Get Mystery Box with random crypto!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ne_siha_eslamik — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ne_siha_eslamik — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የሰርጥ አድራሻ: @ne_siha_eslamik
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.26K
የሰርጥ መግለጫ

بسم الله الرحمن الرحيم
📮እንኳን ወደዚህ ቻናል ተቀላቀሉ‼️
በዚህ ቻናል ቂርአቶችን፣ ሙሐድራዎችን፣ዳዐዋዎችን እና ሌሎችንም ከአረብገንዳ መስጊድ በአሚሩ አማካኝነት በቀጥታ የምታገኙበት ቻናል ነው።
ሃሳብ አስተያዬት ካለ በዚህ ያድርሱን ⤵️
@ye_Arebgenda_mesgid_wetatoch_bot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-09-19 20:50:17 ይህን ያውቁ ኑሯል

ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ኢስራ ወል ሚዕራጅ ደርሰው ሲመጡ በየሰማያቱ እነማንን እንዳገኙ...

:➊. 1ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ አደም (ዐ.ሰ)

➋. 2ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ የህያ (ዐ.ሰ) እና ኢሳ(ዐ.ሰ)

➌. 3ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ዩሱፍ (ዐ.ሰ)

➍. 4ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ኢድሪስ (ዐ.ሰ)

➎. 5ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ሃሩን ቢን ኢምራን (ዐ.ሰ)

➏. 6ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ሙሳ ቢን ኢምራን (ዐ.ሰ)

➐. 7ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ)……ናቸው፡፡
http://t.me//@arebgendamesjid
SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
609 views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-18 18:39:21 #አንብቤው_ከተመቸኝ_ላካፍላችሁ!
#ክፍል_ሁለት

ሀዘን እና ትካዜ ወደ ኋላ ጣላቸው!


ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለት እንዲህ ይላል፦
"ሀዘን ቁርኣን ውስጥ በክልከላ መልኩ ወይም በማራቅ መልኩ ቢኾን እንጂ አልተጠቀሰም
ልክ አላህ እንዳለው

{ وَلَا تَهِنُوا وَلَا تَحْزَنُوا }
{አትስነፉ አትዘኑም}


{ فَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ }
{ፍርሃት የለባቸውም፤ እነርሱም አያዝኑም}"

የዚህ ሁሉ ሚስጥሩ
ሸይጣን ከሚያስደስተው ነገር ሁሉ ትልቁ ሙዕሚን የኾነ ሰው አዝኖ ማየቱ ነው። ከዚያም ከመንገዱና ከጉዞው ሊገታው።

በእርግጥም ነብዩ ሙሐመድ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከሐዘን ተጠብቀዋል
"اللهم إني أعوذ بك من الهم والحزن"
[አላህ ሆይ እኔ ከሀዘንና ከጭንቀት በአንተ እጠበቃለሁ] በማለት


ኢብኑል ቀይም በድጋሚ እንዲህ ይላል፦
"ሀዘን ብሎ ማለት
ቀልብን ያደክማል፣ ቆራጥነትን ያከሽፋል፣ ፍላጎትን ይጎዳል፣ ወደ ሸይጣንም ምንም ተወዳጅ ነገር የለም ሙዕሚን አዝኖ እንደ ማየት"


ስለኾነም፦
ሀዘንን ራቁ!
   መልካምን ከጅሉ!
      በአላህ ላይ መልካም ግምት ይኑራችሁ!
       አላህ ዘንድ ባለው ተማመኑ
          በአላህም ላይ ተመኩ
              በአላህ ፍቃድ በሁሉም ሁኔታ ደስተኞች ትኾናላችሁ


ብትመለከት፦
አላህ ብዙ ነገራቶች ሳትጠይቀው ሰጥቶሃል። ስለዚህ አላህ የምትፈልገውን ነገር እንደ ማይከለክልህ እርግጠኛ ሁን። ምን አልባት ግን አለ መሰጠትህ የተሻለልህ ካልኾነ በስተቀር።


