Get Mystery Box with random crypto!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ne_siha_eslamik — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ne_siha_eslamik — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የሰርጥ አድራሻ: @ne_siha_eslamik
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.26K
የሰርጥ መግለጫ

بسم الله الرحمن الرحيم
📮እንኳን ወደዚህ ቻናል ተቀላቀሉ‼️
በዚህ ቻናል ቂርአቶችን፣ ሙሐድራዎችን፣ዳዐዋዎችን እና ሌሎችንም ከአረብገንዳ መስጊድ በአሚሩ አማካኝነት በቀጥታ የምታገኙበት ቻናል ነው።
ሃሳብ አስተያዬት ካለ በዚህ ያድርሱን ⤵️
@ye_Arebgenda_mesgid_wetatoch_bot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-10-10 15:24:08 #የኢብሊስ_አሟሟት

ዱንያ ልትጠናቀቅ ጥቂት ሲቀራት እና ጡሩንባው
ከመነፋቱ በፊት የሰው ልጆች በየመገበያያዎቻቸው ላይ
በመገበያየት ላይ ሳሉ ድንገት ከፍተኛ ድምፅ ይፈጠርና
ከምድር ሰዎች ግማሹ በድንህጋጤ ሲሞት የተቀሩት
ደግሞ ልክ አውሬ እንዳየ እንስሳት ይደናበራሉ።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉም ብዙ ሳይቆዩ ከወደ ሰማይ በኩል
ከፍተኛ የሆነ እና የመብረቅ ነጎድጓድ መሳይ ድምፅ
መጥቶ የተቀረውን ፍጥረት ከሙታን ተርታ ያሰልፋል።
ያን ግዜ ምድር ከህያዋን ፍጥረታት ባዶ ትሆናለች።
ጂኖች፣ ሰዎች እና ሰይጣናት በሙሉ ሙተው ምድር ላይ
ኢብሊስ ብቻውን ይቀራል።ይህች ቅፅበት በአላህ እና
ለኢብሊስ መካከል የነበረችዋ ቃል ኪዳን ምትፈፀምባት
ናት።
አላህም ለመለከል መውት እንዲህ ይለዋል፦"እኔ
በመጀመሪያዎቹም በመጨረሻዎቹም ፍጥረታቴ ቁጥር
ያህል ረዳቶችን መድቤልሃለሁ። የሰማይን እና የምድር
ነዋሪያንን ጉልበት ሁሉ ሚያክል ላንተ ሰጥቼሀለሁ።
ዛሬ የቁጣን እና የበቀልን ልብስ አልብሼሀለሁ። በበቀል
እና በቁጣ ተሞልተህ ወደ ረገምኩት ኢብሊስ ውረድ።
ሞትንም አቅምሰው። ከሞት ምሬትም ፍጥረታት፣ ጂኖች
እና ሰዎች ሁሉ የቀመሱትን እጥፍ ድርብ አድርገህ
አቅምሰው።
ዘባኒያዎችም የጀሀነምን ሰንሰለት ይዘው ይጠብቁሀል።
ከጀሀነም በሆኑ 70,000 አውሬዎችም ተጠቅመህ ግም
የሆነች ነፍሱን ገሽልጣት።ከዝያም ማሊክ/የጅሀነም
ጠባቂን በሯን እንዲከፍት ጥራው" ይላል።
ከዝያም መለከል መውት ለአላህ ትዕዛዝ በመተናነስ ወደ
ምድር ፍፁም አስፈሪ በሆነ ገፅታው ይወርዳል። በዚያ
ገፅታው ሰው፣ጂን እና መላዕክት ቢመለከቱት ትዕይንቱን
መቋቋም አቅቷቸው ይቀልጡ ነበር።
መለከል መውት ምድር ወርዶ ልክ ኢብሊስን
እንደተመለከተው በከፍተኛ ድምፅ ይጮህበት'ና ኢብሊስ
ራሱን ሲስት አንድ ግዜ ይጠልዘዋል።
ይህን ግዜ መለከል መውትም እየተከተለው፦"ቁም አንተ
እርጉም ዛሬ ባጠፋኸው ነፍስ ቁጥር ሁሉ አንተንም ሞትን
አቀምስሃለሁ። ስንት እድሜ ጨርሰሃል!!! ምን ያህል ክፍለ
ዘመናትንስ ነው ፍጥረትን በማጥመም የከረምከው!!!!?
በጀሀነም ሚቆራኙህ ስንት ቁራኛዎች እንዳሉህ ብታይ!
ዛሬማ ባንተ እና በአላህ መካከል የነበረችው ቃል ኪዳን
ምትፈፀምበት ቀን ናት። ዛሬ ወዴት ትሸሻለህ!!!?"
ይለዋል።
ከዝያም ኢብሊስ ወደ ምስራቅ ጫፍ ይሸሻል። ይሁን
እንጂ ፊቱ ላይ መለከል መውትን ያገኘዋል። ባህር ውስጥ
ይሰምጣል። አሁንም ከፊቱ መለከል መውትን ያገኛል፤
ባህርም ይተፋዋል።
ምንም ሳይታክት በተቻለው መጠን ለመሸሽ ምድርን
ይዞራል። ይሁን እንጂ ምንም ማምለጫም ሆነ መሸሸግያ
አይኖርም።ከዝያም ምድር ወገብ ላይ የአደም ቀብር
በሚገኝበት ስፍራ ይቆም'ና፦"አንተ አደም!!! ባንተ ሰበብ
ነው እርጉም ሆኜ የቀራሁት። ምን ነበር ባልተፈጠርክ!'
ይላል።
ከዝያም ኢብሊስ ለመለከል መውት፦"በምን አይነት ፅዋ
ነው ሞትን ምታቀምሰኝ?! ይለዋል።
መለከል መውትም፦"በ ለዟ፣ በሰቀር እና በእሳት ሰዎች
ፅዋ ነው አባዝቼ እማቀምስህ" ይለዋል።
ይህን የተመለከተው ኢብሊስም ጥቂት መሬት ላይ በፀፀት
ይንከባለልና ወደ ምስራቅ እና ወደ ምዕራብ ሲመላለስ
ዘባኒያ የተባሉት የጀሀነም ወታደሮች ድሮ ኢብሊ ከሰማይ
የወረደባት ቦታ ላይ ከጀሀነም አውሬዎች ጋር ሁነው
ይይዙታል።
በአውሬዎቹ እየተዘረገፈ እና እየተሰቃየ ላልተወሰነ ግዜ
በጣዕረ ሞት ላይ ይቆያል። ከዝያም ሀዋ እና አደም
ትዕይንቱን እንዲያዩ ይደረጉ'ና፦"ጠላታችሁን ተመልከቱ።
የሞትን ፅዋም እንዴት እንደሚቀምስ እዩ" ይባላሉ።
ሀዋ እና አደምም፦"ጌታችን ሆይ!!! ፀጋህን እኛ ላይ
ሞልተህልናል" ይላሉ።


