Get Mystery Box with random crypto!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ne_siha_eslamik — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ne_siha_eslamik — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የሰርጥ አድራሻ: @ne_siha_eslamik
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.26K
የሰርጥ መግለጫ

بسم الله الرحمن الرحيم
📮እንኳን ወደዚህ ቻናል ተቀላቀሉ‼️
በዚህ ቻናል ቂርአቶችን፣ ሙሐድራዎችን፣ዳዐዋዎችን እና ሌሎችንም ከአረብገንዳ መስጊድ በአሚሩ አማካኝነት በቀጥታ የምታገኙበት ቻናል ነው።
ሃሳብ አስተያዬት ካለ በዚህ ያድርሱን ⤵️
@ye_Arebgenda_mesgid_wetatoch_bot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2022-09-04 16:45:45

100 views13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 23:44:02 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-19-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
19 views20:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 23:43:53 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                 ክፍል 12

    እስኪ በዚህ ወቅት አቡበክር(ረ.ዐ) ባይኖሩ ኖሮ ምን ሊከሰት እንደሚችል ልብ በሉ! ሶሃቦች ሊረጋጉ አይችሉም ነበር፡፡ ድንጋጤያቸው ምን ሊያደርጋቸው እንደሚችል አስቡ፡፡
ከዚህ በኋላ አጸደ-ሥጋቸው የት ማረፍ አለበት በሚለው ላይም ሶሃቦች አንዳንድ ልዩነቶችን ፈጠሩ። አስ-ሲዲቅ እንዲህ አሉ «ረሱል
(ሰዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ” እኛ ነቢያት የምንቀብረው እዚያው ሞትንበት ቦታ ነው፡፡ ከዚያም ሶሃቦች በነገሩ ተስማሙና የእሜቴ ዓኢሻ አልጋ የነበረበትና የሞቱበት ቦታ ግብዓተ መሬታቸው እንዲፈጸም አደረጉ፡፡

           ለኸሊፋው ቃል ኪዳን መግባት

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በሕልፈት አማካኝነት ወደ ዝንተ ዓለመ ኑሮ ከተሸጋገሩ በኋላ የርሳቸውን ቦታ ማን ይተካ?› በሚለው ጉዳይ ላይ ሶሃቦች በመጠኑም ቢሆን ለመወሰን መቸገራቸው አልቀረም፡፡ የመዲና ቀደምት ነዋሪ የሆኑት አንሷሮች ይህን ለመወሰን በሰቂፋበኒ ሳዒዳ አዳራሽ ውስጥ ጉባኤ ተቀምጠዋል፡፡ ሃሳባቸው ከነርሱ ውስጥ አንዱ የሆነውንና በመካከላቸው ተሰሚነቱ የጎላውን ሰዒድ ቢን ዑባዳን ለመምረጥ ነበር፡፡ ሆኖም ሰዒድ በወቅቱ ታሞ ስለነበር በቦታው አልተገኘም፡፡

  ሰይድ ዑመር ቢን አል ኸጣብ(ረ.ዐ) አንሷሮች በሰቂፍ ጉባኤ መቀመጣቸውን ሲሰሙ አቡበክር አስ-ሲዲቅንና አቡ ኡበይዳህ ቢን አልጀራህን ይዘዋቸው ወደ ሰቂፋ አቀኑ፡፡ እንደ ደረሱም ከአንሷሮች ጋር ውይይት ማድረግ ጀመሩ፡፡

  አንሷሮች እንዲህ አሉ ‹‹በዚህ ጉዳይ ላይ (ኸሊፋ በመሆን ጉዳይ ላይ መብቱ ያለን እኛ ነን፡፡ ምክንያቱም ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) የረዳነውም ያስጠጋነውም እኛ ነን፡፡ እኛ ዘንድ ሰዕድ ቢን ዑባዳ ስላለ እርሱን መሾም እንችላለን፡፡»

  ሰይድ ዑመር(ረ.ዐ) ሁኔታውን ሲያስታውሱ እንዲህ ይላሉ «በወቅቱ ሰፋ ያለ ንግግር ለማድረግ ተዘጋጅቼ ነበር፡፡ አቡበክር(ረ.ዐ) እንዳልናገር እጄን ያዝ አድርገው ከለከሉኝ፡፡ ከዚያም እንዲህ አልኩኝ "በእርግጥ በመጀመሪያ የረዳችሁና ያሥጠጋችሁት እናንተ ናችሁ፡፡ አሁን ተገቢውን ገር ለመቀየር የመጀመሪያዎቹ አትሁኑ፡፡ እናንተ አንሷሮች ዐረቦች ይህ ጉዳይ ለቁረይሾች ካልሆነ በቀር ለማንም እንደማይገባ ያምናሉ፡፡»

  አንሷሮች ««እኛም ዘንድ መሪ አለ። እናንተም ዘንድ መሪ አለ፡፡ አሉ «አቡበክርም ቀበል አደረጉና ‹‹እንዲህማ ተገቢ አይደለም» አሉ። በሺር ቢን ሰዕድ የተባለ የኸዝረጅ ጎሳ አባልና አንሷሪ ተነሳና እንዲህ ሲል አቡበክርን(ረ.ዐ) ደግፎ ተናገረ "እናንተ አንሷሮች! ወላሂ ለዚህ ጉዳይ ከእኛ የበለጠ መብት ያላቸው እነርሱ ናችው። እኔ አመራርን ለመቀበል ቃል እገባለሁ!» ሰይድ ዑመርም(ረ.ዐ) ለአቡበክር “እጅዎን ይዘርጉ!›› አሉና «ቃል እገባሎታለሁ» ብለው ጨበጧቸው። ዑመርን ተከትለው ሁሉም ሶሃቦች በየተራ እየሆኑ ለአቡበክር የኸሊፋነትን ቃልኪዳን (ሙባየን) ገቡላቸው፡፡

  ይህን የመሰለው ከበድ ያለ ጉዳይ እንዲህ በእርጋታ ተከናወነ።
ሶሃቦች ልባቸው ከአላህ (ሱ.ወ) ጋር የተቆራኘና ጥልቅ የሆነ መጣጣም ስለነበራቸው ነገሩ በዚሁ ቋጩት፡፡

