Get Mystery Box with random crypto!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ne_siha_eslamik — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ne_siha_eslamik — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የሰርጥ አድራሻ: @ne_siha_eslamik
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.26K
የሰርጥ መግለጫ

بسم الله الرحمن الرحيم
📮እንኳን ወደዚህ ቻናል ተቀላቀሉ‼️
በዚህ ቻናል ቂርአቶችን፣ ሙሐድራዎችን፣ዳዐዋዎችን እና ሌሎችንም ከአረብገንዳ መስጊድ በአሚሩ አማካኝነት በቀጥታ የምታገኙበት ቻናል ነው።
ሃሳብ አስተያዬት ካለ በዚህ ያድርሱን ⤵️
@ye_Arebgenda_mesgid_wetatoch_bot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2022-08-22 20:48:09 ለየት ያሉ ሰሐቦች
▬▱▬▱▬▱▬

አቡ ኡበይዳ ዓምር ኢብኑ አል ጀራህ
በኡሁድ ጦርነት አባቱን የገደለ ሰሃባ

ኡሰይድ ኢብኑ ሁደይር
ቁርዓን ሲቀራ መላኢኮች ድምፁን ሊሰሙ ከሰማይ የወረዱለት ሰሐባ።

ዒምራን ኢብኑ ሁሰይን
በታመመ ጊዜ መላሂኮች አሰላሙ ዐለይኩም ያሉት ሰሐባ።

ዐብደላህ ኢብኑ ዐባስ
ከታላላቅ ሰሐቦች ጋር ለሹራ ይቀመጥ የነበረ ወጣት ሰሐባ።

ዐብደላህ ኢብኑ ሰላም
አይሁዳዊ ሰሐባ

ደህየተል ከልቢ
ጅብሪል ዐለይህ ሰላም ብዙ ግዜ በርሱ ተመስሎ የሚመጣ መልከ መልካም ሰሃባ።

ዑስማን ኢብኑ ጠለሃ
የመካ መከፈት ቀን ነቢዩ የከዕባን ቁልፍ ያስረከቡት ሰሃባ።

ዑመር ኢብኑ አል ኸጣብ
ሸይጧን በፍራቻ መንገድ የሚለቅለት ሰሐባ።

ዑካሽ ኢብኑ መህስን
ያለ ምርምር ና ያለ ቅጣት ጀነትን ከሚገቡ 70ሺህ ሰዎች መካከል እንደሆነ ነብዩ የመሰከሩለት ሰሐባ።

ኡሰይርም ኢብኑ አብዱል አሽሀል
በኡሁድ ጦርነት የሠለመ አንዲትም ሱጁድ ሳያደርግ ጀነት የገባ ሰሐባ።
http://t.me//@arebgendamesjid
SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
613 views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 21:24:45 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
ክፍል-6-
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
823 views18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 22:43:16 ከዑመር (ረዲየላሁ አንሁ) አባባሎች
የተቀነጨበ

"ስለቁርአን ውብነት፣ስለ እውቀት ፋፋቴነት የአላህን ችሮታ ስለ ሚጠይቅ ሰውነት ሁኑ፡፡"

"እናቶቻቸው ነፃ አድርገው የወለዳቸውን ሰዎች ባሪያ አታድርጉ፡፡

መልካም ለሆነላችሁ መልካም ሁኑ፡እኩይ ለሚያስብባችሁ ድክመቱን ተረዱ፡፡"

"ስለ ነገሮች በጥርጣሬ የሚናገር (የሚከውን) ሰው ስለርሱ መጥፎ የሚናገሩ ሰዎችን መቃወም የለበትም፡፡"

"ሰዎችን ባየህባቸው ወቅታዊ ገፅታ እንጂ በዉስጣቸዉ እንዲህ ያስባሉ ብለህ አትዳኝ፡፡"

"ስለሚበልጡት የማይቀና፡ስለሚበልጣቸው የማያዝንና ስለሥራው ዋጋ የማይጠይቅ ሰው ምሁር አይባልም፡፡"

"እስልምና በምሁራን ስህተትና የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት ቁርአንን አጣመው በሚከራከሩ መናፍቃን ይጠፋል፡፡"

"መልካም ጎደዬችን ያዙ"

