Get Mystery Box with random crypto!

ኖኅ Book Delivery

የቴሌግራም ቻናል አርማ noahbookdelivery — ኖኅ Book Delivery
የቴሌግራም ቻናል አርማ noahbookdelivery — ኖኅ Book Delivery
የሰርጥ አድራሻ: @noahbookdelivery
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.84K
የሰርጥ መግለጫ

The first and the only book delivery service in Ethiopia. Order books all over the world with fair price & fast delivery
Free delivery
ለአስተያየትና መፅሐፎችን ለማዘዝ ከታች ባሉት አድራሻ መልዕክት ያስቀምጡልን
@Noahbook7

"ማንበብ ፋሽን ነው"
Join us @noahbookdelivery

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-13 09:13:14
Book Suggestion
"Shadow and Bone"
Leigh Bardugo

Surrounded by enemies, the once-great nation of Ravka has been torn in two by the Shadow Fold, a swath of near impenetrable darkness crawling with monsters who feast on human flesh. Now its fate may rest on the shoulders of one lonely refugee.

Alina Starkov has never been good at anything. But when her regiment is attacked on the Fold and her best friend is brutally injured, Alina reveals a dormant power that saves her life—a power that could be the key to setting her war-ravaged country free. Wrenched from everything she knows, Alina is whisked away to the royal court to be trained as a member of the Grisha, the magical elite led by the mysterious Darkling.

Yet nothing in this lavish world is what it seems. With darkness looming and an entire kingdom depending on her untamed power, Alina will have to confront the secrets of the Grisha… and the secrets of her heart.

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

@Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
92 viewsኖኀ መፅሐፍ, 06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 08:54:42
Book Suggestion
" The Burning Girls "
C.J. Tudor

A dark history lingers in Chapel Croft. Five hundred years ago, local Protestant martyrs were betrayed then burned.Thirty years ago, two teenage girls disappeared without a trace.And a few weeks ago,the vicar of the local parish hanged himself in the nave of the church.

Reverend Jack Brooks, a single parent with a fourteen-year-old daughter and a heavy conscience, arrives in the village hoping for a fresh start. Instead, Jack finds a town rife with conspiracies and secrets, and is greeted with a strange welcome package: an exorcism kit and a note that warns, “But there is nothing covered up that will not be revealed and hidden that will not be known.”

The more Jack and daughter, Flo, explore the town and get to know its strange denizens, the deeper they are drawn into the age-old rifts, mysteries, and suspicions. And when Flo begins to see specters of girls ablaze,

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

@Noahbook7 0939115238

Join us @noahbookdelivery
139 viewsኖኀ መፅሐፍ, 05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 08:41:39
Book Suggestion
"THE THURSDAY MURDER CLUB"
Richard osman
Novel

In a peaceful retirement village, four unlikely friends meet weekly in the Jigsaw Room to discuss unsolved crimes; together they call themselves the Thursday Murder Club.

When a local developer is found dead with a mysterious photograph left next to the body, the Thursday Murder Club suddenly find themselves in the middle of their first live case.

As the bodies begin to pile up, can our unorthodox but brilliant gang catch the killer, before it's too late?

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

@Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
167 viewsኖኀ መፅሐፍ, 05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 08:21:22
ያልነቀልከው ነገር መባዛቱ አይቀርም

ብዙዎች የተሳሳቱትን ስህተት እንዳትሳሳት ይህችን ምክር ጣል ላድርግልህ፡፡ በሕይወትህ አንድ ችግር አይተህ በቸልተኝነት “በራሱ ጊዜ ይሄዳል” ብለህ ከመተው ተጠበቅ፡፡ ማንኛውም ችግር ዝም ካልከው በራሱ ጊዜ ይሄዳል የሚል አመለካከት ያላቸው ሰዎች ችግሩ ገዝፎና በዝቶ ከአቅም በላይ ሲሆን ነው የሚባንኑት፡፡

