Get Mystery Box with random crypto!

መዝሙረ ዳዊት

የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmurochh — መዝሙረ ዳዊት
የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmurochh — መዝሙረ ዳዊት
የሰርጥ አድራሻ: @mezmurochh
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 42.70K
የሰርጥ መግለጫ

🔔🔔🔔 መዝሙረ-ዳዊት 🔔🔔🔔

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት ይቀላቀሉ
☞ @mezmurochh
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት
☞ @Mezmuredawit_bot ላይ ያገኙናል

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-03-22 16:55:15
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥ 
@teksochina_meslochi
  ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
12.7K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-11 12:36:07 ዘወረደ /ዘመነ አዳም/

የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡ ዘወረደ ማለት፣ ከላይ የመጣ፣ የወረደ ማለት ነው፡፡ ይህም የአምላካችን ሰው መሆን ያመለክታል፡፡ ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም ካለው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሳት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዕለት ምስባክ “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ” በማለት በጾመ ድጓው መጀመሪያ ላይ ገልጾት ይገኛል፡፡
አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት፣ የሰማይን ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም ብሎ ተናግሮ ነበር፡፡ ይህም ድርሰት በቤተ ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የሆነው ዕለተ ሰንበት ዋዜማ፣ መግቢያ፣ /መሐትው/ ሆኖ ከዋዜማ በፊት ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፡፡ ይዘመራል፡፡ ይመሰገናል ማለት ነው፡፡
ስለዚህ የሳምንቱ ስያሜ ከዚህ የተወሰደ ነው፡፡ እንዲሁም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን የጀመረው፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው በመሆን ፣ በዮርዳኖስ ተጠምቆ በማስተማር እንደሆነ ሁሉ የመጀሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
በዚህ ሳምንት በተለይም እሑድና ሰኞ የሚነገሩት ውዳሴያት ከመጻሕፍተ ኦሪትና ነቢያት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሁለተኛም ሙሴኒ በመባል ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን ለማዳን ከሰማይ መውረዱንና በመስቀል መሰቀሉን ስለሚያወሳ ነው፡፡
የቤተ ክርስቲያናችን ታሉቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ በዘወረደ ጾመ ድጓው ሰንበት ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን፣ ሕይወት ላለው ነገር ሁሉ ጸጥታና ሰላም የሰፈነባት የዕረፍት ቀን ስለመሆኗ “አዘዞ እግዚአብሔር ለሙሴ ወይቤሎ ሰብዕከ ወላህምከ ወኲሉ ቤትከ ያዕርፍ በሰንበት” ዘፀ.20፥10፣23፣12፣ ጾመ ድጓ፣ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝብህ የከብትህ መንጋህ ቤተሰብህ ሀሉ በሰንበት ቀን ከድካማቸው ይረፉ በማለት አዘዘው ይላል፡፡ በዚህም ዘመነ ጾም፣ ወይም ጾመ ሙሴ ይባላል፡፡