"እውቀትን ፈልጉ የማትፈልጉ ከሆነ ደግሞ አዋቂዎችን ዉደዱ ይህንንም ለማድረግ ከተሳናችሁ ግን ቢያንስ የእውቀት ባለቤቶችን አትጥሉ፡፡"

"ስለፍላጎታችን መሳካት አላህን ካለመታዘዝ የርሱን ፍላጎት ለማሟላት መታዘዙ በላጭ ምንዳ አለው፡፡"

"ሚስጥሩን የደበቀ ሰው ነፃ ለመሆን አማራጭ አለው፡፡ ሚስጥሩን ለአንድ ወይም ለሁለት ሰዎች እያለ የተናገረ ግን ስለሚደርስበት ትችት ማስቆም አይቻልም፡፡"


http://t.me//@arebgendamesjid


SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
362 views19:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 21:01:18 የሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር አሳዛኝ ታሪክ
================================
ሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር ረዲየልሏሁ ዐንሁ እስልምናን ከመቀበሉ በፊት፣
በመካ ሰዎች ዘንድ እጅጉን የተከበረ፣ ተክለ ቁመናው የሚያምር፣ የባለ ሀብት ልጅ ነበር።
ከመቀማጠሉ የተነሳ አንዳንዶች እንደሚሉት፣
በመንገድ ላይ ሲኬድ ዝም ብሎ ሽቶ ከሸተተ፤
በቃ፥ በዚህ መንገድ ሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር አልፏል ይሉ ነበር።

ሙስዐብ ነብያችን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዳሩል አርቀም በነበሩበት ጊዜ መጣ፣ የሚያስተምሩትን አዳመጣቸው።
በትምህርታቸው ተማርኮ እስልምናን ተቀበለ።
ነገር ግን በተለይም እናቱን ስለፈራ እስልምናውን ደበቀ።
በኋላ ግን ሲሰግድ ታይቶ ታወቀበት።ወደ እስልምና ከገቡ የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎች ውስጥ አንዱ ነው።

መገለልና እንግልት ደረሰበት፣ ብዙ ስቃዮችን አሳለፈ።
የመጀመሪያው ወደ ሐበሻ ስደት ጊዜ ሲሰደዱ እርሱም ነበረበት።
በኋላ ደግሞ ወደ መዲና ተሰደተ።
ለመጀመሪያ ጊዜ መዲና ላይ ጁሙዐን የሰገደ ነውም ይባላል።
*
የሙስዐብ ባለቤት የረሱልሏህ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ባለቤት የሆነችው የዘይነብ ቢንት ጀህሽ እህት ነበረች።
ሙስዐብ አንድ ሴት ልጅ ብቻ ነበረችው።

የበድርና የኡሑድን ዘመቻዎች ተሳትፏል።
በኡሑድ ጦርነት ጊዜ አንድ ኢብኑ ቀምኣህ የሚባል ግለሰብ፣ መጀመሪያ እቃ የያዘውን እጁን በሰይፍ ቆረጠው፣ ከዚያም እቃውን በግራው ሲይዝ ግራ እጁንም ቆረጠው፣ በደረቱ ጨምዶ ሲይዝ ደግሞ፥ ደረቱን ወግቶ ገደለው።

ሙስዐብም ሸሂድ ሆነ።

ረሱልሏህ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የሙስዐብን መሞት ሲያዩ፤
ይህን የአላህ ቃል አነበቡ፦
" مِنَ الْمُؤْمِنِينَ رِجَالٌ صَدَقُوا مَا عَاهَدُوا اللَّهَ عَلَيْهِ فَمِنْهُمْ مَنْ قَضَى نَحْبَهُ وَمِنْهُمْ مَنْ يَنْتَظِرُ وَمَا بَدَّلُوا تَبْدِيلًا"

"ከአማኞች በርሱ ላይ ለአላህ ቃል ኪዳን የገቡበትን በእውነት የፈጸሙ ወንዶች አልሉ።
ከነርሱም ስለቱን የፈጸመ (ለኃይማኖቱ የተገደለ) አልለ፤ ከነርሱም ገና የሚጠባበቅ አለ።
(የገቡበትን ቃል) መለወጥንም አልለወጡም።"