            የኸሊፋው ፖሊሲዎች

   የኸሊፋነቱን ቦታ አቡበክር አስ-ሲዲቅ ተረከቡ፡፡ ኸሊፋነቱን ገና እንደተረከቡ አቋምና ፖሊሲዎቻቸውን እንደሚከተለው ለሚመሩት
ሕዝብ ይፋ አደረጉ፡፡
   "እኔ በእናንተ ላይ የተሾምኩት ከእናንተ በልጬ አይደለም፡፡ እውነት ላይ ሆኜ ካገኛችሁኝ አግዙኝ፡፡ ወደ ሀሰት ስዘነበል ካያችሁ ደግሞ መልሱኝ፡፡ አስተካክሉኝ አላህን እስከታዘዝኩ ብቻ ታዘዙኝ፡፡
አላህን ካመጽኩ ግን መታዘዝ የለባችሁም፡፡ ከእናንተ መካከል ደካማው ድርሻውን እስከሰጠ ድረስ በኔ ዘንድ ኃያል ነው። ኃያሉም የሌሎችን ድርሻ እስኪሰጥ ድረስ በኔ ዘንድ ደካማ ነው፡፡ እናንተ ሰዎች በአላህ መንገድ ላይ መታገል ለሚያቆሙ ሕዝቦች አላህ የሀፍረት ካባ ያከናንባቸዋል፡፡››

   አቡበክር አስ-ሲዲቅ በዚህ መልኩ በአመራር ወቅት የሚከተሏቸውን ፖሊሲዎች በግልጽ ይፋ አደረጉ። ገለጻቸው አምስት መሠረታ ነጥቦችን አካቶ ይዟል።
1. መተናነስ (ተዋዱዕ)
2. በእውነት ላይ መተጋገዝ ያለው ተገቢነት፣
3. ስህተትን ማስተካከልና መቃወም ያለው አስፈላጊነት፣
4. ደካማም ቢሆን ተበዳይ እስከሆነ ድረስ መረዳትና የፈለገ
ኃይለኛ ቢሆን በዳይን መከልከል ወሳኝ መሆኑ፣
5. በአላህ መንገድ መታገል(ጂሐድ) የኡማው ክብርና ማእረግ መሆኑናቸው።

   አቡበክር አስ-ሲዲቅም በኸሊፋነት በመመረጣቸው ያልወደደ አልነበረም፡፡ ልጅ አዋቂው ሳይቀር ተደሰተ። የአቡበክርን ደግነት ሁሉም ያውቅ ስለ ነበር ሁሉም ተቀበለ። አቡበክር ከአዘኔታቸው የተነሳ አንዳንዴ በመንገድ ሲያልፉ ሕጻናቶች እየመጡ ይጠመጠሙባቸው ነበር፡፡ «አባቴ! እባቴ! ይሏቸዋል። እርሳቸውም ኸሊፋነታቸው ሣያስኮፍሳቸው ሕፃናቶቹን ያቅፏቸውና ይሽከሟቸው ነበር።

   ከአቡበክር የተባረኩ የትሁትነት ልምዶች አንዱ ! ባሎቻቸው ሰማዕት ሆነው የተለዪዋቸው ሴቶችን ላሞች በማለብ በሥራ ማገዝ ነበር። አንዴ ባላቸውን በዚህ ሁኔታ ያጡ ሴቶች አቡበክር ኸሊፋ ከሆኑ በኋላ «አሁንሥ ማን ወተት ያልብልናል» ማለታቸውን አቡበክር ይስሙና ወደ ሴቶቹ ሄደው እንዲህ ይሏቸዋል «ያላችሁትን ሁሉ ሰምቻለሁ ወላሂ አቡበክር እስኪሞት ድረስ የላሞቻችሁን ወተት ከማለብ አይወገድም፡፡››

   አንድ ጊዜ ሁለት ሰዎች መሬት ይሰጡዋቸው ዘንድ ለመጠየቅ ወደ አቡበክር(ረ.ዐ) ይመጣሉ፡፡ አቡበክርም እነዚህ ሰዎች ቀልባቸው ወደ እስልምና እንዲያዘነብል በማሰብ መሬት ሊሰጡዋቸው ተስማሙ። ሆኖም ግን በጉዳዩ ላይ ሰይድ ዑመር(ረ.ዐ) መስማማት እንደሚኖርባቸው ነግረዋቸው ወደ እርሳቸው ዘንድ እንዲሄዱ ያደርጋሉ፡፡

  ዑመር(ረ.ዐ) በጉዳዩ ሳይስማሙ ይቀራሉ። እስልምናን ለማጠናከር በሚል ስዎችን በጥቅማጥቅም ማባበሉ ተገቢ እንዳልሆነና እስልምና በራሱና ብቻውን ጠንካራ መሆኑን በመግለጽ አቋም ይይዛሉ፡፡ ሁለቱ ሰዎችም በሁኔታው ተበሳጭተው ወደ ኸሊፋው ይመለሳሉ፡፡ ‹‹ ለመሆኑ ኸሊፋ እርሶ ኖት ወይስ እርሳቸው?›› በማለት አቡበክርን ይጠይቃሉ። አስ-ሲዲቅም ‹‹ኢንሻአላህ እርሱ ነው» ብለው ይመልሱላቸዋል።

         ታሪክ ያልደገመው ሰው

  አቡበክር አስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) ለኸሊፋነት በበቁ ማግስት በርካታ ጎሳዎች በእስልምና ሳይ ክህደት ፈጽመው ነበር፡፡ ከመካ እና ከመዲና ወጪ የሚኖሩ ጎሳዎች እስልምናን ክደዋል፡፡

  ሰይድ አቡበክር(ረ.ዐ) በሁለት ዓመታት የኸሊፋነት ጊዜያቸው በእስልምና ላይ ያንዣበበውን ይሀን አደጋ ገፈው ለመጣል ችለዋል:: በዓረበ ፔንሱሳ (ጀዚረተል ዐረብ) የተፈፀመውን ክህደት በሙሉ አስቀርተው ጎሳዎቹ በመሉ ወደ እስልምናቸው እንዲመለሱ አድርገዋል፡፡ በዚህ የሁለት ዓመት ዕድሜ ውስጥም የፋርስና የሮም ሀገራትን ማቅናት፣ ቁርኣን በጥራዝ መልክ እንዲሰባስብ ማድረግ ችለዋል፡፡
http://t.me//@arebgendamesjid
   ➛➛➛➛ይቀጥላል
ኢንሻ አላህ➛➛➛