እስቲ አቤትህ ብቅ ጥልቅ ሲሉ ያየሃቸውን ተባዮች ዝም በላቸው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ተባዝተው ካልወረስንህ ይሉሃል፡፡ የተቀረውንም በሕይወትህ አላስፈላጊ የሆኑ ሁኔታዎችንም በዚህ መልኩ ማየት መጀመር አለብህ፡፡

እውነታው፡- ያላከምከው ቁስል በቶሎ አይድንም . . . ያልነቀልከው አረም በራሱ አይሄድም . . . መስመሩን ያላበጀህለት ሰው በላይህ ላይ መረማመዱ አይቀርም . . . ያልቀጣኸው ልጅ መሞላቀቁና መበላሸቱ አይቀርም . . . እምቢ በማለት ያላባረርከው ሃሳብ ወደተግባርና ወደልማድ መለወጡ አይቀርም፡፡

ዛሬ ምን ምን እንዳከናወንክ የማሰብህን ያህል ከዚያው ጋር ሊያሳስብህ የሚገባው ነገር አለ፡፡ ዝም ብለህ እንደፈለገ እንዲሆን ስለተውከው ጉዳይም ጭምር ልታስብና የእርማት እርምጃን ልትወስድ ይገባሃል፡፡ አለዚያ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ነገ ችግሩን መጋፈጥህ አይቀርም፡፡ ለዚያውም ገዝፎና አይሎ!  

                       ዶ/ር እዮብ ማሞ

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
789 viewsኖኀ መፅሐፍ, 05:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 08:18:29 [ሴት እና ሰይጣን አንድ ናቸዉ!]

ገነትን ሻች~ፃዲቅ ነኝ ባይ፤
አደግዳጊ~ ጽሩይ መሳይ፤
ያንቺን ዉበት ከገነቱ ልቆ ቢያየዉ፤
... አማኙ ሰዉ እምነት ከዳዉ...!

  ቃል አነሳ~ብሂል ሳበ፤
ፈጣሪን ከፍጡር~እያስተዛዘበ...
ገነትን ከዉበትሽ~ሊያልቀዉ የጣረ፤
ተፈጣሪነትሽን~በሰይጣን ቀየረ..!!
                   :
ላልኖረበት ገነት~አይቶት ለማያዉቀዉ፤
እምነት የቃል እዳ~ገነቱን አስናቀዉ!

አልተረዳም እንጂ~ቢያዉቀዉማ ኖሮ፤
ደጉ አምላካችን~የልቡን መርምሮ፤
''ገነትን በሴት ላይ~አኑሯል ቀይሮ..!! "
   
      {..ሴት እና ገነት አንድ ናቸዉ..!!}


ዳግማዊ ውሉደ-ሰብ

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
748 viewsኖኀ መፅሐፍ, 05:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 15:29:54
አዲስ መጽሐፍ ጥቆማ
"ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ"
በመጋቤ ምሥጢር ቡሩክ ጌታቸው

ቅዱስ ያሬድ በአካል ያልነበረበትን ዘመን በምሥጢር ሰረገላ ወደኋላ ተጉዞ በአካል በቦታው ላይ እንደተገኘ ሰው ትኩስ ምሥጢር ሲያሳፍሰን እንዲህ ይላል ‹‹እነብር ቤተ መቅደስ እምግርማ ውእቱ መልአክ ክነፊሁ ዘእሳት መንበሩ ዘሜላት ልብሱ ጽሑፍ ወልደ እግዚአብሔር ይመስል ወደቁ ገጽየ ወበቃሉ አንሥአኒ እግዚኦ ተሠሃለኒ›› በማለት ምስክርነቱን ይናገራል። ይህን የድጓ ምንባብ መነሻ አድርገው ታላቁ ሊቅ አለቃ አያሌው ታምሩ የዝማሬውን ትርጉም በስንኝ መልክ ሲተረጉሙት እንዲህ ብለዋል።
«ኾኜ ቤተ መቅደስ ድንገት ከተፍ ያ መልአክ እሳት ክንፉ መርዕድ ወመደንግጽ ግርማና ሞገሱ
ሐር ነው መንበሩ ቃል ተከትቧል ልብሱ
የእግዜር ልጅ ነው እሱ
በአፍጥሜ ተደፋሁ ድንጋጤ ጣለኝ፤
ቃሉ ግን አነሣኝ፤
አውጣኝ አምላኬ አቤቱ ይቅር በለኝ»