[አል አሕዛብ፥ 23]
||
ሙስዐብ ተገድሎ የተገኘ ጊዜ ሶሐቦች ለመከፈን ፈለጉ።
ነገር ግን ሙስዐብ ለእስልምና ብሎ የቅንጦት ህይወቱን ትቶ ስለተሰደተ፣
ከባለብትነት ወደ ደሃነት ተቀይሯል።
የለበሳት አንድ ነጠላ ብቻ ነበረች።
በዚህች ነጠላ ለመከፈን ሲፈልጉ ከማነሷ የተነሳ፣
ራሱን ሲያለብሱት እግሩ ይገለጥባቸውዋል፤
እግሩን ሲያለብሱት (ሲሸፍኑት) ጭንቅላቱ ይገለጥባቸዋል።
أرادوا تكفينه بها، فكانوا إذا غطوا رأسه بدت رجلاه، وإذا غطوا رجليه بدا رأسه!

በመጨረሻም ለረሱልሏህ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "ምን እናድርግ?" ብለው ሲያማክሯቸው፣
ጭንቅላቱን አልብሱትና፣ እግሩ ላይ ቅጠል (ሳር) ጣል አድርጉበት (አልብሱት) አሏቸው።
فقال النبي محمد: «غطوا رأسه، واجعلوا على رجليه من الإذخر»،
ሶሐቦችም በተባለው መሰረት ከፍነው ቀበሩት።

ረዲየልሏሁ ዐንሁ ወአርዷህ
ያ ዝነኛ ቅምጥል ሶሐባ ነው እኮ እንዲህ የሆነው

የሚሄድበት መንገድ እንኳ ሳይቀር ሽቶ ሽቶ እንዳልሸተተ ሁሉ፣
ሲሞት የሚከፈንበት አንድ በቂ ነጠላ እንኳ አጥቶ በቅጠል (ሳር) ተጨምሮ ተከፈነ።

ሀከዘ ዱኒያ ያ አኺ ወ ያ ኡኽቲ

ይህን ያክል ክብራቸውንና ዱኒያቸውን ጥለው የተሰውለትን ዲን ነው እኔና እናንተ ዛሬ የያዝነው።

እኛስ ምን ሰርተን ይሆን

በነርሱ ፈለግ ላይ ነን

ራሳችንን እንጠይቅ!!

http://t.me//@arebgendamesjid

SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
390 views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 22:27:02 . አስተዉሉ እህቶቼ...

#ስንቶቻችን ነን ክብራችንን ምንጠብቀዉ??
ሼር
#እናቴ (ዝሙት) መስራት እፈልጋለሁ...
.
አንዲት ወጣት እንስት እናቷን ዝሙት ትፈጽም ዘንድ ታስፈቅዳታለች።
.
እናትየውም በእርግጥም የፈለግሽውን ነገር ከመፈጸምሽ በፊት
ለአንድ ሳምንት የማዝሽን መፈጸም ይኖርብሻል ስትል አቋሟን
ታሳውቃለታለች።
.
#እናትየውም እንዲህ ስትል ታዛታለች ወደ ንጉሱ ቤተ መንግስት ሂጂና
ልክ
ንጉሱ ከቤተ መንግስት ሲወጣ እራሱን እንደሳተ ሰው ውደቂ
.
#ልጅየውም ልክ እንደተባለችው እራሷን ስታ ትወድቃለች ንጉሱም
እራሱ ከሰረገላው ላይ ወረደና ሙሉ
እንክብካቤ እንዲደረግለትና ቤቷ
እንዲያደርሷት አዘዘ
.
#በሚቀጥለው ቀንም ንጉሱ ከቤተመንግስት ሲወጣ አሁንም
ራሷን ስታ ወድቃለች ንጉሱም ችላ
ብሎ አለፈ ዞር ብሎ እንኳን አልተመለከታትም
.
የንጉሱ ተከታይም ከወደቀችበት አነሳት በሶስተኛው ቀን እሱም
ይተዋትና የዘበኞች አለቃ ያነሳታል
.
#በአራተኛው ቀን አለቃውም ትቷት አንድ ተራ ወታደር ያነሳታል
በሚቀጥለው ቀን ግን እሱም ቀርቶ ሰዎች እየገፉ ወደ ዳር ያወጧታል።
እንደተለመደው በመጨረሻው ቀንም እራሱን እንደሳተ ሰው ወደቀች
.
#ይሄኔ ግን ፊቷን ከሚልሳት ውሻ ውጪ ምንም ነገር አላገኘችም
.
ከዚያም የእናቷ ተግባር የታከለበት ምክሯን እንዲህ ለገሰች
.
በማህብረሰቡ ውስጥ ክብሯን ያጣች ሴት ምሳሌም ይሄው ነው
በመጀመሪያ የተከበረች ሴት
በመሆኗ ሁሉም ይንሰፈሰፍላታል
.
☞ክብሯን ስታጣ ግን ፈላጊዋ ይጠፋል ሁሉም እንዳሻው ይጫወትባታል