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
18 views20:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 20:15:40 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-18-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
264 views17:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 20:15:34 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                     ክፍል 11

«እናንተ ሰዎች ሆይ! የእኔና የእናንተ የቀጠሮ ቦታ ዱኒያ
አይደለችም፡፡ ቀጠሮዋችን ሐውድ ዘንድ ነው፡፡ ከዚሁ ሆኜ እያየሁት
ይመስለኛል፡፡ ሰዎች ሆይ! የሶላት ነገርን አደራ! በሴቶቻችሁ ላይ አላህን ፍሩ፡፡ እናንተ ሰዎች ሆይ! ድህነት ያገኛችኋል ብዬ አልፈራም፡፡ ይልቁንም በኃብት ትጥለቀለቁና ስትፎካከሩ ያለፉት ሕዝቦች እንደጠፉት ሁሉ እናንተም ሃብት ያጠፋችኋላ ብዬ እፈራላችኋለሁ።

  እናንተ ሰዎች ሆይ! አላህ ባሪያውን ከዚህ ዓለምና እርሱ ጋር
ከመገናኘት አማረጠው፡፡ ባሪያውም ከአላህ ጋር መገናኘትን መረጠ፡፡» ሶሃቦች ንግግራቸውን ጸጥ ረጭ ብለው ያዳምጡ ነበር፡፡ ጭንቅላታቸው ላይ ወፍ ቢያርፍ እንኳ ግዑዝ እስኪመስለው ድረስ በድን ሆነው ነበር፡፡

   አስ-ሲዲቅ(ረዐ) ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) መጨረሻ የተናገሩት ምን ማለትእንደሆነ ገባቸውና ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ይንሰቀሰቁ ጀመር፡፡ «አባቴም እናቴም ልጆቼም ገንዘቤም መስዋዕት ይሁንሎ!›› እያሉ ማልቀሱን ተያያዙት፡፡ ሶሃቦች ነገሩ አልገባቸው ኖሮ ወደ አስ-ሲዲቅ ዘወር ብለው የረሱልን (ስ.ዐ.ወ) ንግግር በማቋረጣቸው ይወቅሷቸው ጀመር፡፡

  ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ ‹‹አቡበክርን ዝም በሉት! አትንኩት! ወላሂ! ከአቡበክር በስተቀር ከእናንተ ውስጥ እኛ ዘንድ ውለታ ኖሮበት ያልመለስንለት የለም፡፡ የአቡበክርን ውለታ ግን የመመለስ አቅሙ የለኝም፡፡ ውለታውን አላህ እንዲመልስለት ትቼዋለሁ፡፡››

  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከአቡበክር(ረ.ዐ) ቤት በስተቀር የሁሉም ሶሃቦች ቤት እንዲዘጋ አዘዙና ለሶሃቦች ዱዓ ያደርጉላቸው ጀመር። «አላህ
ያሥጠጋችሁ አላህ ድልን ያጎናጽፋችሁ፡፡ አላህ ያግዛችሁ። አላህ
ይጠብቃችሁ፡፡ አላህ ከፍ ያድርጋችሁ እናንተ ሰዎች ሆይ እስከ እለተ ትንሳኤ ድረስ እኔን ለተከተሉ ሁሉ ሠላምታዬን አድርሱ!››
ወዓለይኩምሰላም ያረሱሉላህ!

  ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ተሸክመው ወደ ቤታቸው እስኪያደርሷቸው ድረስ (በል አረፊቂል ኣዕላ በል አረፊቂል ኣዕላ!» ይሉ ነበር፡፡ እሜቴ ዓኢሻ ከዱኒያ ይልቅ የዝንተ ዓለሙን ሕይወት እየመረጡ እንደሆነ ተረዳች፡፡ ከዚያም ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) “አቡበክርን እንዲያሰግድ ንገሩት” ብለው ሲያዙ እሜቴ ዓኢሻ እንዲህ አለች “አንቱ የአላህ መልዕክተኛ አቡበክር(ረ.ዐ) እኮለስላሳ ሰው ናቸው። ቁርዓንን ከቀሩ በጣም ተንሰቅስቀው ያለቅሳሉ” ብለው ሌላ ሰው እንዲቀይሩ ጎተጎተቻቸው፡፡

  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ግን ደገሙና «አቡበክር እንዲያስግድ ንገሩት››
አሉ፡፡ እሜት ዓኢሻም ዑመር ቢን አል-ኸጣብ(ረ.ዐ) እንዲቀየሩ አዘዘች፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ይህን አወቁና እንዲህ አሉ ‹‹አቡበክር ያሰግድ አላልኩም ነበር? አላህም ሆነ መስሊሞች ሌላ ሰው እንዲያሰግድ አይፈቅዱም፡፡ አቡበክር እንዲያሰግድ እዘዙት!››

   ከዚያም በታዘዙት መሠረት አቡበክር(ረ.ዐ) ሰዎችን ያሰግዱ ጀመር፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይህንኑ ተመለከቱና የመጨረሻ ፈገግታቸውን ፈገግ አሉ፡፡ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የመጨረሻ ፈገግታ ብልጭ ያለችው ሶላት በፈጠረው ደስታ ነበር፡፡ እስኪ አንተ ፈጅር የማትሰግድ ሰው! ይህን በደንብ አስተውል።

  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) አቡበክር ሙስሊሞችን ኢማም ሆነው ሲያሰግዱ
ከተመለከቱ በኋላ እጅግ እርካታ ተሰማቸውና ወደ ቤታቸው "በል
አረፊቂል አዕላ" እያሉ ተመለሱ። ከዚያም በእሜቴ ዓኢሻ ደረት ላይ
ጋደም ብለው ተኙ፡፡ እሜቴ ዓኢሻ ይህንን ሁኔታ ስትገልጽ ‹‹ይህንኑ
ቃል ይደጋግሙ ነበር፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ እጃቸው ሸርተት ብሎ
ወደቀ፡፡ ደረቴ ላይ እንዳሉ ይከብዱኝ ጀመር፡፡ ማለፋቸውን ወዲያው
አወቅሁ።

