እንደ ራስ አድርጎ መንክባከብ የሞያ ሥነ ምግባር አለው። ከእኛ ዘመን መምህራን አንዳንዶቻችን ስንታይ ደግሞ እንኳን ከሌላ ሃይማኖት ላለ እኛ ውስጥ ሆኖ በፈተና ውስጥ ለሚኖር እንኳ ርኅራሔ የማናሳየው ብዙዎች ነን። ሰው ሆኖ ሊሳሳት እንደሚችል አስቦ በፍቅር አስረድቶ ከማነጽና በእምነቱ ከማጽናት ይልቅ መናፍቅ አስኝቶ ለማስጠላትና ለማባረር ያለው ሩጫ በእጅጉ ያሳስባል፣ ያስደነግጣልም። ሐኬት ሰልጥኖብናልና።

እንዲህ ያሉ መጻሕፍት ረሀበ ነፍስን ያስታግሳሉ። ምክንያቱም እርሱ ራሱ በዚሁ መጽሐፍ ላይ ተናግሮት በዚህ መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ እንደምናየው እያደረገው የሚያስተምር መምህር ነበርና። በመጨረሻው ዘመን ስለሚነሣው የቃለ እግዚአብሔር ረሀብ የተነገረውን ትንቢት ሲያብራራ የረሀቡ ምክንያት የመምህራን አለመኖር መሆኑን ያሰቀድማል። የሉም የተባሉት  ግን መምህራን ወይም ሰባክያን ጠፍተው ሳይሆን የማያደርጉትንና የማይኖሩትን ስለሚያስተምሩ ነው ይላል። እርሱ ግን አድርጎት ያስተማረው ስለሆነ ትምህርቱ በትክክል ከረሀብ የሚታደግ የማያውቀውን የማይናገር፣ እንደሚያውቅ ለማሳወቅም የማይደክም፣ ሌሎችን በመንቀፍ፣ በማስጸይፍና በመሳለቅ ግብር ውስጥ ያልተያዘ ስልሆነ ምንም ዐይነት ሐኬት አይታይበትም። ይህም ለስጦታ መብቃት ነው።
ጠቋሚ፦መ/ር ብርሃኑ አድማስ

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

@Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
1.2K viewsኖኀ መፅሐፍ, 19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-04 08:18:34
አዲስ መጽመፍ ጥቆማ
" ቅድስና በክርስትና "
በሊቀ ማእምራን ዮሐንስ ለማ

"እግዚአብሔር ለሕዝቡ በውስጥዋም ለተወለዱት አለቆችዋ በመጽሐፍ ይነግራቸዋል" (መዝ.86(87)÷7)

ታላቅ የምሥራች ለመጻሕፍት አፍቃርያን እና አንባብያን በሙሉ!
#የዚህ ድንቅ መጽሐፍ ይዘት በክርስትና ሕይወት ውስጥ ቅድስና እጅግ አስፈላጊና የክርስትናችን ማጣፈጫ ቅመም  መሆኑንና እንዲሁም ቅድስናና ክርስትና ሊለያዩና ሊነጣጠሉ የማይችሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን በሰፊው ታትተውበታል። 

በተጨማሪም ጠላት ዲያብሎስ በመንፈሳዊ ሕይወታችን፣ በትምህርታችን፣ በሥራችን ፣በትዳራችን ፣በኑሯችን እንዲሁም በተለያየ መንገድ የሚያመጣብንን ክፉ ፈተና ማሸነፍና ድል ማድረግ የምንችለው በቅድስና ሕይወት ስንመላለስና ሰውነታችንን ከኃጢአትና ከርኩሰት ለይተን ለቅዱሱ እግዚአብሔር ማደሪያ (ታቦት) ስናደርገው ብቻ መሆኑንና በቅድስና ሕይወት ሕይወት ስንኖር ጠላት ሊታገለን ይችል ይሆናል እንጂ ፈጽሞ ሊጥለንና ሊያሸንፈን እንደማይችል በሰፊው የተብራራበት ድንቅ መጽሐፍ ነው ።

#መጽሐፉ 10 ምዕራፎች እና 390 ገጾች ያሉት ሲሆን ሁላችሁም ይህንን ከንጹህ ምንጭ የተቀዳ ድንቅ መጽሐፍ ገዝታችሁ እንድታነቡና አብዝታችሁ እንድታተርፉበት እንዲሁም ለሕይወታችሁ መንፈሳዊ ስንቅን እንድትሰንቁ  ግብዣዬ ነው።
ጠቋሚ፦ ደብረ ከርቤ ቅድስተ ማርያም  ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ።

ሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ማንኛውንም መፅሐፎች ከልዩ ቅናሽ ጋር ይዘዙ።
Order the book all over the world with fair price and fast delivery