☞በመጨረሻ ግን ማንም የማይፈልጋት ርካሽ እቃ ትሆናለች። ስትል
ልጇን
በጥበብ አስተማረቻት።
~~~~
ፈጣሪን መፍራት ጥበብ ነው! ከሀጢያት መራቅ ማስተዋል ነው።

ሴቶች ለወደፊት ትዳር ካሰባችሁ ከዚና መራቅ አለባችሁ

በዚህ በአለንበት ዘመን ሰውን ያንበረከከ ትልቁ ሀጢያት እንደ ቻይና ልብስ የተያዘ ፋሽን ቢኖር "ዝሙት" ነው

እህቶቼ ተጠንቁቁ

SHARE SHARE
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
536 views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 17:29:00

639 views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 17:21:45

682 views14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 22:56:35
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
ተደራሽነት ዕንዲሰፋ ሸር ዕናድርግ። የአጅሩ ተካፋይ ዕንሁን። ሸር ዕያደረግን።
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
771 views19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 22:27:54 የጀግና እናት ምክር!

መካ በአል-ሐጃጅ በተከበበች ጊዜ ኸሊፋው አብዱላህ ኢብን ዙበይር ሁሉም ደጋፊዎቹ ጥለውት ሸሽተው ከአንድ ልጁና ከአምስት ወዳጆቹ ጋር ብቻ ቀረ።

በኋላም የመጨረሻውን ስንብት ሊደርግ ወደ እናቱ አስማ ቢንት አቡበክር ሲዲቅ (ረዐ) ዘንድ ሄደ። አስማ በጊዜው መቶ ዓመት ያለፋትና ዓይኗን የጋረዳት አሮጊት ብትሆንም ጥርሷ ያልተነቀለና አዕምሮዋም የሰላ ነበረ።

አብዱላህም ሰላምታ አቅርቦ ግንባሯን ከሳማት በኋላ «የገዛ ልጆቼ ሳይቀር ሁሉም ሰዎች ጥለውኝ ሸሽተው ካለረዳት ቀርቻለሁ። ሐጃጅ ደግሞ እጄን ከሰጠሁ ደህንነቴ እንደሚጠበቅ ይነግረኛል። እናም አሁን የመጣሁት ምክርሽን ለመስማት ነው።» አላት። አስማም «ሁኔታውን ከአንተ በላይ አላውቅም። በሃቅ ላይ ከሆንክ እንደ ወዳጆችህ ሸሂድ እስክትሆን ፅና። ይህንን ዓለም ካስበለጥክ ደግሞ ታላቅ ጥፋት ይመጣብሃል። ለበኑ ዑመያዎች እጅህን እንዳትሰጥ። ሰዎች በክህደታቸው ደካማ እንዲያደርጉህ አትፍቀድላቸው። ሞት የሚመጣው በቀኑ ብቻ ነው። እንደ ወንድ ተጋድለህ ሙት።» አለችው።

አብዱላህም «የምፈራው ከሞትኩ በኋላ ጀናዛዬን በፈረስ ጭነው መጫዎቻ እንዳያደርጉት ነው።» አላት። አስማም «ልጄ! በግ ከታረደች በኋላ እኮ ስለሚሆነው ነገር ጉዳዩዋ አይደለም።» አለችው። አብዱላህም የእናቱን ግንባር ሳመና «የእኔም ሃሳብ ይሄው ነው። በእርግጥ ከዚህ ዓለም ምንም ጥቅም ፈልጌ አላውቅም። እስካሁንም የደከምኩት የአላህን ቃል ለመሙላት ብዬ ነው። እስከመጨረሻዋ እስትንፋሴም እጋደላለሁ። የአላህን ቃል ተላልፌ መጥፎ ነገር ሰርቼ አላውቅም። ዛሬ በእርግጥ የምሞትበት ቀን ይመስለኛል። ወደ አላህም በመጠጋቴ ሀዘን እንዳይገባሽ።» አላት።