በጾመ ድጓው ዘወረደ እየተባለ የሚታወቀው፣ በጾመ አርባው ወቅት በተለይም በመጀመሪያው ሳምንት የሚገኘው ያሬዳዊ ድርሰት በነግህ በሠለስት፣ በቀትርና በሠርክ እንዲሁም ቅዳሜና እሑድ በሌሊት የሚዘመር ነው፡፡ በውስጡም የያዘው ፍሬ አሳብ፣ የጾምን፣ የጸሎትን፣ የምጽዋትንና የፍቅርን ጠቃሚነት አጉልቶ የሚያስተምር ነው፡፡
በዚህ በጾም ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት በአብዛኛው ከቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ የሚዘመረው ምዕራፍ የተባለው ነው፡፡ ምዕራፍ የተባለበት ምክንያትም በየመዝሙራቱ መሀል ሃሌታና ድጓ እያስገባ ለመዝሙሩ ማረፊያ ስላበጀለት በዚህ ምክንያት ምዕራፍ የሚል ስያሜ ሊያገኝ ችሏል፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በሁለት ታላላቅ ክፍሎች ይከፈላል፡፡ ይኸውም የዘወትር ምዕራፍና የጾም ምዕራፍ በመባል ይታወቃል፡፡የዘውትር ምዕራፍ የሚባለው በዓመቱ ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ ሳምንታትና በዓላት ሁልጊዜ በአገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን፣ የጾም ምዕራፍ የሚባለው ደግሞ በጾመ አርባ ብቻ ለአገልግሎት የሚውል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በዐሥሩ ምህላት አርዕስተ ምህላ በዚሁ ክፍል ይካተታል፡፡ የምዕራፍ ቅንብር ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከድጓና ከጾመ ድጓ ጋር የተቀናጀ ነው፡፡ የትምህርት አሰጣጡም እንደ ድጓው ወይም እንደ ዝማሬ መዋሥዕቱ መጽሐፍ ተዘርግቶ ሳይሆን በቃል የሚጠናና የሚወሰን ነው፡፡ ስለሆነም ምዕራፍን ለመማር 150 መዝሙረ ዳዊትን፣ ከነቢያት 15 ምዕራፎችንና 5 መኃልያተ ሰሎሞንን በቃል ሸምድዶ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ወይም ግድ ነው፡፡
ጾምን መጾም የፈቃድ ብቻ ሳይሆን የትእዛዝም ነው፡፡ በዘመነ ብሉይ ነቢዩ ኢዩኤል “ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ” ጾምን ያዙ አጽኑ ምሕላንም ዐውጁ ሸማግሌዎቹን ከፈጣሪያችን ቤት ሰብስባችሁ በአንድነት ሁናችሁ ወደ እግዚአብሔር ጩሁ /ለምኑ/ ብሏል፡፡ ኢዮ.ምዕ.1፥11፣ 2፣12፣15-16 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ወኲኑ ላዕካነ፣ ለእግዚአብሔር በጾም ወበንጽሕ፡፡ በጾም፣ በንጽሐና ተወስናችሁ እግዚአብሔርን አገልግሉ ብሏል 2ቆሮ.6፥4-6፡፡
ጾም ከሌለ ወይም ተገቢ ካልሆነ ጌታችን በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ ስለ ጽድቅ የሚራቡ የሚጠሙ ንዑዳን ክብራን ናቸው ለምን አለ? ማቴ.5፥፣6፣16፡፡ ነቢዩ ዳዊትም ሰውነቴን በጾም አሳመምኳት በቀጠና፣ በሰልት አደከምኳት ለምን አለ መዝ.34፥68፣ ት.ዳን. 9፥3-4፣ 14፥5
ነብዩ ሚኪያስ ሐዋርያት ሙሸራውን ከነሱ ለይተው የሚወስዱበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ያለውን የጌታን ቃል መሠረት በማድረግ ክርስቶስ በሞት ከተለያቸው በኋላ ጾመዋል፡፡ ጾምንም ሠርተዋል የሐዋ.ሥራ 13፥3፡፡ ሠለስቱ ምዕትም ሐዋርያት የጾሙትንና እንዲጾም የወሰኑትን መጾም ይገባል ብለው ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸውን አጽዋማት እንዲጾሙ መወሰናቸው ይህን የጌታ ቃል መሠረት በማድረግ ስለሆነ፣ የትእዛዝ መሆኑን ተገንዝበን መጾም አለብን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠራዔ ሕግ እንደመሆኑ አርባ ቀን አርቦ ሌሊት ጾመ እንጂ እርሱ ሳይጾም ጾሙ አላለንም ማቴ.4፥2፡፡

