Get Mystery Box with random crypto!

መዝሙረ ዳዊት

የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmurochh — መዝሙረ ዳዊት
የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmurochh — መዝሙረ ዳዊት
የሰርጥ አድራሻ: @mezmurochh
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 43.70K
የሰርጥ መግለጫ

🔔🔔🔔 መዝሙረ-ዳዊት 🔔🔔🔔

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት ይቀላቀሉ
☞ @mezmurochh
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት
☞ @Mezmuredawit_bot ላይ ያገኙናል

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-05-07 15:21:01 ሚያዝያ_30

ቅዱስ_ማርቆስ_ሐዋርያ

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሚያዝያ ሠላሳ በዚች ቀን ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳት አለቃ የሆነ ወንጌልን የጻፈ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት አረፈ።

የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አርስጦቡሎስ ነው እርሱም ከአምስቱ አገሮች የሆነ የእናቱም ስም ማርያም ነው እርሷም በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ተጽፋለች እርሱም አስቀድሞ ስሙ ዮሐንስ ነው። በግብረ ሐዋርያት ማርቆስ በተባለ በዮሐንስ እናት ቤት ሐዋርያት ይጸልዩ ነበር ተብሎ እንደ ተጻፈ። እርሷም ባለጸጋ ነበረችና የዮናናውያንን የሮማይስጥን የዕብራይስጥን ትምህርት ለልጅዋ ለማርቆስ አስተማረችው።

በአደገም ጊዜ በርናባስ ወንጌልን ለመስበክ ከጳውሎስ ጋራ ሲሔድ ይዞት ሔደ በእነርሱም ላይ የሚደርስባቸውን መከራ አይቶ በጵንፍልያ ከተማ ሳሉ ትቷቸው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።

ሐዋርያትም በተመለሱ ጊዜ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን አሕዛብ እንደ ተመለሱ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ላይ ድንቅ ተአምራትን እንዳደረገ ተናገሩ። ይህ ብላቴና ማርቆስም ከእርሳቸው ስለ መለየቱ አዘነ ተጸጸተ።

ከዚያም አብሮአቸው ሊሔድ ፈለገ አስቀድሞ ትቷቸው ስለተመለሰ ጳውሎስ ሊአስከትለው አልወደደም በርናባስ ግን ወሰደው አጎቱ ነውና። በርናባስም ከአረፈ በኋላ ወደ ሮሜ አገር ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ሒዶ ለእርሱ ደቀ መዝሙሩ ሆነ በዚያም ቅዱስ ጴጥሮስ የተረጐመለትን ወንጌልን ጻፈ በሮሜ አገርም አስተማረበት። ከዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዝና በሐዋርያትም ትእዛዝ ወደ እስክንድርያ አገር ሔደ። በውስጥዋም የከበረ ወንጌልን አስተማረ ደግሞም በአፍራቅያና በአምስቱ አገሮች በርቃ በሚባልም አገር ወደ እስክንድርያ ከተማ በገባ ጊዜ ጫማው ተቆረጠ።

በዚያም በከተማው መግቢያ ጫማ ሰፊ ነበረ። ቅዱስ ማርቆስም እንዲሰፋለት ለርሱ ሰጠው ሲሰፋም ጣቱን ወግቶ ሰነጠቀው ከእርሱም ደም ፈሰሰ በዮናኒም ቋንቋ ኢታስታዖስ አለ ትርጓሜውም አንድ እግዚአብሔር ማለት ነው። ቅዱስ ማርቆስም ስሙን የምትጠራው አውቀኸው ነውን አለው እንጠራዋለን እንጂ አናውቀውም አለ።

እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ከፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ አባታችን አዳም ትእዛዙን እንደተላለፈ የጥፋት ውኃም እንደ መጣ ሙሴንም እንደላከውና እስራኤልን ከግብጽ እንዳወጣቸው ሕግንም እንደ ሠራላቸው ናቡከደነጾርም ወደ ባቢሎን ማርኮ እንደወሰዳቸውና ከሰባ ዓመት በኋላ ወደ አገራቸው ኢየሩሳሌም እንደ ተመለሱ ክርስቶስ ሥጋ በመልበስ ወደ ዓለም ስለ መምጣቱ ነቢያት ትንቢት እንደ ተናገሩ ያስተምረው ዘንድ ጀመረ።

ከዚያም በኋላ ወደ ምድር ምራቁን ትፍ ብሎ ጭቃ አድርጎ ጣቱን ቀባው ወዲያው ዳነ በጌታችንም አመነ። ያም ሰፊ ስሙ አንያኖስ ነው። ቅዱስ ማርቆስንም ወደ ቤቱ ወስዶ ልጆቹን ዘመዶቹንም ወደ ርሱ አቀረበ እርሱም አስተምሮ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው።

በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑ ሰዎች በበዙ ጊዜ የቅዱስ ማርቆስን ዜና ሰምተው የአገር ሰዎች ሊገድሉት ተሰበሰቡ እርሱም አንያኖስን ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሹሞ ልጆቹን ቄሶችና ዲያቆኖች አድርጎ ከዚያም ወደ በርቃ ወደ አምስቱ አገሮችም ወጥቶ አስተማረ። በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው በእርሳቸውም ዘንድ ሁለት ዓመት ኖረ ኤጲስቆጶሳትን ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው።

ከዚህም በኋላ ወደ እስክንድርያ ተመለሰ ምእመናንም ተጨምረው በዝተው በታወቁ ቦታዎች ሁሉ በባሕሩም ዳር በላሞች መካበቢያ በሚባለውም አብያተ ክርስቲያን ሠርተው አገኛቸው።

ከሀድያንም የከበረ ሐዋርያን ይገድሉት ዘንድ በብዙ ድካም ፈለጉት እርሱም አምስቱን አገሮች ሲጐበኝ በሥውር ወደ እስክንድርያ ከተማ ይገባ ይወጣ ነበር። በአንዲትም ዓመትም ከአምስቱ አገሮች ተመልሶ ሚያዝያ ዐሥራ ሰባት ቀን በመድኃኒታችን የትንሣኤ በዓል ወደ ቤተክርስቲያን ገባ ሕዝቡም ሁሉ በዙሪያው አሉ። ከሀድያንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተው በአንገቱ ውስጥ ገመዶችን አድርገው በከተማው ሁሉ ጎተቱት። እነርሱም ገና እንደፍየል ሙክት እንጎትተዋለን እያሉ ይጮኹ ነበር። በላሞች መካበቢያና በሀገሪቱ አደባባይ በከተማውም ዙሪያ በየቀኑ ሲጎትቱት ኖሩ።

ሌሊትም በሆነ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሐዋርያት ጋራ በነበረበት አርአያ ሁኖ ተገለጠለት ሰላምታም ሰጥቶ አጽናናው ቃል ኪዳንም ሰጠው። እነሆ አንተ ከወንድሞችህ ሐዋርያት ጋር ተካከልህ አለው። እርሱም በልቡናው ፈጽሞ ደስ አለው። በማግሥቱም ሁለተኛ ገመዶችን በአንገቱ አድርገው በአገሮች ሁሉ ጎተቱት በቀኑም መጨረሻ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።

ከሀዲዎችም ታላቅ እሳትን አንድደው የቅዱስ ማርቆስን ሥጋ ከውስጡ ጨመሩ። በክብር ባለቤት ጌታችን ፈቃድም ንውጽውጽታ ጨለማ ቀዝቃዛ ነፋስ መብረቅና ነጐድጓድ ሆነ። ፀሐይም ጨለመ ከሀዲዎችም ሸሹ ምእመናንም መጥተው የሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስን ሥጋ ወሰዱ ምንም ጥፋት ሳይደርስበት ደኀና ሆኖ አገኙት በመልካም ልብስም ገንዘው በጥሩ ቦታ አኖሩት መታሰቢያውንም አደረጉ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ማርቆስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሚያዝያ)

