2022-08-23 10:48:18
#ሶላት_የማይሰግድ_ሰው_አንገት_እንደሌለው_ነው_የሚቆጠረው
ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.አ.ወ)
ሶላትን የመተው አደጋው
የአደምልጅ ሆይ
☞ስትወለድ ጆሮህ ላይ አዛን ይባልብሀል
☞ስትሞት ሶላት ይሰገድብሀል
☞በዱኒያ ላይ ሂወትህ ከአዛን እስከ ሶላት እንዳለው ጊዜ ነው ስለዚህ ሳይሰገድብህ ስገድ ጊዜህን በማይጠቅምና
❖ባልባሌ ቦታ አታሳልፍ
❖መቆያህን መስጅድ መረጋጊያህን ቁርአንን አድርግ።
አላህ ሱብሀነሁወተአላ ሶላትን ደንግጓል።
የኢስላምም ምሰሶና አስኳል አድርጎታል።
ነቢዩ ሙሀመድም( ) እንዲህ ብለዋል ፦ የነገሩ ሁሉ ራስ ኢስላም ነው።ሶላት ምሰሶው ነው። ለአላህ ተብሎ የሚደረግ ጂሃድ ደግሞ ጣራው ( ሻኛው) ነው።
ከኢባዳዎች ሁሉ በቅድሚያ ግዴታ የተደረገው ሶላት ነው።
ነቢዩ ወደ ሰማይ ባረጉበት ሌሊት ።አዎ በዚያች በተከበረችወወ ሌሊት ያለማንም አገናኝ ( መልእክት አስተላላፊ) አላህ ሱብሃነሁ ወተአላ ነቢዩን የሶላትን አስፈላጊነትና ግዳጅነት በቀጥታ አሳወቃቸው ። ለዚህ ነው ሶላትን ሆን ብሎ የተወ ሰው ወደ ክህደትና ጥመት ደረጃ ደርሷል ወይም ከሃዲ ነው የሚል ብይን የሚሰጠው ።
በርግጥ ከሶላት የራቀ ሰው
☞ከኢስላም ርቋል ፤
☞ጌታውን አስቆጥቷል ፤
☞ራሱንም ለጥፋት ዳርጓል ፤
☞መልካም ስራውንም አውድሟል ።
የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ፦ በአንድ ሰውና በክህደት መካከል ( መለያ የሚሆነው) ሶላት መተው ነው።
ኢማሙ አህመድ እና ሌሎችም ቡረይዳ( ረ ዐ) የተባሉትን ሰሃባ ( ረ ዐ) ጠቅሰው እንደዘገቡት ነቢዩ እንዲህ ብለዋል ፦ በኛና በነርሱ ( በከሃዲዎች) መካከል ያለው ልዩነት ሶላት ነው ። ሶላት የተወ ሰው በርግጥ ክዶአል ።
አብደላህ ኢብን ዑመር ( ረ ዐ) እንዳወሩት የአላህ መልእክተኛ ( ) ስለ ሶላት የሚከተለውን ብለዋል ፦ ሶላትን የጠበቀ ለርሱ ብርሃን ማስረጃና ነፃ መውጫ ይሆነዋል ።
ሶላትን ያልጠበቀ ለርሱ ብርሃን ፣
ማስረጃና ነፃ መውጫ አይኖረውም ። በእለተ ትንሳኤ ከቃሩን፣
ከፊርኦውን እና ከኡበይ ኢብኑ ኸለፍ ጋር ይሆናል ( ይጎዳኛል) ።
አላህ ተከሳሪወች አያድርገን ከጀሀነም ቅጣትም እሱው ይጠብቀን አንተ አዛኝ ነህና እዘንልን የአላህ
http://t.me//@arebgendamesjid
SHARE SHARE
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
በኢስላምእንኖራለን...በሰለፎችፋና
598 views07:48