አስማም ልጇን አቅፋ ከሳመች በኋላ የለበሰውን ዳብሳ «ምንድነው ይሄ?» አለችው። እሱም «መከላከያ የሚሆን ጥሩር ነው» አላት። «አውልወቅና ሱሪ ልበስ። ስትወድቅ አፍረተገላህ እንዳይጋለጥ ይረዳሃል። የእኔ ልጅ! በጀግንነት ተጋደል። አንተ የአባትህ የዙበይር፣ የአያትህ የአቡበክር ሲዲቅ፣ የሴት አያትህ የሰፊያ ልጅ ነህ።» አለችው።

አብዱላህም ጥሩሩን ጥሎ ተራ ልብስ እንደለበሰ ሰይፉን ይዞ ወጣ። ለጓደኞቹም «የዙበይር ልጆች! ፈፅሞ እንዳትፈሩ። ስትቆስሉም ቅባት አታድርጉበት። ከጉዳቱ የበለጠ ያማችኋልና። ብዛታቸው እንዳስፈራችሁም አይናችሁን ዝቅ አድርጉ። ወደ እኔም ሳትመልከቱ ከተዋጋችሁ በእርግጥ በጠላቶች መሃል ታገኙኛላችሁ።» አላቸው።

በዚያን ቀንም አብዱላህ እንደ አንድ ሺህ ሰው ያህል ተዋጋ። በአንድ አቅጣጫ የመጡትን ሶርያውያንም ከጓደኞቹ ጋር እንዲያፈገፍጉ አደረጋቸው። በመሃልም ተመልሶ በኢብራሂም መቆሚያ ላይ ሁለት ረከዓ ሰገደ። ከዚያም ወደ ውጊያው ተመልሶ ገባ። ውጊያውም እስከ እኩለ ቀን ቀጠለ።

በመጨረሻም ሐጃጅ ቀስተኞችን በመያዝ ማጥቃት ያዘ። የአብዱላህ ጓደኞችም አንድ በአንድ ወደቁ። ከዚያም አንድ ቀስተኛ ከሶፋ ተራራ ላይ ሆኖ የአብዱላህን ጭንቅላት አገኘው። ጉዳቱም ከፍተኛ ስለነበረ ደሙ በአሸዋው ላይ ተዘራ። አብዱላህም ራሱን መቆጣጠር ተስኖት መንገዳገድ ሲጀምር ከየአቅጣጫው የተወረወሩ ቀስቶች አረፉበት። በዕለተ ማክሰኞ በጀማዱል አወል 73 ሒጅራም ታላቁ ሰሃባ አብዱላህ ኢብን ዙበይር ኢብን አል-አዋም በ73 ዓመቱ ሸሂድ ሆኖ ወደቀ።

እናቱ አስማም ከልጇ ሞት ጥቂት ቀናት በኋላ ይህንን ዓለም ተሰናብታ ተከትላው ሄደች።

(ኢብን አሲር- አል-ካሚል 4/352)

ሼር እናድርግ።የአጅሩ ተካፋይ ዕንሁን
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
615 views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 22:26:49 صلُّوا عليه وسلِّموا تسليمًا

يقول ابن الجوزي -رحمه الله- :

واعلموا أنه ما مِن عبد مسلم أكثر الصلاة على محمد عليه الصلاة والسلام، إلا نوَّر الله قلبه، وغفر ذنبه، وشرح صدره، ويسَّر أمره، فأكثروا من الصلاة؛ لعل الله يجعلكم من أهل مِلَّته، ويستعملكم بسُنته، ويجعله رفيقنا جميعًا في جنته، فهو المتفضل علينا برحمته .

بستان الواعظين (٢٩٧)
511 views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