                ጠንካራ አቋም
 
    እሜቴ ዓኢሻ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ማለፋቸውን እንዳወቀች የምታደርገው ሁሉ ጠፍቷት ነበር፡፡ የምትሆነው ጠፋት፡፡ ሶሃቦቹ
ወዳሉበት መስጂድ እየተጣደፈች ሄዳ «የአላህ መልዕክተኛ ሞተዋል... የአላህ መልዕክተኛ ሞተዋል" እያለች ጮኸች...
መስጂዱ በቅፅበት በጩኸት ተናጋ፡፡ ዓሊይ ኢብን አቡጣሊብ
መቆም አቃታቸው፡፡ ዑስማን ቢን ዓፋን የሚያደርጉትን ኣጡ፡፡ እንደ
ህፃን ሁለቱንም እጃቸውን ተይዘው ወዲህ ወዲያ ይላሉ፡፡ የነብዩ
(ስ.ዐ.ወ) ልጅ ፋጢማ «ወይኔ አባቴ! የጌታውን ጥሪ ተቀበለ፡፡ ወይኔ አባቴ ፊርደውሰል ጀነት መጠጊያው፡፡ ወይኔ አባቴ! የጅብሪል ጓደኛ" እያለች እሪታዋን አቀለጠችው፡፡

ጀግናው ዑመር ቢን አልኸጣብ እንደ ነበልባል የሚወናጨፈውን
ሰይፋቸውን ምዝዝ አድርገው ሲያወጡት ሁሉም ሰው ረጭ አለ፡፡ "ዝም በሉ! አንድም ሰው ከአሁን በኋላ መሐመድ ሞቱ ቢለኝ ጭንቅላቱን በዚህ ሰይፍ አሽቀንጥሬ እጥለዋለሁ። ሙሳ እንዳደረጉት ሁሉ ጌታቸው ሊያናግሩ ነው የሄዱት። አንድ ሰው ሞቱ ቢለኝ ጭንቅላቱ ይቀነጠስላታል።" አሉ፡፡

   ሶሃቦች ሁሉ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የነበራቸው ፍቅር በጣም ከፍተኛ
ነበር፡፡ የአቡበክር ግን ልክ አልነበረውም፡፡ እየገሰገሱ መጡ፡፡ ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ቤት ገቡና የነገሩን ትክክለኛነት ካረጋገጡ በኋላ ጠጋ ብለው በዓይኖቻቸው መካከል ያለውን ቦታ ሳም አደረጓቸውና እንዲህ አሉ «እርሶ ሞተውም ህያውም ሆነው ውብ ነዎት፡፡ ከዚያም እንዲህ ሲሉ ደጋገሙ «ዋ ወዳጄ! ዋ ውዴ! ዋ አፍቃሪዬ! ዋ ነብዬ!››

  ከዚያም ወደ መስጂድ ወጡና እንዲህ አሉ ‹‹ ዑመር ዝም በል! ,
ግራ የገባቸው ዑመር ዝም ሊሉ አልቻሉም፡፡ አቡበክር ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እንዲህ አሉ “እናንተ ሰዎች ሆይ መሐመድን ያመልክ የነበረ ሰው ካለ ሙሐመድ ሞቷል፡፡ አላህን ያመልክ የነበረ ሰው ካለ ግን አላህ ምን ግዜም ሕያው ነው። አይሞትም›› ከዚያም የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ አነበቡ፡፡

وَمَا مُحَمَّدٌ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ ۚ أَفَإِن مَّاتَ أَوْ قُتِلَ انقَلَبْتُمْ عَلَىٰ أَعْقَابِكُمْ ۚ وَمَن يَنقَلِبْ عَلَىٰ عَقِبَيْهِ فَلَن يَضُرَّ اللَّهَ شَيْئًا ۗ وَسَيَجْزِي اللَّهُ الشَّاكِرِينَ

"ሙሐመድም ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ ታዲያ ቢሞት ወይም ቢገደል ወደ ኋላችሁ ትገለበጣላችሁን ወደኋላው የሚገለበጥም ሰው አላህን ምንም አይጎዳም፡፡ አላህም አመስጋኞቹን በእርግጥ ይመነዳል፡፡"     (አል-ኢምራን 144)

  ሰይድ ዑመር ሁኔታውን ሲያስታውሱ እንዲህ ይላሉ ‹‹የቁርኣን
አንቀፁን ስሰማ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት ያህል ሆነብኝ፡፡ ሰይፌ ከእጄ ላይ ወደቀ፡፡ ምን እያደረግሁ ነው ብዬ ራሴን ታዘብኩ፡፡ ከዚያም ለብቻዬ ገለል ብዬ ማልቀስ ጀመርኩኝ፡፡››...
http://t.me//@arebgendamesjid
----------◌◌ይቀጥላል◌◌---------ኢንሻ አላህ

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
218 views17:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 10:41:43 #የጁምአ_ቀን

ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ .ወሰለም )እንዲህ ብለዋል ፡-
አርብ(ጁመዓ) ቀን፡ ገላውን ታጥቦ መላ ሰውነቱን አፀዳድቶ ፡ቅባትና ሽቶ ከተቀባ በሗላ ጁመአ ለመስገድ ቀደም ብሎ ወደ መስጊድ ፡በመሔድ ሌሎች ሰዎችን ሳይገፋና ሳይረብሺ በፀጥታ ቦታውን ለሚይዝ ፡ከዚያም የቻለውን ያህል (ነፍል) ከሰገደ በሗላ በፀጥታ ኹጥባን(የኢማሙን ንግግር )ለሚያዳምጥ ሰው ከዚያ ጁመዓ ጀምሮ እስከሚቀጥለው ጁመአ ድረስ በመካከል ያለው ሐጢያቱን አላህ ይተውለታል፡፡ ነብዩ{ሰ,ዐ,ወ} ስለ ጁምአ ቀን ታላቅነት ሲናገሩ የጁምአ ቀን የቀኖች ሁሉ ኑጉስ ነው እነዚህ አምስት ነገሮች በጁምአ ቀን ተከስተዋል ብለዋል። እነሱም
1, አላህ አደምን የፈጠረው በጁመአ ቀን ነው፣
2, አደም ከጀነት የወጡት በጁምአ ቀን ነው፣
3, አደም የሞተውም በጁመአ ቀን ነው፣
4, ቂያማ የምትቆመውም በጁመአ ቀን ነው፣
5, በጁምአ ቀን የሆነች ሠአት አለች።አንድ የአላህ ባሪያ የጠየቀውን ነገር ይሠጠዋል፣ያቺን ሠአት ካገኛት ሀራም ነገር እስካልሆነ ድረስ አላህ ይቀበለዋል። በሌላ የሀድስ ዘገባ አንድ ሰው ታጥቦ ያለውን ጥሩ ልብስ ለብሶ ሽቶ ተቀብቶ ወደ መስጂድ ሄዶ ማንንም አዛ ሳያደርግ ኢማሙ ቁጥባ ሲያደርጉ ዝም ብሎ ከሠማ ጁማአውን ከሰገደ አላህ ካለፈው ጁምአ እሥከ አሁኑ ጁምአ ያለውን ወንጀሉን ያብስለታል። በሌላ የሀድስ ዘገባ የጁምአ እለት በመጀመሪያ ሠአት ወደ መስጅድ የገባ ግመል ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ የቀንድ ከብት ሠደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ በግ/ፍየል ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ ዶሮ ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ እንቁላል ሠደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታላ። ኢማሙ ሚንበር ላይ ሲወጡ የሚመዘግቡት መላኢኮች የኢማሙን ኹጥባ ለመስማት መስጂድ ይገባሉ።