ቻናላችን
#join
ያድርጉና ይቀላቀሉ
http://t.me//@arebgendamesjid
✹••••━━✿ ❁ ✿━━••••

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
212 views12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 16:50:09 42ኛ  ሓዲስ

መሃርታን መጠየቅ እና ተውሒድ

:አነስ ኢብን ማሊክ የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ አለ፦ አላህ እንዲህ አለ “አንተ የአደም ልጅ ሆይ!አንተኮ በጠራሃኝ እና መሃርታን በጠየቅከኝ ግዜ ካንተ ምንም ቢኖርም እምርሃለሁ ወንጀልህ ቢበዛም ምንም አይመስለኚም። አንተ የአደም ልጅ ሆይ!ወንጀልህ ሰማይ ቢደርስኳ መሃርታን ከጠየቅከኝ እምርሃለሁ። አንተ የአደም ልጅ ሆይ!አንተኮ ምድርን የሞላ ወንጀል ይዘህ በእኔ ግን ሳታጋራ ወደኔ ብትመጣ ከዚያም ብትገናኘኝ እኔም እሷን በሞላ መሃርታ ወዳንተ እመጣ ነበር።”

ሓዲሱን ቲርሚዚይ ዘግቦታል

ከአርባ ሁለተኛው ሓዲስ የምንወስዳቸው ትምህርቶች

.የሰው ልጅ ኣላህን በለመነ እና ከኣላህ በከጀለ ቁጥር ኣላህ እንደሚምረው።
.የኣላህ እዝነትን እንረዳለን። 
.የሰው ልጅ ወንጀል ቢበዛም፣ ከኣላህ መሃርታን ከጠየቀ ኣላህ እንደሚምረው።  
ተውሒድ (ኣምልኮን ለኣላህ ብቻ ማድረግ እና ኣምልኮን ለኣላህ ብቻ ብሎ መስራት)በጣም ትልቅ ደረጃ እንዳለውና ወንጀላችንን እንድንማር እንደሚያደርግ።
 
:አርበዑነ ነወውያ(42 ሀዲሶች))
       ከ27ኛው -42 ኛው ሀዲስ ተጠናቀቁ

http://t.me//@arebgendamesjid
110 views13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 10:10:40

108 views07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 11:37:48

76 views08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 11:24:24 ┈ድንቅ ታሪክ ናት┈┉┅━

{በሙሳ ዐ.ሰ} በዘመን ነው ....
አንድ በጣም ድህነት ያጎሳቆላቸው ለዘመናት በችግር እና በረሀብ የኖሩ ባልና ሚስት ነበሩ።
ይሁን እንጂ ይህን ሁሉ ዘመናት በሰብር አሳልፈዋል.።