ምን አልባት፦
አንተ ተኝተህ ሳለህ የሰማይ በሮች ላንተ ዱዐ በሚያደርጉልህ ሰዎች እየተንኳኩልህ ይኾናል።

ድሃ ኾኖ የረዳኸው፣
  አዝኖ ያስደሰትከው፣
    የተጣበበ ኾኖ ያቃለልክለት፣
       እያለፈ ብቻ ፈገግ ያልክለት

እጁን ዘርግቶ እየለመነልህ ሊኾን ይችላል።

መልካምን ከመስራት መቼም አትቆጠብ


ከቀደምቶች አንዱ እንዲህ ይላል፦
"አላህ የኾነ ነገር እጠይቀዋለሁ, ያንን ነገር ከሰጠኝ አንዴ እደሰታለሁ፤  ያንን ነገር ካልሰጠኝ ግን አስር ጊዜ እደሰታለሁ፤ ምክንያቱም መሰጠቴ የእኔ ፍላጎት ነበር አለመሰጠቴ ደግሞ የአላህ ፍላጎት ነው።"


ሌላኛው ደግሞ እንዲህ ይላል፦
"ህይወት አጭር ናት።
      በሀዘን፣
         በጭንቀትና
            በጥበት
                አታሳጥራት"

በያላችሁበት የአላህ እዝነትና ጥበቃ አይለያችሁ
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
741 views15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-13 20:23:01 ይህ የረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ታላቅ ምክር ነው።

አንድ ሰው ወደ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) መጣና "ለዱንያም ሆነ ለአኼራ የሚጠቅም ንግግር ለመጠየቅ መጣው" አላቸው።
# እሳቸውም ደግሞ "የመጣልህን ጠይቅ" አሉት።

"ከሰው ሁሉ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለው?"
# እሳቸውም "አላህን ፍራ" አሉት

"ከሰው ሁሉ ሀብታመ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው።
# "ባለህ ነገር ተብቃቅተ አላህን አመስግን" አሉት

"ትክክለኛ ፈራጅ እና ታማኝ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል
# "ለራስህ የምትወደውን ለሰዎች ውደድ"አሉት።

"ከሰው ሁሉ ብርቱ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል
# "በአላህ ተወከል"አሉት

"በአላህ ዘንድ ብቸኛ ተመራጭ ለመሆን
እፈልጋለው" ሲላቸው?
#"ዚክር አብዛ" አሉት።

"ከሰው ሁሉ በላጭ ለመሆን እና ጥሩ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል
# "ለሰው ጠቃሚ ሁን" አሉት።

"የተከበረና ቸር ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው
# "ችግርህን ለፍጡር አትንገር" አሉት።

"ረሱል እና አላህ እንዲወዱኝ እፈልጋለው?" ሲል
#"አንተም እነሱ የወደዱትን ውደድ" አሉት::

"ከወንጀል የጠራው ሁኜ አላህንመገናኘት እፈልጋለው" ሲል
# "ጀናባህን በደንብ ታጥበ እስቲግፋር አብዛ ማልቀስ መተናነስ መታመም አለብህ" አሉት።

"ከበጎ ሰሪወች ለመሆን እፈልጋለው" ሲላቸውም
#"አላህን ልክ እንደምታየው ሁነክ ተገዛው" አሉት።

"ኢማኔ እንዲ ሞላ እፈልጋለው" ሲል
# "ፀባይህን አሳምር" አሉት።

"እርዝቄ እንዲሰፋ እፈልጋለው" ሲል
# "ተዋዱዕ አዘውትር" አሉት።

"ዱዓዬ ሙስተጃብ እንዲሆንልኝ እፈልጋለው?" ሲላቸው
# "ሀራም አትብላ" አሉት::

"አላህን ከሚታዘዙ ሰዎች ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል
# "ግዴታዎችህን ፈፅም" አሉት።

"በአላህ ዘንድ ትልቁ ሀሠና ወይም ደግ ሥራ የቱ ነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው
# "መልካም ፀባይ መተናነስ እና በበላ ላይ ሰብር ማድረግ ነው" አሉት።

"በአላህ ዘንድ የትኛው ስርዓት ነው መጥፎ ሥራ?" ሲል ሲጠይቃቸው
# "መጥፎ ፀባይና ፍላጎትን መከተል ናቸው" አሉት

"በዱንያም ሆነ በአኼራ የአላህን ቁጣ የሚያበርድ ምንድነው" ሲል ጠየቃቸው?
#"ድብቅ ሰደቃ እና ዘርን መቀጠል ናቸው" አሉት።

"የቂያማ ቀን በአላህ ኑር ለመሰብሰብ
እፈልጋለው?" ሲል
# "ሰውን አትበድል" አሉት

"የቂያማ እለት አላህ እንዲያዝንልኝ እፈልጋለው?"
# "ለአላህ ባርያዎች እዘን" አሉት።

"የቂያማ ቀን የጀሀነም እሳት የሚያጠፋው ምንድነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው
# "በችግር ላይ ወይም በሙሲባ ላይ ትህግስት መሰድረግ ነው" አሉት።