የአላህ መላእክተኛ(ሰ,ዐ,ወ) እንድህ ብለዋል፦

የጁምአ ቀን በእኔ ላይ ሠላወትን ማውረድ አብዙ፣ማንኛውም ሠው የጁምአ ቀን በእኔ ላይ ሠላዋት አያወርድም ሠላዋቱ ቢቀርብልኝ እንጅ።

{አልባኒ ሶሂህ ብለውታል} ‌"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በዐርብ ቀን ለስግደት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ። መሸጥንም ተዉ፡፡ ይህ የምታውቁ ብትኾኑ ለእናንተ በጣም የተሻለ ነወ።" ‌ "ሶለቲቱም በተፈጸመች ጊዜ በምድር ላይ ተበተኑ። ከአላህም ችሮታ ፈልጉ፡፡ አላህንም በብዙ አውሱ፡፡ ልትድኑ ይከጀላልና፡፡" ((62:910)

[የጁመአ ቀን ሱናወች] ~‌
~ገላን መታጠብ
~ ጥሩ ልብስ መልበስ
~ሽቶ መቀባት ለወንዶች
~ ሲዋክ
~ ማልዶ በግዜ ወደ መስጅድ መሄድ
~ ሱረቱል ካፍን መቅራት ዱአ ማብዛት ~ በረሱል (ሰ፣ዐ፣ወ) ላይ ሰለዋት ማውረድ።

  اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيد
      
الَّلهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّد ٍﷺ 
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
101 views07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:55:39   ሰይድ አቡበክር ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሄዱና እንዲህ አሏቸው
«ዑመርን ይቅርታ አድርግልኝ፣ ታረቀኝ ብለው እንቢ አለኝ ከዚያም
ዑመር ትንሽ ቆይተው ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መስጂድ ሲገቡ አቡበክር አጠገባቸው እንደተቀመጡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በጣም ተቆጥተው ፊታቸው ቀልቶ አዩዋቸው።

   አቡበክርም ይህንኑ የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሁኔታ ሲመለከቱ
ያበርዷቸውና ያረጋጓቸው ጀመር፡፡ «ረሱል ሆይ! እባክዎን ይረጋጉ እኔ ነኝ ጥፋተኛ አሉ። ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ “ምን ሆነህ ነው ዑመር እንዴት ለአቡበክር ፊት ትነሳዋለህ?..»

   "ሰዎች ሆይ! ይህን ዲን ዤ ስመጣ ሰው ሁሉ ፊት ሲነሳኝ
የተቀበለኝ አቡበክር ነው፡፡ እውነተኛ ነህ ያለኝ አቡበክር ነው፡፡ ገንዘቡን፣ ነፍሱንና ቤተሰቡን አሳልፎ የሰጠኝ አቡበክር ነው፡፡ እባካችሁ ጓደኛዬን እንዳትነኩት፡፡" ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አቡበክርን(ረ.ዐ) ቀና ብሎ ያያቸው ኣልነበረም፡፡

           የመዋደድ ውበት

  በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)ና በአቡበክር(ረ.ዐ) መካከል የነበረው መዋደድ መለኪያ አልነበረውም። አንድ ቀን በነብዩና (ሰ.ዐ.ወ) በእሜቴ ዓኢሻ መካከል የፍቅር ጭቅጭቅ ይጀመራል፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ «በመካከላችን ማን እንዲፈርድ ትፈልጊያለሽ፡፡ አቡ ኡበይዳ ይፍረድ?›› ዓኢሻም “አቡኡበይዳ መልካም ሰው ቢሆንም ከመጣ እርሶን ነው የሚደግፈው” ይላሉ ‹‹እሺ አባትሽ ይሁን?› እሜቴ ዓኢሻ ይስማማሉ፡፡

  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) አስ-ሲዲቅን አስጠሯቸው። አቡበክር እንደመጡ እሜቴ እንዲህ ይላሉ «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እውነቱን ብቻ
ይንገሩት›› አቡበክርም ተቆጥተው ‹‹እርሳቸው ያለእውነት መች ይናገራሉ” ብለው ዓኢሻን ሊመቷት ተጠጉ፡፡ ረሱልም (ስ.ዐ.ወ)
በመሃላቸው ይገቡና ‹‹አቡበክር ይህን እንድታደርግ አላስጠራንህም፡፡ በቃ ተወው›› ይሏቸዋል፡፡

  አቡበክር ከወጡ በኋላ ለእሜት ዓኢሻ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ
ይሏቸዋል «በእርሱና በአንቺ መካከል እንዴት ገላጋይ እንደሆነኩ አየሽ አይደል» አቡበክር(ረ.ዐ) ቆየት ብለው ተመልሰው ሲገቡ ሁለቱም ሲሳሳቁ አገኙዋቸውና ‹‹ስትፋለሙ እንደጠራችሁኝ በተስማማችሁ ጊዜም አሳትፉኝ» በማለት ቀለዷቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «አቡበክር ና ተሳተፍ› አሏቸው፡፡

  ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) መውደድ ከአላህ (ሱ.ወ) የሚገኝ በረከትና ጸጋ
ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ባሪያውን ሲወድ ይህን በረከትና ጸጋ ያጎናጽፈዋል፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ወደድክ ማለት የአላህን (ሱ.ወ) ሪዝቅና ችሮታ አገኘህ ማለት ነው፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ወዳጆች ከሆኑ ሙስሊሞች ጎን መሰለፍም ይጠበቅብናል፡፡

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በሌሊት ጉዞ ባደረጉበትና ወደሰማይ በመጠቁበት ወቅት የአፍታ ማረፊያ የነበራቸው ቁዱስን ከጥቃት ካልተከላከልን
እንዴት ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) እንወዳለን እንላለን፡፡ ታላቁ አቡበክር ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከእንቅልፋቸው እንዳይነቁ ብለው እባብን የሚያክል ነገር
ሲነድፋቸው ድምጻቸውን ዋጥ ማድረጋቸዉን አይተናል፡፡ እኛ ግን የተቀደሰ የመሰሊም ግዛቶች በጠላት እጅ ሲቆሽሹ ዐይተን እንዳላየ
መስለን እናንቀላፋልን፡፡

  አንድ ቀን አቡበክር(ረ.ዐ) ለረቢዓ ቢን ካዕብ ትንሽ የሚያስከፋ ንግግር ይናገሩትና በመካከላቸው አለመግባባት ይፈጠራል፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) በሁኔታው ያዝኑና «ረቢዓ ግድ የለም የተናገርኩህን መልሰህ ተናገረኝ” ይሉታል፡፡ ‹‹ረቢዓም መልስማ አልሰጦትም» ይላል፡፡ አቡበክርም «ረቢዓ በዚህ ንግግሬ አላህ ፊት እንድከሰስ ትፈልጋለህ?›› ይሉታል፡፡ ሳይናገር ዝም ይላቸዋል፡፡ አቡበክርም ቆጣ ብለው «ከዚህ ቃሌ ጋር አላህ ፊት እንድቀርብ ትወዳለህ ማለት ነው ወላሂ ለረሱል ሄጄ እነግራቸዋለሁ» ይላሉ፡፡

  የረቢዓ(ረ.ዐ) ወገኖችም ተገርመው «ራሱ የሚያስከፋ ንግግር ተናግሮህ ሲያበቃ እንደገና ለረሱል(ሰ.ዐ.ወ) እናገራለሁ ይላል እንዴ?›› ይላሉ። ሪቢዓም «ለመሆኑ የሰውየውን ማንነት አውቃችኋል? ዝም በሉ አስ-ሲዲቅ እኮ ነው! አሁን ለኔ ወግናችሁ እንዲህ ስትናገሩ እንዳይሰማንና እንዳይቆጣን ደግሞ! ከተቆጣ ለረሱል ሄዶ ይናገራላ ረሱልም እርሱን በማስቆጣታችን ይቆጡናል እርሳቸው ከተቆጡ ደግሞ ለእርሳቸው እና ለአቡበክር ቁጣ ሲል አላህም ስለሚቆጣ ረቢዓን ታስጠፋላችሁ፡፡ አሁን ዝም በሉ፡፡››ይላቸዋል ረቢዓ(ረ.ዐ) በስጋት ከአስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) ኋላ እየተከተለ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ሲደርሱ ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ፈገግ ብለው "አል ሲዲቅና አንተ ምን ሆናችሁ?" ይላሉ አንድ የሚያስከፋኝን ቃል ተናገሩኝና እርሱን መልሰህ ተናገረኝ ሲሉኝ እኔ ደግሞ አይሆንም አልኳቸው›› አለ ረቢዓ፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «ረቢዓ አዎን ልክ ነህ፡፡ ከአቡበክር ጋር መመላለስ የለብህም ይልቁንም አቡበክር ሆይ! አላህ ይማርህ» ብለው» አሉት፡፡

              በስንብቱ ዋዜማ

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ስልሣ ሶስተኛ ዓመታቸው ላይ ደርሰዋል፡፡
ሠውነታቸው ላይ የድካም ሁኔታ ይተይባቸው ጀምሯል። አንዲት ሴት ወደ ርሳቸው ዘንድ መጥታ የሆነ ነገር እንዲሰጥዋት ጠይቃቸዋለች፡፡ ከዓመት በኋላ እንድትጠይቃቸው ይነግሯታል፡፡ እርሷም «እኔ ስመለስ ባላገኞትስ?›› ትላለች፡፡ ከመድከማቸው የተነሳ እስከ ቀጣዩ ዓመት ሊቆዩ እንደማይችሉ ገምታለች። «እኔን ካላገኘሽኝ አቡበክር ጋር ሄደሽ ትጠይቂዋለሽ ይሏታል። ይህ የመልዕክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) አባባል ከርሳቸው በኋላ አቡበክር እንደሚተካቸው (ሊተኳቸው እንደሚገባ) አመላካች ነው፡፡

  ከዚህ ክስተት በኋላ ነበር ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የመሰናበቻውን ሐጅ
ያደረጉትና ተከታዩ የቁርዓን አንቀጽ የወረደው

الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا ۚ

"ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ፡፡"  (ሱረቱል ማኢዳህ- 3)

  ይህ አንቀጽ ሲወርድ ሶሃቦች ሁሉ በደስታ ሲስቁ አስ-ሲዲቅ ብቻ በአንቀጹ ስለ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መሰናበት የሚጠቁም ነገር እንዳለ ስለገባቸው ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡

  በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ላይ ሕመም ይጠናባቸው ጀመር፡፡ ዓኢሻ ቤት ሆነው ታስታምማቸው ዘንድ እንዲፈቅዱላቸው ሚስቶቻቸውን ሁሉ
አስፈቀዱ፡፡ ፈቀዱላቸው፡፡ የመጨረሻዎቹ ሰዓታት ሲደርሱ ሶሃቦች ሁሉ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መስጂድ ተሰባስበው ከፍ ባለ ድምፅ ያዝመትሙ ጀመር። ረሱል (ስ.ዐ.ወ) ድምጻቸውን ሰምተው ምን እንደሆኑ ሲጠይቁ በርሳቸውስጋት ገብቷቸው እንደሆነ ተነገራቸው!! ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) "ያሉበት ተሽክማችሁ ውሰዱኝ» አሉ፡፡

  እንደደረሱም ሶሃቦችን እንዲህ አሏቸው «እናንተ ሰዎች ሆይ! የኔ ሁኔታ አስፈርቷችኋልን?» ሶሃቦችም "አዎን አንቱ የአላህ መል
ዕክተኛ» በማለት መለሱላቸው እርሳቸውም እንሚከተለው አሏቸው... «እናንተ ሰዎች ሆይ! የእኔና የእናንተ የቀጠሮ ቦታ ዱኒያ
አይደለችም፡፡ ቀጠሮዋችን ሐውድ ዘንድ ነው፡፡ ከዚሁ ሆኜ እያየሁት ይመስለኛል...