ሲል ቅዱስ ያሬድ በተመስጦ እየተነጠቀ ዓለመ መላእክትን ያየበትን አንቀጽ ሊቁ ይዘቱን እንደጠበቀ በግጥም መልክ ተርጉመውታል።ቅዱስ ያሬድ ይህን ድርሰት ለብሥራተ ገብርኤል ነው የደረሰው ብለው አባቶች ታኅሣሥ ፲፱ ቀን ከሚባሉ ዜማዎች ጋር መድበውታል፤ቃሉም የሚለው ገብርኤል ተልኮ ሲመጣ ታላቁን የምሥራች ይዞ ቤተ መቅደስ ነበርኩ ደነገጥኩ ወደቅሁ ተነሣሁ ማለቱ ገብርኤል ተልኮ የመጣው ያሬድ ከመወለዱ ከ፮፻ ዓመታት በፊት ሲኾን ታዲያ እንዴት እዛው ነበርኩ ይለናል፤ብለን የጠየቅን እንደኾነ የደራሲ ምናብ በቦታና በጊዜ የማይወሰን እንደኾነ እንረዳለን።የሰው ልጅ በአሳቢነቱ (በለባዊነቱ) ሩቅ ያያል፤ጥልቁን ሕይወት ይመረምራል፤አካባቢውን ያጠይቃል፤በተጓዳኝ ያሉትን አንድምታዎችን ያብሰለስላል።

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

@Noahbook7 0939115238

Join us @noahbookdelivery
73 viewsኖኀ መፅሐፍ, 12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 08:32:42
አዲስ መጽሐፍ ጥቆማ
" ኦሪት ዘፍጥረት ማብራሪያ "
ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን የመጽሐፍ ልገሳ ተደረገ።

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ "እኔ የተዋሕዶ ድምፅ ነኝ! እናንተስ?" ዘመቻ ማጠናቀቂያ ላይ እንደተናገሩት መምህር ያረጋል አበጋዝ "ኦሪት ዘፍጥረት ማብራሪያ" የተሰኘ መጽሐፍ ጽፈው ሙሉ ገቢውን ለጣቢያው ማበርከታቸውን ገልጸዋል።

ዋና ጸሐፊው አክለውም ስለተደረገው ልገሳ አመስግነዋል።

መምህር ያረጋል አበጋዝ "መድሎተ ጽድቅ" ተከታታይ ቅጾችን ጨምሮ በርካታ መጽሐፍት የጻፉ ሲሆን "ብሉይ ኪዳን" በሚባለው የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መርሐ ግብር ላይ ከ4 ዓመት በላይ በተከታታይ እያስተማሩ ይገኛሉ።

መጽሐፉ ታትሞ ስርጭት ላይ ሲሆን ዋና አከፋፋይ አርጋኖን መጽሐፍ መደብር ነው።

ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ለ1 ወር የቆዬ ገቢ አሰባሰብ ላይ መሆኑ ይታወቃል።

ሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ማንኛውንም መፅሐፎች ከልዩ ቅናሽ ጋር ይዘዙ።
Order the book all over the world with fair price and fast delivery

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

   @Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
461 viewsኖኀ መፅሐፍ, 05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 07:01:38 አንዳንድ ሰዎች የተለየ የህይወት ጫወታ ይጫወታሉ፤ ሁሌም በህብረተሰቡ ዉስጥ የሚነገረን ሰዉ ስኬታማ ለመሆን ተምሮ ፡ዲግሪ ይዞ ፡አግብቶ ጥሩ ስራ ይዞ መኖር እንዳለበት ነዉ፡፡ ግን ህይወትን በሌላ ትምህርት፡ በሌላ ዲግሪ፡ በሌላ ስራ ይተዋወቋታል