"የቂያማ እለት ነውሬ እንዲሸፈንልኝ እፈልጋለው?" ሲል
# "የወንድምህን አይብ ሸፍን" አሉት።

"የቂያማ ቀን ከአላህ ቁጣ ሰላም ለመሆን
እፈልጋለው?" ሲል
# "በአንድም ፍጡር አትቆጣ" አሉት።

*** አላህ ሱብሃን ወተአላህ ባወቅነው. በስማነው የምንስራ ያድርገን አሚን!!!!
http://t.me//@arebgendamesjid
SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
1.1K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 20:43:40 የዑመር ኢብኑልኸጣብ (ረዐ) 20ምርጥ ምክሮች፤
.
1. ‹የምትጠላውን ሰው ተጠንቀቅ፤›

2. ‹ብልጥ ሰው የእለት ስራዎቹን ከራሱ ጋር ይተሳሰባል፡፡

3. ‹የዛሬን ስራ ለነገ አታሳድር፡፡›

4. ‹ከሰዎች ጥያቄ ተነስተህ አስተሳሰባቸውን መለካት ይቻላል፡፡›

5. ‹ለሌሎች ዳዕዋ በምታደርግበት ወቅት እራስህን አትርሳ፡፡›
.
6. ‹ከዱንያ ትንሽን ብቻ ስትፈልግ ይበልጥ ነፃነትን እያገኘህ ትሄዳለህ፡፡›

7. ‹ወንጀል አለመስራት ከፀፀት ይሻላል፡፡›

8. ‹ታጋሽ ሁን፤ ትዕግስት የእምነት ምሶሶ ነችና፡፡›

9. ‹አሏህን ፈሪ መሆን እድለኛነት ነው፤ ከዚህ ውጭ ያለው እድለቢስ መሆን ነው፤›

10. ‹ወደ አኺራ የሄዱ ሰዎችን ንግግር ጠብቁ፤ እነርሱ የተናገሩት አሏህ እንዲናገሩ ያገራላቸውን ብቻ ነውና፡፡
.
11. ‹አሏህን ፍራ፤ እርሱ ሁሌም ህያው፤ ከርሱ ውጭ ያሉ ሁሉ ጠፊ እና አላቂ ናቸውና፡፡

12. ‹ጥፋቴን በነገረኝ ሰው ላይ የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡

13. ‹እውቀትን ገብያት፤ ከዚያም ለሰዎች አስተምር፡፡›

14. ‹የተከበርክ፣ ታማኝ እና እውነተኛ ሁን፡፡›

15. ‹ትምክህተኛ ምሁር አትሁን፤ ትምክህተኛነት እና እውቀት አንድ ላይ አይሄዱምና፡፡
.

16. ‹ለዚህች አለም ፍቅር ያለው አዋቂ ባየህ ግዜ እውቀቱ አጠራጣሪ መሆኑን ተረዳ፡፡›

17. ‹ትንሽ አውርቶ ብዙ በሚሰራ ሰው ላይ የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡›

18. ‹ታማኝነት ማለት በምትሰራው፣ በተናገርከው እና በምታስበው ነገሮች ልዩነት አለመኖር ማለት ነው፡፡

19. ‹የሰው ልጅ ምንም እንኳ እንደ ቀስት ቀጥ ያለ ስራ ቢሰራ ተቃውሞ አያጣውም፡፡›

20. ‹አዕምሮህ እንዲሰፋ ከፈለግክ፤ ከፈሪሀ አሏሆች ጋር ተቀመጥ፤›

ለወዳጆችዎ ሼር በማድረግ ያካፍሉ

SHARE SHARE
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
1.0K views17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 10:27:33
1.1K views07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 15:24:13 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል- የመጨረሻ ክፍል-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
1.1K views12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 21:57:04 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

የመጨረሻ ክፍል
  
የአል-ፋሩቅ መተካት

የአቡበክር አስ-ሲዲቅ ሞት ምክንያት ላይ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰንዝረዋል፡፡ የሞቱት ከፍተኛ ቅዝቃዜ ባለው ውሃ በመታጠባቸው ምክንያት ብርድ በሽታ ታመው ነው የሚሉ እንዳሉ ሁሉ የለም እርሳቸው የሞቱት አንድ አይሁዳዊ የተመረዘ ምግብ አብልቷቸው ለአስራ አምስት ቀናት ያህል ታመው ነው የሚሉም አሉ፡፡ ..