----------ኢንሻአላህ ይቀጥላል-----
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ

http://t.me//@arebgendamesjid
185 views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:55:34 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-17-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
202 views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:50:31 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-16-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
134 views18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:50:23 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                     ክፍል ዘጠኝ
 
  «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኛ በቀጥታ የመጣነው ፈጅር ለመስገድ ነው በዚህ ሰዓት እንዴት የታመመን ልንጠይቅ እንችላለን፡፡» በማለት ዕይድ ዑመር መለሱ፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኔ ወደ መስጅድ ለመሄድ ከቤቴ ስወጣ ትላንት ወንድሜ አብዱራህማን ቢን ዐውፍ መታመሙን አስታወስኩ፡፡ የርሱ ቤትና የእኔ ቤት በመስጅዱ መካክል ይገኝ ነበር፡፡ ለሪጅር ሶላት መንቃቱን ስላወቅኩ  አንድ አፍታ ገብቼ ጠየቅሁትና ወደዚህ ለሶላት መጣሁ» አሏቸው፡፡

    ረሱል (ሰዐ,ወ) ቀጠል አደረጉና «ዛሬ ምሽት ከናንተ ውስጥ ሶደቃ የሰጠው ማነው?» ብለው ጠየቁ፡፡ ዑመርም “በዚህ ምሽት ሶደቃ የሰጠነው ማንም ደሃ የለም” ብለው መለሱ፡፡ «አንቱ፡ የአላህ መልዕክተኛ ቢን ዓውፍን ከጠየቅሁ በኋላ ወደ መስጂድ ስገባ ድሃ አገኘሁና በእጄ የተጋገረ ዳቦ ይዤ ስለነበር ለርሱ ሰጠሁት» በማለት አቡበክር ተናገሩ፡፡

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ “አንተ አቡበክር ዛሬ አንተን በጀነት
አብስሬሃለሁ ይህን ሁሉ ሥራ የሠራ ሰው ጀነት ሊበሰር ይገባዋል፡፡”
ዑመርም ደንገጥ አሉና “አቡበክር ሆይ! በምንም ነገር አንተን ቀድሜህ አላውቅም" አሏቸው።

                   ከባዱ ዘመቻ

   ሰይድ ዑመር(ረ.ዐ) እንዲህ ይላሉ፡- «በተቡክ ዘመቻ ጊዜ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደኛ መጡና ለዘመቻው ግልጋሎት ይውል ዘንድ እንድንወድቅ (እንድንመጸውት) ቅስቀሳ እደረጉልን። ይህ ሀሳብ በጣም ተስማማኝ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ ስለነበረኝ ዛሬ እበበክርን በመብለጥ አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡ ወደ ቤቴ ሄድኩና ካለኝ ገንዘብ ውስጥ ግማሹን ይዤ ተመለስኩና ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ፊት ዘረጋሁት፡፡ እሳቸውም «ለቤተሰቦችህ ምን ያህል
እስቀረህላቸው ብለው ጠየቁኝ። እኔም "ከገንዘቤ ግማሹን ትቼላቸዋለሁ::" አልኳቸው። አቡበክርም(ረ.ዐ) ምንም እንኳ ከዑመር ያነሰ ቢሆንም ቤታቸው ሄደው ገንዘባቸውን ሁሉ አንዲትም ሳያስቀሩ ጠራርገው በማምጣት ነብዩ(ሲ.ዐ.ወ) ፊት ዘረገፉት ነብዩም (ሰዐ,ወ) ለቤተሰቦችህ ምን ያህል አስቀረህላቸው አቡበክር? በማለት ጠየቋቸው:: አበበክርም «ለቤተሰቦቼ ከአላህና ከርሶ በስተቀር ምንም የተውኩላቸው ነገር የለም፡፡"  በማለት መልስ ሰጡ። እኔም እንዲህ አልኩኝ "አቡበክር ሆይ! ወላሂ
ከአሁን በኋላ ካንተ ገር ለመፎካከር አልሞክርም።"  ሃብት ንብረታቸውን በመሉ ለአላህ (ሱ.ወ) ዲን ሲሉ ለሶስት ጊዜያት ያህል የሰጡት ብቸኛ ጀግና አቡበክር አስ-ሲዲቅ ናቸው፡፡

   እስቲ ጥቂት ቆም ብለን ራሳችንን እንጠይቅ! ማነው እስቲ ከኛ
ውስጥ ለአላህ (ሱ.ወ) ብሎ የተቸገሩ ወገኖቹን ለመርዳት ገንዘቡን ሁሉ የሚሰጥ ሰዎች አሁንም ሞልተዋል፡፡ እኔ ራሴ በዐይኔ አንድ በጣም ደካማ ሰው የቦስኒያ ሙስሉሞችን ለመርዳት ራሱ የሚጠቀምበትን ዊልቸር ሲቸር ተመልክቻለሁ፡፡ አንዲት ሴትም ምንም ነገር ስላልነበራት ሙስሊሞችን ለመርዳት የራሷን ጌጣ ጌጦች ስትሰጥ አይቻለሁ፡፡ በዚህ ኡማ ውስጥ የአቡበክርን ዓርአያነት የሚከተል ሰው ሞልቶናል፡፡ ይህ ዓይነቱ ድንቅ ዓርአያነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንመኛለን፡፡

  አቡበክር ገንዘባቸውን ሁሉ ለአላህ (ሱ.ወ) ሲሉ ሶስት ጊዜያት
ያህል መጽውተዋል ብለናል፡፡ እነርሱም፡-
-አንዲት ሚስኪን ሴት ከባርነት ነጻ ሲያወጡ፣
- ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ወደ መዲና ሲሰደዱና
- አሁን እንዳልነው በተቡክ ዘመቻ ወቅት ናቸው፡፡