ሠናይ መዋዕለ ጾም፡፡

የተሣተውን ፤ የተረሳው፤ የተገደፈውን፤ የነጠፈውን በቀና መንፈስ አቃንታቹ አንብቡት     
                             
ስለ  ማይነገር ስጦታው   እግዚአብሔር ይመስገን

ለመቀላቀል  
      ┏━━° •❈• ° ━━┓
      @mezmurochh
     @mezmurochh
     @mezmurochh
      ┗━━° •❈• ° ━━┛

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን
13.3K views••●◉ Estifanos ◉●••, 09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-05 10:37:51
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥  @teksochina_meslochi ✥
  ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
13.2K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-20 17:23:07 ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

መዝሙረ ዳዊት

◦ በቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

✧ ቸርነትህ ነው ✦

✥ መዝሙረ ዳዊት / በ ቴሌግራም/ ✥

|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
@mezmurochh
@mezmurochh
@mezmurochh
|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
22.5K views••●◉ Estifanos ◉●••, 14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-20 17:22:58 ✞ ቸርነትህ ነው

ቸርነትህ ነው ያደረሰኝ እስከ ዛሬ
ቸርነትህ ነው የጠበቀኝ እስከ ዛሬ
ላመስግንህ የኔ ጌታ በዝማሬ /2/

መክሊቱን ቀብሬ ባሳዝንህ
መብራቴንም ይዤ ባልጠብቅህ
በታላቅ ይቅርታህ እንዳትረሳኝ
በፍቅርህ ጎብኝተህ ከሞት አውጣኝ
ከቤትህ እርቄ መች ጠገብኩኝ
በርሃብ በእርዛት ተቸገርኩኝ
አምናለሁ አምላኬ እንድትምረኝ
ለይቅርታህ መጣሁ ተቀበለኝ

አዝ______

አንዳች እንደሌለኝ አውቀዋለሁ
ባንተ ቸርነት ግን እመካለሁ
የከበደው ሸክሜ ይቀለኛል
ይቅርታህ ለባሪያህ ይደርሰኛል
በመቅደስህ ቆሜ ለመዘመር
ስራህን ለትውልድ ለመመስከር
እኔ ማነኝ ብዬ አስባለሁ
አምላክ ቸርነትህን አደንቃለሁ
በሰው እጅ መመካት አቁሚያለሁ

አዝ______

እረዳቴ አንተ ነህ አውቂያለሁ
አንተ ከጠበቅከኝ በሕይወቴ
ቅጥሬ አይደፈርም መድሃኒቴ
የእኔን ስራ ተወው ተግባሬን
የመስቀሉን ነገር መርሳቴን
አዚሜን አንስተህ አንተን ልይህ
ኢየሱስ ክርስቶስ አምላኬ ነህ

አዝ______

ቸርነትህ ነው የጠበቀኝ እስከ ዛሬ
ላመስግንህ የኔ ጌታ በዝማሬ /2/

                   መዝሙር
           ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

  ╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╮
   ✥ @mezmurochh    ✥
   ✥ @mezmurochh    ✥
   ✥ @mezmurochh    ✥
   ╰══•❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
18.7K views••●◉ Estifanos ◉●••, 14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-10 13:28:50
ቅዱስ ዑራኤል መልአክ

╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥  @teksochina_meslochi ✥
  ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
26.3K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-10 13:28:34 ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

መዝሙረ ዳዊት

✧ የሲሎንዲስ ጥበብ ✧

✥ መዝሙረ ዳዊት / በ ቴሌግራም/ ✥

|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
@mezmurochh
@mezmurochh
@mezmurochh
|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
20.4K views••●◉ Estifanos ◉●••, 10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-10 13:28:24 ✞ ​​የሲሎንዲስ ጥበብ