እናም አንድ ቀን እቤታቸው ጋደም ብለው ሳለ
#ሚስት #ለባለቤትዋ፦"ሙሳ አላህን ማናገር የሚችል ነቢይ ነው አይደል?" ብላ ትጠይቀዋለች።

#እሱም፦"አዎን" ይላታል።
"ታዲያ ለምን እሱጋ ሄደን ስለ ሁኔታችን አንነግረውም አላህንም ስለኛ ያናግረው ሀብታም እንዲያረገን ቀሪ ህይወታችንን በድሎት እንድንኖርም ይጠይቅልን።" አለችው።

ባልም በሚስቱ ሀሳብ ይስማማና ሌሊቱ እንደነጋ ጉዞ ወደ {ሙሳ ዐ.ሰ} ቤት ጀመሩ።
{ሙሳንም ዐ.ሰ} አገኟቸው። ስለድህነታቸው ነግረዋቸውም በዚህ ጉዳይ እሳቸው አላህን እንዲለምኑላቸው ጠየቋቸው።
{ሙሳም ዐ.ሰ} አላህን ለመኑላቸው።


#አላህም፦"ሙሳ ሆይ! እኔ እነዚህን ሰዎች በችሮታዬ ለአንድ አመት ያህል ሀብታም አደርጋቸዋለሁ ! አንድ አመት ካለፈም ወደነበሩበት ድህነት እመልሳቸዋለሁ። #ብሎ_መለሰላቸው።

እሳቸውም ጥንዶቹ ጋ በመሄድ  #አላህ ዱዓቸውን #ሙስተጃብ እንዳደረገላቸው። ሀብታምም እንደሚሆኑ ነግረዋቸው እናም ግን ለ አንድ አመት ቢቻ እንደሚቆይ አክለው ነገሯቸው። እነዚህ ምስኪኖችም የሰሙትን ማመን ተሳናቸው።

በአጭር ግዜ ውስጥ ካለሰቡበት መንገድ ሀብታም መሆን ጀመሩ ማንም ከሚኖረው የተሻለ ኖሮ መኖርም ጀመሩ። እናም አንድ ቀን ይህች ብልህ #ሚስት #ለባሏ እንዲህ አለችው፦

"ይህ ፀጋ ይህ ድሎት ለአንድ አመት ብቻ እንደሚዘገይ ታውቃለህ አይደል? ስለዚህ በዚህ ንብረታችን #አንድ_መልካም_ስራ_እንስራ
#ባልይውም በሀሳቧ ይስማማል።

ከዚያም በከተማዋ ግንባር ቦታ ላይ አደባባይ መልክ አንድ ትልቅ ቤት ይገነቡና 7 በር አበጁለት። ለሰውም መተላለፊያ ሰሩ። ቤቱ ተገንብቶ ካለቀ በኋላ እዛ ቤት ውስጥ ምግብ እያዘጋጁ ለአላፊ አግዳሚ #ጠዋት #ማታ ምግብ ይቀልቡ ጀመር...በዚህ ሁኔታ ሳሉ ወራት አስቆጠሩ።

#ሙሳም በትኩረት ይከታተሏቸው ነበር። ማይደርስ ቀን የለምና ያ የተወሰነላቸው ቀን ቀጠሮውን ጠብቆ ከች አለ። እነሱ ግን የቀጠሮ ቀኑ ሁላ ትዝ አላላቸውም በስራቸው ተጠምደዋል። ያ ቀጠሮ ቀናቸው አለፈ እነሱ ግን ያው ናቸው ምንም አልቀነሱም ብቻ በስራቸው ተጠምደዋል....

{ሙሳንም ዐ.ሰ} ባዩት ሁኔታ ተገርመው፦
#ያ_ረብ_ቃል_የገበኽላቸው_ለአንድ_አመት_ሆኖ_ሳለ_እንዴት_እስካሁን_እልደኸዩም?"ብለው አላህን ጠየቁ። እዚጋ እሳቸው ሰዎቹን ተመቃኝተው ሳይሆን #የአላህን_ሂክማ_ለማወቅ_ነው።


የጠየቁት/ ቸር የሆነው #አላህም፦ ሙሳ ሆይ ለነዚህ ጥንዶች ከፀጋ በሮቼ አንዲትን በር ስከፍትላቸው... እነሱ ደሞ 7 በር ከፍተው ባሪያዎቼን መቀለብ ጀመሩ።  ሙሳ ሆይ እነሱ ይሄን ሲያረጉ አይቼ የከፈትኩላቸውን በር መዝጋት ከበደኝ"አለው።