ይህ በእርግጥ ለአይሁዶች አዲስ አይደለም፡፡ ብዙ ነብያትን የመግደል ልምድ አካብተዋል፡፡ ሰይድ ኢሳን (ዐ.ሰ) ለመግደል ሞክረዋል፡፡ ነብዩን (ሰዐ.ወ) ሶስት ጊዜ ለመግደል ሞክረው አልተሳካላቸውም፡፡ ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር አድርገው ለዑመር ቢን አል ኸጣብ፣ ለዑስማን ቢን ዓፋን ለጦልሃና ለዙበይር መገደል ምክንያት የሆኑት አይሁዳዊያን ናቸው፡፡

ሰይድ አቡበክር ላይ ሕመም በጠናባቸው ጊዜ ሶሃቦች በርሳቸው ቦታ ላይ ሰይድ ዑመርን እንዲተኩ እያማከሯቸው ነበር፡፡ አስ-ሲዲቅ ዓብዱራህማን ቢን ዓውፍን ስለ ዑመር ሲጠይቋቸው እንዲህ ሲሉ መለሱ፡፡ «አንቱ የረሱል ኸሊፋ ሆይ ዑመር ከምናስባቸው በላይ ጥሩ ሰው ናቸው።››

ዑስማንን ሲጠይቋቸው ደግሞ እንዲህ አሉ... “ከላያቸው በተሻለ ውስጣቸው ጥሩ እንደሆነ አስተምረውኛል፡፡” አቡበክር ሌሎችንም ታላላቅ ሶሃባዎችን ሲያማክሯቸው በጉዳዩ ላይ ተስማሙ።

አንዳንድ ስዎች ደግሞ እንዲህ አሏቸው “ዑመር ኃይለኛነት አለባቸው፡፡ አላህ እንዴት ኸሊፋ አደረግካቸው ብሎ ቢጠይቅዎ ምን ሊመልሱ ነው” አቡበክርም ተቆጡና እንዲህ አሉ... “ደግሞ በአላህ ታስፈራሩኛላችሁ... ወላሂ አላህ ቢጠይቀኝ ከምርጥ ሰዎችህ ምርጥ የሆነውን በእኔ ቦታ ተክቼዋለሁ ብዬ እመልስለታለሁ፡፡”

ከዚያም አቡበክር ዑስማን ቢን ዓፋንን(ረ.ዐ) አስጠሯቸውና እንደሚከተለው እንዲጽፉ አዘዟቸው፡፡... “ይህ ኑዛዜ ከዱኒያ ለመጨረሻ ጊዜ ሲሰናበት ወደ አኼራ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሄድ አቡበክር ቢን አቢ ቁሃፉ ያስተላለፈው ትዕዛዝ ነው። ሐሰተኞች እውነት እንዲናገሩ፣ አመጸኞች አደብ እንዲገዙ፣ ከሃዲዎች እንዲያምኑ ስል ይህን ትዕዛዝ አስተላልፌያለሁ... ተክቼላችኋለሁ...” የተኩትን ሰው በስም ሳይጠቅሱ ራሳቸውን ይስታሉ።

ሰይድ ዑስማን “ዑመር ቢን አል-ኸጧብን ተክቼላችኋለሁ...” የሚል ዓረፍተ ነገር ጻፉ። ዑስማን ይህን ያደረጉት አስ-ሲዲቅ የተኩትን ስው በግልጽ ሳይናገሩ ካለፉ በሙስሊሞች መካከል ውዝግብ ይፈጠራል ብለው ሰግተው ነው። በተጨማሪም አቡበክር( በርሳቸው ቦታ መተካት ያለበት ሰው ማን እንደሆነ መወሰናቸውን ዑስማን(ረ.ዐ) ስለሚያውቁ፡፡