የሲሎንዲስ ጥበብ እወድሻለሁ
የናሆም መድሐኒት እወድሻለሁ
ማርያም አከብርሻለሁ
ማርያም እወድሻለሁ/፪/

አዝ____

ተጨንቄአለሁ ልንገርሽ
ምሥጥረኛዬ እናቴ ነሽ
ሠው የአልሠማውን ብርቱ ምሥጢር
ድንግል ሆይ ለአንቺ ለአማክር

ለቁሥለኛውም መድሐኒቱ
ለአዳም ዘር ሁሉ ነሽ ሕይወቱ
መፍትሔ አለ በእጅሽ
ተንበርክኬ ልማጸንሽ

አዝ____

ሳልናገረው ይገባሻል
የውሥጤ ሁሉ ይታይሻል
ድርሽ እናቴ ተረጅኝ
ያለ አንቺ ለእኔ ማን አለኝ

ደሥታዬ ደሥታ የሚሆነው
በሐዘኔም የምጽናናው
አንቺ ከእኔ ጋር ስለ ሆንሽ
ተጽናንቻለሁ በሥምሽ

አዝ____

ወንድሞቼ እንኳን ቢሸጡኝ
ሠው ሁሉ ጠላት ቢሆነኝ
በእመ አምላክ ሐይል ከብሬአለሁ
በጠላት ላይ ሠልጥኛለሁ

የረሱኝ ሁሉ የአስቡኛል
የተጣሉኝም የአከብሩኛል
አንቺ አንግሠሽኝ አልወድቅም
እቆማለሁኝ ዘለዓለም

አዝ____

መንገዴ ረዝሞ ደክሜብሽ
መከራው በዝቶ ታምሜብሽ
ወድቄ ሳዝን ድረሽልኝ
ለባርያሽ ሐይሉን እንድትሠጪኝ

ፍቅርሽ በውስጤ ተንሠራፋ
በእናትነትሽ ልቤ ሠፋ
የሚለያየን ማንም የለም
ማርያም ልበልሽ ለዘለዓለም

                  መዝሙር
           ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

   ╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
   ✥     @mezmurochh     ✥
   ✥     @mezmurochh     ✥
   ✥     @mezmurochh     ✥
   ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
19.4K views••●◉ Estifanos ◉●••, 10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-02 09:01:43 ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

  መዝሙረ ዳዊት

       ✧ በሰባረ አፅሙ ✧

  ✥ መዝሙረ ዳዊት / በ ቴሌግራም/ ✥

              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
           @mezmurochh    
           @mezmurochh    
           @mezmurochh    
              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
27.3K views••●◉ Estifanos ◉●••, 06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-02 09:01:33 ✞ በስባረ አፅሙ

በስባረ አፅሙ በገድለ ድካሙ 
በፀናበት በአስቦ ገዳሙ 
ስድስት ክንፍ አገኘ  
ተክለሃይማኖት ምድራዊ መልዐክ ተሰኘ 
 
ትናገር ደብረ አስቦ የተጋደለባት  
ተክልዬ በአንድ እግሩ ቆሞ የፀለየባት 
በመላዕክት ከተማ ህብረት የፈጠረ 
ከካህናተ ሰማይ መንበሩን ያጠነ 
 
አዝ___
 
ቅዳሴ ቀድሷል ሚካኤል ተራድቶት 
ወንጌልን መስርቷል በፅላልሽ ዳሞት 
ተክለሃይማኖት ፃድቁ አዲስ ሐዋርያ 
ሞገሷ ነህ አንተ ለኢትዮጵያ 
 
አዝ___
 
የመንፈስ ልጆችህ አእላፍ ሆነዋል 
በፀሎትህ ታምነው ቤትህን ሞልተዋል 
የላመ የጣመ መና በሌለበት 
ዳቤው ንፍሮው ውሃው ውበት 
 
አዝ___
 
እፁብ ነው ድንቅ ነው የተሰጠህ ፀጋ 
ቋጠሮ ቢፈታ ከአንተ የተጠጋ 
የፃድቅ ሰው ፀሎት ምልጃው ይፈውሳል 
ተክልዬን ያመነ ኧረ ምን ይሆናል

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

    ╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
    ✥       @mezmurochh    ✥
    ✥       @mezmurochh    ✥
    ✥       @mezmurochh    ✥
    ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯

   ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
26.7K views••●◉ Estifanos ◉●••, 06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