━┅┉┈ሱብሀን አላህ┈┉┅━

SHARE SHARE
http://t.me//@arebgendamesjid
አረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
135 views08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 13:38:21 Watch "ዝምድናን መቁረጥ || የጁሙአ ኹጥባ (በአማርኛ)|| ሸይክ ዑመር ዓሊ" on YouTube


241 views10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 06:56:00 # ኢልም ትልቅ ቦታ አለዉ

قال ابن الجوزي رحمه الله تعالىٰ
#ኢብኑ ጀዉዚይ አሏህ ይርሀማቿና እንዲ አሉ

من أحب أن يكون للأنبياء وارثًا وفي مزارعهم حارثًا فليتعلم العلم النافع وهو علم الدين ففي الحديث : « العلماء ورثة الأنبياء »،
#ለነቢያቶች ወራሽ በማሳቸዉ አራሽ ሊሆን የፈለገ ሰዉ ጠቃሚ እዉቀትን ይማር እሱም ዲንን ማወቅ ነዉ #በሀዲስ ዉስጥ "ኡለሞች የነቢያቶች ወራሽ ናቸዉ" ይላል
وليحضر مجالس العلماء، فإنها رياض الجنة،
#እንዲዉም የኢልም መቀመጮችን ይጣድ እሱዋ የጀነት ጨፌ ናት


ومن أحب أن يعلم ما نصيبه من عناية الله، فلينظر ما نصيبه من الفقه في دين الله، ففي الحديث : « من يرد الله به خيرًا يفقهه في الدين »،
#ከአለህ ትክረት ሆኖ ያለዉን ድርሻ ሊያዉቅ የፈለገ ሰዉ በአለህ ዲን ሆኖ ያለዉን ግንዛቤ ልክ ይመልከት #በሀዲስ ዉስጥ "አሏህ ኸይር ያሻለት ሰዉ በዲን ላይ ግንዛቤን ይሰጣዋል" ይላል

ومن سأل عن طريق تبلغه الجنة، فليمش إلىٰ مجلس العلم، ففي الحديث : « من سلك طريقًا يلتمس فيها علمًا سلك الله به طريقًا إلىٰ الجنة »،
#ወደ ጀነት ምታደርሰዉን መንገድ የጠየቀ የኢልም መቀመጫ ይሂድ በሀዲስ ዉስጥ "መንገድን የገባ በሱ ኢልምን ሚፈልግ ሴሆን አሏህ በሱ መሄድ ወደ ጀነት ያለ መንገድ ያስገቧል" ይላል

ومن أحب ألاّ ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم بالتدوين والتعليم، ففي الحديث : « إذا مات الإنسان انقطع عمله إلاّ من ثلاث صدقة جارية، أو علم ينتفع به، أو ولد صالح يدعو له » .
#ከሞተ ቦሃላ ኸይር ስራዉ ላይቁዋረጥበት የፈለገ ኢልምን በመፃፍም ና በማስተማር ያሰራጭ በሀዲስ ዉስጥ "ሰዉ የሞተ ግዜ ስራዉ ይቆረጣል ከሶስት ነገር ስቀር #ቀጣይነት ያለዉ ሰደቃ #ወይም ሰዎች ምጠቀሙበት ኢልም ያስቀመጠ #ወይም ጥሩ ልጅ ለሱ ዱዓ ምያደርግለት ልጅ ስቀር" ይላል!!

"التذكرة في الوعظ" (٥٥/١)**
{{ምንጭ "አተዝኺረቱ ፊል ወዕዚ" 1/55"}}
////
ኢልም.ኢልም.ኢልም.የዱኒያ.ና.የአኼራ.ብርሃን

ኢልምን እንዉረስም እናዉርስም አደራ አደራ

http://t.me//@arebgendamesjid
አረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
127 views03:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 17:10:57
340 views14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 17:10:35 ~ለውጤታማ ስራ~
ፍሬ ያለው መልካም ስራ መስራት ከፈለግክ የሚከተለውን መንገድ ተከተል። ምንዳው የተሟላ፤ ስራውም ስኬታማ ይሆንለሃል።
:የምትሰራውን ስራ አሳንሰህ ተመልክተው። ካሳነስከው ከመኩራራት ትጠበቃለህ፤ ስራውም ይተልቅለሃል።
:የምትሰራውን ስራ ደብቀው። ከደበቅከው ሪያእ/ታይታ/ ስራህን አያበላሸውም።
:የጀመርከውን ስራ አፍጥነው። ካፈጠንከው ከሸይጧን የውስወሳ ወጥመድ ታመልጣልህ። ከመጥፎ ጥርጣሬም ትድናለህ

http://t.me//@arebgendamesjid
አረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
323 views14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 10:22:38 Watch "ዝምድናን መቁረጥ//የጁምዐ ኹጥባ//" on YouTube


351 views07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