  የሆነ ነገር ለማግኘት በፈለክ ቁጥር የበለጠ እየራቀህ ይሄዳል፡፡ በህይወቴ ከተረዳሁት ነገር ዉስጥ የፈለኩት ነገር ጥሎኝ ሲሄድ አይቻለሁ፡፡

  ሰዎች ህይወታቸዉን ሊያደላደሉ ሲጥሩ አያለሁ፡፡ ቦታ ካስያዙት በኋላ ሁሉም ነገር ወደነሱ እንደሚመጣ ያስባሉ ነገር ግን ይህ በገሃዱ አለም የማይሆን ነገር ነዉ፡፡

  ሰዎች የሚያወሩትን ሳይሆን የሚያደርጉትን አስተዉል፡፡ ሰዎች አቁስለዉኛል ምክንያቱም ተግባራቸዉን አተኩሬ ጊዜ ስላልሰጠሁት ዉስጤን አደሙት!

  ከሚሰጡት በላይ የሚቀበሉ ሰዎችን አትታገሳቸዉ፡፡ ከሚጠቅሙበት ነገር በበለጠ የሚጎዱበት ማንነታቸዉ የጎላ ሰዎችን ከህይወትህ ካላወጣሃቸዉ ውስጥህን እንደ'ብል'ይበሉታል

  ብዙ መሰናክሎች እራስህ የምትፈጥራቸዉ ናቸዉ፡፡ ማህበረሰቡ፣ ጓደኞቼ ወይም ቤተሰቦቼ መሰናክል እንደሆኑብኝ አምን ነበር ግን በመስታወት የማየዉ ማንነቴ እርስ በእርሱ ተሰነካክሏል፡፡

  ህይወት አጭር ናት፡፡ ሞት ደግሞ የማይቀር ጉዳይ ነዉ፡፡ ይህን ማሰብ ላትፈልግ ትችላለህ ግን አንድ ቀን ትሞታለህ፡፡ አንተ ብቻ ሳትሆን የምታየዉ ሰዉ ሁሉ ቀኑን ጠብቆ ይሞታል፡፡ ስለዚህ ሕይወትህን እስከ እንጥፍጣፊዋ ድረስ ኑርባት!

  መልካም መልካሙን እናስብ፤ እንናገር፤ እንተግብር፡፡ መልካም ህይወት ይገጥመናልና፡፡

                              #አናንያ

             መልካም አሁን


"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
515 viewsኖኀ መፅሐፍ, edited  04:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 21:44:02
መጽሐፍ ጥቆማ
" መዝገበ በረከት ዘሰሙን ቅድስት "
ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙ

ዲ/ን ሕሊና በለጠ እይታ

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የሱታፌ ቤት ናት።
የቤተክርስቲያንን ዶግማ ለሃይማኖት አካል እንደ አጽም (skeleton) ብንወስደው: የአበው አስተምህሮ ደግሞ እንደ ሥጋ (flesh) ነው። ተማህልሏዊነት (mysticism) ደግሞ ለዚህ አካል እንደ የደም ዝውውር ነው። የደም ቱቦውም ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ነው። የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት: በዶግማ አጥንትነት የቆመን፣ በትምህርተ አበው ሥጋነት መልክዕ የያዘን የምሥጢርን ደም እያፈሰሰ ከእርካታው የሚያሳትፈን የምሥጢር ቧንቧችን ነው። ደሙና የደም ቧንቧው ከሌሉ: ረቂቃኑ አጥንቱና ሥጋውም ለእኛ ለግዙፋኑ ባዕድ ይኾናሉ።

ምሥጢርና ሥርዓት ግዘፍ ነሥተው ከሚታዩባቸው የቤተ ክርስቲያናችን የአምልኮ ጊዜያት ዋናዎቹ ደግሞ ሰሙነ ሕማማትና ሰሙነ ትንሣኤ ናቸው። ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙም መጻሕፍትን አናዝዘውና ቀደምት አበውን አናግረው ከአኃትና ከምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ጋር እያናጸሩ በዚህ መጽሐፍ ያቀረቡልን: ኹሉም ሰው የሚናፍቃቸውን  የእነዚህን ጊዜያት ምሥጢርና ሥርዓት ነው።

እነሆ የሕማሙን ሱታፌ ወደ ቀራንዮ ወስዶ የሚያሳትፈን የደም ሥር የኾነ መጽሐፍ!

ሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ማንኛውንም መፅሐፎች ከልዩ ቅናሽ ጋር ይዘዙ።
Order the book all over the world with fair price and fast delivery

Free Delivery
መፅሐፉን ለማዘዝ

   @Noahbook7 0939115238

"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
668 viewsኖኀ መፅሐፍ, 18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 12:17:31 በአንድ ወቅት የከተማዋ ገዢ የሆነው ንጉስ ለሕዝቡ

" የሁላችሁም ጠላት የሆነ ሰው ሞቷል ስለዚህ ለትምህርት እንዲሆናችሁ በሬሳ ሳጥን ውስጥ ተቀምጦላችኃል ሁላችሁም መጥታችሁ እንድትመለከቱ " የሚል አዋጅ አስነገረ

የሁላችንም ጠላት ሊሆን የቻለው ሰው ማነው ? በሚል ብዙ የከተማው ህዝብ በሬሳው ሳጥን ውስጥ ያለውን ለማየት በመጏጏትና በመገረም ስሜት ወደ ቦታው ሄደ ብዙዎች ባዩት ነገር በመገረም አንዳንዶች ደግሞ ግራ የመጋባት ስሜት ይስተዋልባቸዋል

ህዝቡ በሳጥን ውስጥ ያየው ምን ይመስላችኃል?

በሬሳ ሳጥን ውስጥ የተቀመጠው ሰይጣን አሸባሪ አደገኛ ነፍሰ ገዳይ  ወይም ክፋ ሰው ሳይሆን የራስን መልክ መመልከቻ መስታወት ነበር :: ሁሉም ሰው ጎንበስ ብሎ ጠላቱን ሲፈልግ የሚያገኘው የራሱን ፊት ነበር:: ንጉስ ይህን ያደረገበት ምክንያት ሁሉም ሰው የራሱ ጠላት ራሱ መሆኑን ለማስተማር ስለሆነ ነው::

አንድ ግጥም አለ ገጣሚው ሰለሞን ሞገስ ይባላል እንዲም ይላል

ጠላቴን ስፈልግ ከጎረቤቶቼ
ጠላቴን ስፈልግ ከባልደረቦቼ
ጠላቴን ስፈልግ ከሩቅ ከቅርቦቼ
ለካስ ክፉ ጠላት ደመኛዬ ያለው
ከገዛ እኔነቴ ከራሴ ውስጥ ነው !!!    

ብዙዎቻችን ጠላት በዛብኝ እንጂ ጠላት አብዛሁ አንልም ሰው አይመቸኝም እንጂ አልመቸውም ማለት ይከብደናል የራስን ስህተት ማወቅ ትልቅ መሆኑን አንረዳም

ራሳችንን ስለማንወድ ሌላውን መውደድ ራሳችንን ስለማንቀበል ሌላውን መቀበል ይከብደናል እነዚህ ሁሉ ተግባሮች እራስን መግዛት ታላቁ  ግዛት መሆኑን ማሳያ ነው

መደምደሚያ  ቻይናዊው ጥበበኛ  " ሌሎችን የሚቆጣጠር ጠንካራ ሲሆን ራሱን የሚቆጣጠር ግን ኃያል ነው.... ሌሎችን አውቃለው የሚል ብልጥ ሲሆን ራሱን የሚያውቅ ግን ብልህ ነው" ይለናል

ራሳችንን በመግዛት በራሳችን ላይ እንንገስ

     ።።።።።።።።ውብ አሁን።።።።።።።


"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery
634 viewsኖኀ መፅሐፍ, 09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