          ለአላህህ (ሱ.ወ) የነበራቸው ፍራቻና ክብር

    ከዕለታት አንድ ቀን የአስ-ሲዲቅ አገልጋይ ለአቡበክር ምግብ
ያቀርብላቸዋል፡፡ አቡበክርም ትንሽ ቀመስ ያደርጉለታል፡፡ አንድ ምግብ ሲቀርብላቸው የምግቡ አመጣጥ ከየት እንደሆነ የመጠየቅ ልምድ ነበራቸው፡፡ በዚህም መሠረት አገልጋያቸውን የምግቡን ምንጭ ይጠይቁታል፡፡ ‹‹ሙስሊም ከመሆኔ በፊት ለስዎች እጠነቁል ነበር፡፡›› በወቅቱ አንድ የጠነቆልኩለት ሰው የነበረበትን ዕዳ ኣሁን ስለከፈለኝ በዚሁ ገንዘብ ነው ይህን ምግብ የገዛሁት ይላቸዋል፡፡

   አቡበክርም በጣም ተደናግጠው «አጥፍተኸኝ ነበር›› ይሉና
ጣታቸውን ወደ ጉሮሮዋቸው ሰድደው የገባውን ለማውጣት ከራሳቸው ጋር መታገል ይጀምራሉ፡፡ ይህን የተመለከቱ ሰዎች በላዩ ላይ በብዛት ውሃ ጠጥተው ካልሆነ ሊወጣሳቸው እንደማይችል ይነግሯቸዋል። ውሃ አምጣልኝ ብለው ያዛሉ፡፡ የመጣላቸውን ውሃ በደንብ ከጠጡ በኋላ እንዲያስታውካቸው በማድረግ የቀመሱትን ጥቂት ጉርሻ ነቅለው ያወጡታል፡፡ ሁኔታውን የሚመለከቱት ሰዎች ‹‹አላህ ይዘንሎት! ትንሽ ነበርች›› ይሏቸዋል፡፡ እርሳቸውም «ወላሂ  ነፍስህ ካልወጣች በስተቀር አትወጣም ነበር ብባል እንኳ ጎልገዬ አወጣት ነበር” ይላሉ፡፡

              አስገራሚ ትህትናቸው

በመዲና ከተማ ውስጥ ባጋደለ ደሳሳ ጎጆ ውስጥ የምትኖር
አንዲት ድሃ አሮጊት ሴትዮ ነበረች፡፡ አቡበክር አስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) በየሳምንቱ ወደ ቤቷ እየሄዱ ቤቱን አጽድተውላት ይመለሱ ነበር፡፡

     ከዕለታት አንድ ቀን ሰይድ ዑመር (ረ.ዐ) የባልቴቷን ደካማነት ይሰሙና ሊጠይቁዋት ቢሄዱ ቤቷ ጥርት ባለ ንጽህና መያዙን ያዩና እንዲህ አድርጎ የሚያጸዳላት ማን እንደሆነ ይጠይቋቸዋል፡፡ ሴትየዋም ማንነቱን የማያውቁት አንድ ሰው በየሳምንቱ እየመጣ እንደሚያጸዳላቸው ይነግሯቸዋል፡፡

    ሰይድ ዑመርም የዚህን ደግ ሰው ማንነት ማወቅ ይኖርብኛል
በማለት በሳምንቱ ተደብቀው መጠባበቅ ይጀምራሉ፡፡ ዑመር(ረ.ዐ) ሁኔታውን እንዲህ ይተርካሉ፡፡ «አቡበክር(ረ.ዐ) መጥተው ቤቱን አንኳኩ፡፡ በሩ እንደተከፈተላቸው አሮጊቷን ወደ ውጪ ደግፈው አወጧቸውና ቤቱን ካጸዱ በኋላ ሴትየዋን ወደ ነበሩበት መልስው ወዲያው በመውጣት ወደ መጡበት አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡››

  ኧረ ለመሆኑ ! እስኪ ማነው ከእኛ ውስጥ ሃቃቸው የማያልቀውን
እናት አባቱን እንኳ እንዲህ አድርጎ የሚያገለግለውና የሚያግዘው?
ራሳችንን መጠየቅ አለብን፡፡

       ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ስስል ሲዲቅ የነበራቸው ውዴታ

  አንድ ቀን ሶሀባዎች በተሰበሰቡበት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ወደ መስጂድ ገቡና ‹‹አቡበክርስ የታለ?›› ሲሉ ጠየቁ፡፡ አቡበክር ቆም አሉ "ና አጠገቤ ሁን” አሏቸው፡፡ “ዑመርስ የት አለ” ሲሉ አስከተሉ፡፡ እርሳቸውም ቆም ሲሉ ‹‹ና አጠገቤ ሁን›› አሉና የሁለቱንም ሶሀቦች እጅ ይዘው ከፍ
በማድረግ እንዲህ አሉ “በዕለተ ትንሳኤ ልክ እንደዚህ ነው
የምንቀሰቀሰው፡፡”

   ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ከሰው ሁሉ ማንን ይበልጥ እንደሚወዱ ሲጠየቁ ‹‹ዓኢሻን› አሉ፡፡ ከወንዶችስ ሲባሉ ‹‹አባቷን አቡበክርን›› አሉና እንዲህአሉ «አቡበክር ሆይ! በዋሻው ውስጥ ጓደኛዬ እንደነበርከው ሁሉ የጀነትን መጠጥ (ሐውድ) ሳከፋፍልም የቅርብ ጓደኛዬ ትሆናለህ፡፡»

  ከዕለታት አንድ ቀን ሰይድ ዑመር በአንዲት ንግግር አቡበክርን ያኮርፏቸውና ጥለዋቸው ይሄዳሉ፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) ከኋላ እየተከተሉ "ዑመር እባክህ አትቆጣ ይቅር በለኝ” ቢሏቸው ዑመር(ረ.ዐ) ዝም ብለዋቸው ሄዱ፡፡

  ሰይድ አቡበክር(ረ.ዐ) ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሄዱና እንዲህ አሏቸው «ዑመርን ይቅርታ አድርግልኝ፣ ታረቀኝ ብለው እንቢ አለኝ ከዚያም ዑመር ትንሽ ቆይተው...
http://t.me//@arebgendamesjid
--------ኢንሻአላህ ይቀጥላል.......

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
104 views18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