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

   @Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
1.4K viewsኖኀ መፅሐፍ, 05:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 23:05:58
" መኖር ማለት ካልጠበቅነው ነገር ጋር
የመላመድ ጥበብ ነው። "
elenor c.wood

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
1.6K viewsኖኀ book delivery, edited  20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 16:36:42
አዲስ መጽሐፍ ጥቆማ
" ጎሐ ጽባሕ ዘቅኔ "
አዘጋጅ፦ መምህር መርሐ ጽድቅ

  ይህ መጽሐፍ በውስጡ
የቅኔ ምንነት
የአማርኛ ቅኔና የግእዝ ቅኔ ልዩነት
የቅኔ አቆጣጠር ቅደም ተከተል ከበቂ ምሳሌ ጋር
የቅኔ ሙያ አሰጣጥ ቅደም ተከተሎች ከበቂ ምሳሌ ጋር
የአራቱ ንባባት መለያ መንገድ ከበቂ ምሳሌ ጋር
የቅኔ ዜማ ልክ ቀለም አቆጣጠር መንገድ ከበቂ ምሳሌ ጋር
የቅኔ ዜማ ልክ በተለያዩ ስዕላዊ መግለጫዎች የተደገፈ
የግስ አይነቶች
የግስ አርዕስት አወራረድ በአምስቱም አእማድ
ከግስ የሚወጡ ዘሮች መለያ መንገድ ከበቂ ምሳሌ ጋር
ከግስ የሚወጡ ዘሮች ቋሚ ፍች ከበቂ ምሳሌ ጋር
ከግስ የሚወጡ ዘሮች ጥቅም በቅኔ ውስጥ ከበቂ ምሳሌ ጋር የሚሉ በጣም አስፈላጊ ጋር የሚሉ በጣም አስፈላጊ ነገሮችን በውስጡ ይዟል።

ሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ማንኛውንም መፅሐፎች ከልዩ ቅናሽ ጋር ይዘዙ።
Order the book all over the world with fair price and fast delivery

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

   @Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
1.6K viewsኖኀ መፅሐፍ, 13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 09:20:22
አዲስ መጽሐፍ ጥቆማ
"ሕይወት እንዲህ ናት እና ሌሎችም"
በሊቀ ሊቃውንት ስመዐኮን መልአክ

ዓለምን ቅደሙ

ክርስቲያኖች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የሚገሠግሡ በዚህ ዓለም አድርገው ነው።ሰማያዊውን ኑሮ ከምድር ተለይቶ የጀመረ ጻድቅ የለም።ዓለምና ክርስትና ሁልጊዜ ይሽቀዳደሙብናል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ" (ዮሐ 16፤33) ማለቱ ከዓለም ጋር ፉክክር ስላለብን ነው።

በክርስትና መታገል የግድ ነው።መሸነፍ ግን ነውር ነው።ሩቅ መሄድ ይቻላል፤ ነገር ግን በስንዝር በሚለካ እንቅስቃሴ መጀመር የተፈጥሮ ግዴታ ነው።መጥቆ መብረር ይቻላል፤ ነገር ግን መብረርን ለመለማመድ በየጥቂቱ መሬቱን እየለቀቁ መንተፋተፍ ግዴታ ነው።ከሁሉ በላይ እስኪሆኑ ድረስ ማደግ ይቻላ፤ ነገር ግን ከታናሽነት መጀመር ግዴታ ነው።ብዙ ሀብት መሰብሰብ ይቻላል፤ነገር ግን ከትንሽ መጀመር ግዴታ ነው።

ጥቂቷን እርምጃችሁን አትናቋት።ማን ያውቃል ዛሬ በምናደርጋት ትንሽ እርምጃ ሰይጣንን እንቀድመዋለን።ምናልባትም እኛ የምናደርገው እሽቅድምድም የመጨረሻው ዙር ላይ ብንሆንስ?  ቅጽበታዊ በሆነች ፍጥነት ሰይጣንን ስለቀደሙት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የተጋደሉ ሰማዕታት የድል አክሊል ተቀዳጅተዋል።የመጨረሻው ዙር ላይ ባገኙት ውጤት ዘማውያን ደናግሉን ቀድመው ገነትን ተሸልመዋል።

እህቶቼና ወንድሞቼ ኾይ!
ሁልጊዜ በሕይወታችሁ ይሄ የመጨረሻው የመወዳደሪያ ዙር እንደሆነ አስቡ እንጅ ብዙ ዙር እንደቀራችሁ አታስቡ። በዚህ ዙር አሸናፊ ስለመሆን እንጅ በዚህ ዙር ባይሳካልህ በሌላ ዙር አንደኛ ትወጣለህ የሚላችሁን የሰይጣንን ምክር አትስሙ።ይሄ የመጨረሻው ዙር ነው። ፍጠኑ!

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

@Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
1.5K viewsኖኀ መፅሐፍ, 06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