ይህ የረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ታላቅ ምክር ነው። አንድ ሰው ወደ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) መጣና "ለዱንያም ሆነ ለአኼራ የሚጠቅም ንግግር ለመጠየቅ መጣው" አላቸው። # እሳቸውም ደግሞ "የመጣልህን ጠይቅ" አሉት። "ከሰው ሁሉ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለው?" # እሳቸውም "አላህን ፍራ" አሉት "ከሰው ሁሉ ሀብታመ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው። # "ባለህ ነገር ተብቃቅተ አላህን አመስግን" አሉት "ትክክለኛ ፈራጅ እና ታማኝ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል # "ለራስህ የምትወደውን ለሰዎች ውደድ"አሉት። "ከሰው ሁሉ ብርቱ ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል # "በአላህ ተወከል"አሉት "በአላህ ዘንድ ብቸኛ ተመራጭ ለመሆን እፈልጋለው" ሲላቸው? #"ዚክር አብዛ" አሉት። "ከሰው ሁሉ በላጭ ለመሆን እና ጥሩ ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል # "ለሰው ጠቃሚ ሁን" አሉት። "የተከበረና ቸር ሰው ለመሆን እፈልጋለው?" ሲላቸው # "ችግርህን ለፍጡር አትንገር" አሉት። "ረሱል እና አላህ እንዲወዱኝ እፈልጋለው?" ሲል #"አንተም እነሱ የወደዱትን ውደድ" አሉት:: "ከወንጀል የጠራው ሁኜ አላህንመገናኘት እፈልጋለው" ሲል # "ጀናባህን በደንብ ታጥበ እስቲግፋር አብዛ ማልቀስ መተናነስ መታመም አለብህ" አሉት። "ከበጎ ሰሪወች ለመሆን እፈልጋለው" ሲላቸውም #"አላህን ልክ እንደምታየው ሁነክ ተገዛው" አሉት። "ኢማኔ እንዲ ሞላ እፈልጋለው" ሲል # "ፀባይህን አሳምር" አሉት። "እርዝቄ እንዲሰፋ እፈልጋለው" ሲል # "ተዋዱዕ አዘውትር" አሉት። "ዱዓዬ ሙስተጃብ እንዲሆንልኝ እፈልጋለው?" ሲላቸው # "ሀራም አትብላ" አሉት:: "አላህን ከሚታዘዙ ሰዎች ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል # "ግዴታዎችህን ፈፅም" አሉት። "በአላህ ዘንድ ትልቁ ሀሠና ወይም ደግ ሥራ የቱ ነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው # "መልካም ፀባይ መተናነስ እና በበላ ላይ ሰብር ማድረግ ነው" አሉት። "በአላህ ዘንድ የትኛው ስርዓት ነው መጥፎ ሥራ?" ሲል ሲጠይቃቸው # "መጥፎ ፀባይና ፍላጎትን መከተል ናቸው" አሉት "በዱንያም ሆነ በአኼራ የአላህን ቁጣ የሚያበርድ ምንድነው" ሲል ጠየቃቸው? #"ድብቅ ሰደቃ እና ዘርን መቀጠል ናቸው" አሉት። "የቂያማ ቀን በአላህ ኑር ለመሰብሰብ እፈልጋለው?" ሲል # "ሰውን አትበድል" አሉት "የቂያማ እለት አላህ እንዲያዝንልኝ እፈልጋለው?" # "ለአላህ ባርያዎች እዘን" አሉት። "የቂያማ ቀን የጀሀነም እሳት የሚያጠፋው ምንድነው?" ብሎ ሲጠይቃቸው # "በችግር ላይ ወይም በሙሲባ ላይ ትህግስት መሰድረግ ነው" አሉት። "የቂያማ እለት ነውሬ እንዲሸፈንልኝ እፈልጋለው?" ሲል # "የወንድምህን አይብ ሸፍን" አሉት። "የቂያማ ቀን ከአላህ ቁጣ ሰላም ለመሆን እፈልጋለው?" ሲል # "በአንድም ፍጡር አትቆጣ" አሉት። *** አላህ ሱብሃን ወተአላህ ባወቅነው. በስማነው የምንስራ ያድርገን አሚን!!!! http://t.me//@arebgendamesjid SHARE SHARE የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ 1.1K views17:23