6 ኪሎ የሚገኘው ቅዱስ ማርቆስ መቶኛ አመቱን ያከብራት ተገኝተን የበረከቱ ተካፋይ እንድን ሆን በአምላከ ቅዱሳን ስም እንጠይቃለን
4.8K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 11:22:32
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥ 
@teksochina_meslochi
  ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
4.3K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 11:22:15 ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

  መዝሙረ ዳዊት

ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

           ◉ ስምሽን ስጠራው◉

  ✥ መዝሙረ ዳዊት / በ ቴሌግራም/ ✥

              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
            @mezmurochh    
            @mezmurochh    
            @mezmurochh    
              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
4.1K views••●◉ Estifanos ◉●••, 08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 11:22:06 ✞ ስምሽን_ስጠራው

ስምሽን ስጠራው ድንግል
ስምሽን ስጠራው ማርያም
ላንደበቴ ማር ነው ለልቤ ሰላም
ስምሽን ስጠራው ማርያም

ትውልድ ነኝና ልጅሽ የፈጠረኝ
ድንግል እመቤቴ ላንቺ ምስጋና አለኝ
በፈቃደ እግዚአብሔር ባባቶቼ ፀጋ
ሳዓሊ ለነ እላለው ሲመሽም ሲነጋ

አዝ___

በጠየቅሽው ጊዜ ወይኑን እንዲመላ
አክብሮሻልና በቃና ገሊላ
የሰላም እናት ሆይ ሰላም ልበልሽ
ዘመኔ ይፈፀም ሳመሰግንሽ

አዝ__

በሰላምታ ድምፅሽ መንፈስ ተመልቼ
አደግድጌ ልቁም እጆቼን ዘርግቼ
በአብይ ቃል ጮሄ ልመስክር በብርቱ
ቅድስት ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር እናቱ

አዝ__

ከሰማይ ሲገኝ ነው አንችን ማወደስ
ሲገለጥ ሲፈቀድ ከመንፈስ ቅዱስ
ማርያም ህይወቴ ነሽ ምክንያት ለመዳኔ
ብዙ ነው ምስጢሩ አንችን ማመስገኔ

መዝሙር
ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

   ╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
   ✥      @mezmurochh     ✥
   ✥      @mezmurochh     ✥
   ✥      @mezmurochh     ✥
   ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
4.3K views••●◉ Estifanos ◉●••, 08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 14:15:02
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥ 
@teksochina_meslochi
  ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
4.9K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 14:14:56 ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

መዝሙረ ዳዊት

ዘማሪ ታድዮስ ግርማ

✣ አማኑኤል ናና ✣

✥ መዝሙረ ዳዊት / በ ቴሌግራም/ ✥

|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
@mezmurochh
@mezmurochh
@mezmurochh
|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
4.6K views••●◉ Estifanos ◉●••, 11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 12:57:15
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥ 
@teksochina_meslochi
  ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
3.3K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 12:56:57 ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

  መዝሙረ ዳዊት


       ✣ ተነግሮ የማያልቅ ነው ✣

  ✥ መዝሙረ ዳዊት / በ ቴሌግራም/ ✥

              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
            @mezmurochh    
            @mezmurochh    
            @mezmurochh    
              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
3.2K views••●◉ Estifanos ◉●••, 09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 12:56:57 ተነግሮ የማያልቅ

ተነግሮ የማያልቅ ነው ጸጋህ/2/
በጸሎት የተጋህ የሐይማኖት ፍሬ
ተክለ-ሃይማኖት የእምነቱ ገበሬ /2/

  
በወንጌል ብርሀን ሕዝቡን የመራኸው
የኃጢአቱን ባህር ከፍለህ ያሻገርከው
ኢትዮጰያዊው ሙሴ በመስቀልህ ባርከን
ፍሬ እንድናፈራ ንጹሕ ዘር አድርገን /2/