አስሲዲቅ(ረ.ዐ) ትንሽ መለስ እንዳሉ ዑስማን(ረ.ዐ) የጻፉትን እንዲያነቡላቸው አዘዟቸው... “በእኔ ቦታ ዑመር ቢን አል-ኸጣብን ተክቼላችኋለሁ፡፡” የሚለውን አነበቡ። በዚህ ጊዜ ሰይድ አቡበክር እንዲህ አሉ... “አሏሁ አክበር! የተካሁትን ሰው በስም ሳልናገር ሕይወቴ ብታልፍ ሙስሊሞች ይጨቃጨቃሉ ብለህ ስግተህ ነበር ማለት ነው? ለእስልምና እና ለሙስሊሞች ለዋልከው ውለታህ አላህ መልካም ምንዳ ይክፈልህ ዑስማን”

ከዚያም አስ-ሲዲቅ ሶሃቦች እንዲሰባሰቡ አደረጉና እንዲህ አሏቸው... “እናንተ ሰዎች ሆይ! እኔ ዱኒያን ተሰናብቼ ወደ አኼራ መጓዜ ነው፡፡ በዚህ ወረቀት ውስጥ እኔን የሚተካ ሰው ገልጬላችኋለሁ፡፡ እርሱን ስሙት ታዘዙትም፡፡ እኔ ለእናንተ የመረጥኩላችሁን ስው ትቀበሉታላችሁን?” ብለው ሲጠይቁ ሁሉም በህብረት “ተደስተናል” አሉ።

ዓሊይ ቢን አቢ ጧሊብ(ረዐ) ተነሱና እንዲህ አሉ... "ዑመር ካልተሾሙ በቀር አንደሰትም...” አስ-ሲዲቅ ፈገግ አሉና "የተሾመው ዑመር ቢን አል-ኸጣብ ነው፡፡ ስሙት ታዘዙትም። ወላሂ ስለርሱ መልካምን እንጂ ሌላ የማውቀው ነገር የለኝም”

     የወዳጆች መመሳሰል

አቡበክር ዛሬ ቀኑ ማነው” ሲሉ ጠየቁ፡፡ “ሰኞ ነው” አሏቸው “ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በምን ቀን ነበር ያለፉት" ሲሉ አከሉ፡፡ ሰኞ ቀን፡፡ አቡበክርም እንዲህ አሉ “እላህ ሆይ ሞቴን በዚችው ሌሊት አድርግልኝ ከዚያም እንዲህ ጠየቁ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የተከፈኑት በምን ዓይነት ከፈን ነበር” የተከፈኑበትን ነገሯቸው፡፡ “እኔንም በዚያው ዓይነት ከፍኑኝ፡፡ አስክሬኔንም ባለቤቴ አስማእ ቢንት ዑመይስ ትጠበኝ...”

      የአስ-ሲዲቅ ጉዞ
እሜቴ ዓኢሻ ወደ ቤት ገብታ ማልቀስ ስትጀምር አስ-ሲዲቅ ከለከሏት። ከዚያም አጠገባቸው ተቀምጣ ግጥሞችን ትገጥም ጀመር፡፡ አቡበክርም ዓኢሻን እሱን ተይና እንዲህ የሚለውን የቁርኣን አንቀጽ አንብቢ

وَجَاءَتْ سَكْرَةُ الْمَوْتِ بِالْحَقِّ ۖ ذَٰلِكَ مَا كُنتَ مِنْه تَحِيدُ (١٩) وَنُفِخَ فِي الصُّورِ ۚ ذَٰلِكَ يَوْمُ الْوَعِيدِ (٢٠)
"የሞትም መከራ እውነቱን ነገር ታመጣለች፡፡ (ሰው ሆይ)፡- «ይህ ያ ከርሱ ትሸሸው የነበርከው ነው» (ይባላል)፡፡ በቀንዱም ውስጥ ይንነፋል፡፡ ያ (ቀን) የዛቻው (መፈጸሚያ) ቀን ነው፡፡" (ቃፍ 19-20)