አዝ-----------

ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለሃይማኖት
ወንጌል ያስተማርከን ለክርስቶስ መንግስት
ፀበልህ እንዲምረን ውረድ አባታችን
በእጣንህ መአዛ ይፈወስ ደዌአችን /2/

አዝ-----------

ለማጠን የበቃህ የሥላሴን መንበር
ሰይጣን ከቶም አይደርስ በሄድክበት ሀገር
ለህሙማን ሁሉ የሆንካቸው ፈውስ
ጠብቀን ተክልዬ በሥጋም በነፍስ/2/

አዝ-----------        

በጣሙን የበዛ ትሩፋት ምግባርህ
ፀሎትህን ያልተውክ ቢቆረጥ አንድ እግርህ
ምዕራፈ ቅዱሳን የወንጌል ገበሬ
እኛንም አድነን ከዚህ አለም አውሬ /2/

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

   ╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
   ✥    
@mezmurochh     ✥
   ✥    
@mezmurochh     ✥
   ✥    
@mezmurochh     ✥
   ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
3.0K views••●◉ Estifanos ◉●••, 09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 12:14:15
ጉባኤ አቅሌስያ

    የእግዚአብሔር ፍቅር የበዛላችሁ የሊቀ መላእክቱ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ሆይ እነሆ በጎ ስራ በመስራት እግዚአብሔርን ደስ የምናሰኝበት ጊዜ ደረሰ።

    በማዕከላዊ ጎንደር በለሳ ወረዳ ቤተክህነት የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ከፍተኛ የሆነ የህልውና ችግር አጋጥሞታል።
    
      ስለክርስቶስ ስም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ ገዳማውያን አበው መነኮሳት እና መነኮሳይት ከማይታየው ፣ ከማይዳሰሰውና ከማይጨበጠው ጠላታችን ጋር በፆም በፀሎት  ሲዋጉልን በአለም ከሚገጥማቸው ችግር ደግሞ ልናግዛቸው የመንፈስ ልጆቻችሁ አለን ልንላቸው ይገባናል።

     ስለሆነም ገዳሙ ከቁስቋም ቅድስት ማርያም መንፈሳዊ ማህበር ጋር በመተባበር ግንቦት 6 ቀን  2015 ዓ.ም ታላቅ የሆነ ጉባኤ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዮኒቨርስቲ አራተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው አዳራሽ አዘጋጅቷል።
   

    በዕለቱም ትምህርተ ወንጌል

    1- መምህር ጳውሎስ መልከዐ-ሥላሴ
    2- መጋቢ ሀዲስ እሸቱ አለማየዉ
    3-መምህር አንተነ አበበ እና ሌሎች መምህራን

    እንዲሁም  በዝማሬ
      1- ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
      2- ዘማሪት ሲስተር ሊድያ ታደሰ እና ሌሎችም የሚቀርብ ሲሆን

የተለያዩ የኪነጥበብ ስራዎችም በተለያዩ አርቲስቶች
    1-አርቲስት ቸርነት ፍቃዱ እና ሌሎችም ይቀርባል


ኑ የወንጌል ማዕድ እየተቋደስን ስለኛ የተራቡ ገዳማውያንን አለን እንበላቸው።

ለበለጠ መረጃ:-0986348964 ወይም 0912779749

ገዳሙን ድጋፍ ማረግ ለምትፈልጉ በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 1000442598391 ሙት አንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል ገዳም 

ወዳጄ ሆይ የቅዱሳን ገዳማውያን ገድልና የህወታቸው ኑሮ ለሁሉም መልካም ምሳሌና አርአያ ሊሆን ይችላል ።
6.4K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