አስ-ሲዲቅ በመሞቻቸው ዕለት የተናገሯት የመጨረሻዋ ንግግር እንዲህ የምትል ነበረች... "ሙስሊም አድርገህ ግደለኝ፣ ከመልካሞቹም ጋር አስጠጋኝ፡፡" አቡበክር የሞቱት ሰኞ ሌሊት ነበር፡፡ በጀናዛቸው ላይ ያስገዱት ዑመር ቢን አል-ኸጣብ(ረ.ዐ) ናቸው፡፡ መላው የመዲና ከተማ በአቡበክር ሞት ምክንያት ስታነባ ዋለች፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ካረፉበት መካነ መቃብር አጠገብ ተቀበሩ፡፡ ዓሊይ ቢን አቢጧሊብ(ረ.ዐ) ወደ መቃብሩ ተጠጉና እንዲህ አሉ። “አቡበክር ሆይ አላህ ይዘንልህ፡፡ ወላሂ ከሙስሊሞች አንደኛ አንተ ነበርክ፡፡ በኢማን ጥልቀትና ጥንካሬ አንተን የሚያክል የለም፡፡ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) በመንከባከብ፣ እስልምናን በመጠበቅ ወደር አልነበረህም፡፡ ለሙስሊሞች ሩህሩህ ነበርክ፡፡ ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ጋር በአፈጣጠርም፣ በስነምግባርም፣ በግርማ ሞገስም ተመሳሳይ ነበርክ፡፡ ለእስልምና እና ለረሱል (ሰ.ዐ.ወ) የከፈልከውን ውለታ አላህ በመልካም ይመልስልህ። ስዎች ረሱልን (ስ.ዐ.ወ) እምቢ ሲሏቸው ኣንተ አስተናገድካቸው። ተቀበልካቸው፡፡ ሲያገሏቸው አንተ አቀረብካቸው፡፡ ምን ጊዜም ከጎናቸው ነበርክ፡፡ አላህ (ሱ.ወ) በመጽሐፉ እውነተኛ ብሎ ጠርቶሃል. “ያም በእውነት የመጣው በርሱ ያመነውም” ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ያመጡትን እውነት እውነት ብለህ የተቀበልከው አንተ ነህ፡፡ ወላሂ ለእስልምና ጋሻና መከታ፣ ለከሓዲያን ደግሞ ቅጣት ነበርክ፡፡ ጎርፍም ሆነ አውሎ ንፋስ የማያናጋው ተራራ ነበርክ፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ስለ አንተ እንደተናገሩት ሰውነትህ ለስላሳ ቢሆንም በአላህ ትዕዛዝ ላይ ግን ጠንካራ ነበርክ፡፡ ለራስህ የምትተናነስ ብትሆንም አላህ ዘንድ ግን ከፍ ያልክ ነህ፡፡ በምድር ላይ ኃያል፣ ሙስሊሞች ዘንድ ደግሞ ታላቅ ነበርክ፡፡ ለእኛ የዋልከውን ውለታ አላህ በመልካም ይመልስልህ፡፡ ባንተ ላይ ቂምም ሆነ ብሶት ያለበት ሰው የለም፡፡ ደካማ የድርሻውን እስካላገኘ ድረስ አንተ
ዘንድ ኃያል ነበር፡፡ ኃያሉ የሌሎችን ድርሻ እስኪሰጥ ድረስ አንተ ዘንድ ደካማ ነበር፡፡ ምንዳህን አላህ አይከልክለን፡፡ ካንተ በኋላም አያጥምመን፡፡”

  ረ ዲ የ ሏ ሁ  ዐ ን ሁ

ምስጋና ይገባው ለአሏህ ﷻ ይህን ታሪክ አስጀምሮ ላስጨረሰን
http://t.me//@arebgendamesjid
        እዚጋ  ተጠናቀቀ

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
84 views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 11:22:31 #ተውበት (ወደ አላህ መመለስ)
ተዉበት በሠራነዉ ስራ ተፀፅተን ወደአላህ መመለስ ከፈጣሪ ምህረትን መጠየቅ
ነው ይችን ዱኒያ ዛሬ ይሁን ነገ መቸ እንደምንለያት አናቅምና ሁሌም መች እና
እንደት እንደሚመጣብን ለማናዉቀዉ ሞት ማስታወስ ግድ ነው በየትኛዉ ሠከንድ
እንደሚመጣ የአላህ ቀጠሮ አናዉቅምና
ተውበት (ወደ አላህ መመለስ)

#ተውበት፡- በአላህ ትእዛዝ ላይ ከማመፅ ለህግጋቱ ወደ መታዘዝ. መመለስ ነው፡፡

#ተውበት፡- ተውበት አላህዘንድ በጣም የተወደደ ነው።
‹‹… ﺇِﻥَّ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻳُﺤِﺐُّ ﺍﻟﺘَّﻮَّﺍﺑِﻴﻦَ ﻭَﻳُﺤِﺐُّ ﺍﻟْﻤُﺘَﻄَﻬِّﺮِﻱﻥَ
‹‹ ....አላህ (ከኃጢኣት) ተመላሾችን ይወዳል፤ ተጥራሪዎችንም ይወዳል
በላቸው፡፡››
አል በቀራህ 222
ተውበት በእያንዳንዱ አማኝ ላይ ግዴታ ነው፡፡
አላህ እንድህ ይላል:-
ﻳَﺎ ﺃَﻳُّﻬَﺎ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺗُﻮﺑُﻮﺍ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺗَﻮْﺑَﺔً ﻧَّﺼُﻮﺣًﺎ ﻋَﺴَﻰٰ ﺭَﺑُّﻜُﻢْ ﺃَﻥ ﻳُﻜَﻔِّﺮَ ﻋَﻨﻜُﻢْ ﺳَﻴِّﺌَﺎﺗِﻜُﻢْ
ﻭَﻳُﺪْﺧِﻠَﻜُﻢْ ﺟَﻨَّﺎﺕٍ ﺗَﺠْﺮِﻱ ﻣِﻦ ﺗَﺤْﺘِﻬَﺎ ﺍﻟْﺄَﻧْﻬَﺎﺭُ ﻳَﻮْﻡَ ﻟَﺎ ﻳُﺨْﺰِﻱ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﺍﻟﻨَّﺒِﻲَّ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﻣَﻌَﻪُ ۖ
ﻧُﻮﺭُﻫُﻢْ ﻳَﺴْﻌَﻰٰ ﺑَﻴْﻦَ ﺃَﻳْﺪِﻳﻬِﻢْ ﻭَﺑِﺄَﻳْﻤَﺎﻧِﻪِﻡْ ﻳَﻘُﻮﻟُﻮﻥَ ﺭَﺑَّﻨَﺎ ﺃَﺗْﻤِﻢْ ﻟَﻨَﺎ ﻧُﻮﺭَﻧَﺎ ﻭَﺍﻏْﻔِﺮْ ﻟَﻨَﺎ ۖ ﺇِﻧَّﻚَ ﻋَﻠَﻰٰ
ﻛُﻞِّ ﺷَﻲْﺀٍ ﻗَﺪِﻳﺮٌ
‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ ንፁህ የኮነችን ፀፀት በመፀፀት ወደ አላህ
ተመለሱ…..››
አል ተህሪም 8
‹‹… ﻭَﺗُﻮﺑُﻮﺍ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺟَﻤِﻴﻌًﺎ ﺃَﻳُّﻪَ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﻟَﻌَﻠَّﻜُﻢْ ﺗُﻔْﻠِﺤُﻮﻥَ
‹‹ ... ምእመናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ)
ተጸጸቱ፡፡››
ሱረት አል-ኑር 31
መድህን (ፈላህ) ማግኘት ማለት አንድ ሰው የፈለገውን ማግኘት የሚፈራውን
ነገር መዳን ነው፡፡
ፍፁምና እውነተኛ የሆነ ተውበት፡- ኃጢአቱ የፈለጉትን ያህል ቢከብድና ቢበዛም
እንኳን አላህ # ፍፁምና_እውነተኛ ከሆነ ተውበት ኃጢአቶችን ሁሉ ይቅር ብሎ
ምህረት ያደርጋል፡፡
۞ ﻗُﻞْ ﻳَﺎ ﻋِﺒَﺎﺩِﻱَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺃَﺳْﺮَﻓُﻮﺍ ﻋَﻠَﻰٰ ﺃَﻧﻔُﺴِﻬِﻢْ ﻟَﺎ ﺗَﻘْﻨَﻄُﻮﺍ ﻣِﻦ ﺭَّﺣْﻤَﺔِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ۚ ﺇِﻥَّ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻳَﻐْﻔِﺮُ
ﺍﻟﺬُّﻧُﻮﺏَ ﺟَﻤِﻴﻌًﺎ ۚ ﺇِﻧَّﻪُ ﻫُﻮَ ﺍﻟْﻐَﻔُﻮﺭُ ﺍﻟﺮَّﺣِﻴﻢُ
በላቸው «እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት
ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው
አዛኙ ነውና፡፡
አል-ዙመር - 53
http://t.me//@arebgendamesjid
SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
195 views08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 21:19:12 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-21-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
131 views18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:53:24 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-20-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
273 views17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