Get Mystery Box with random crypto!

መዝሙረ ዳዊት

የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmurochh — መዝሙረ ዳዊት
የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmurochh — መዝሙረ ዳዊት
የሰርጥ አድራሻ: @mezmurochh
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.22K
የሰርጥ መግለጫ

🔔🔔🔔 መዝሙረ-ዳዊት 🔔🔔🔔

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት ይቀላቀሉ
☞ @mezmurochh
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት
☞ @Mezmuredawit_bot ላይ ያገኙናል

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-15 07:10:27
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
@teksochina_meslochi
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
2.6K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 07:06:57 ቀዳም ሥዑር

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለበት ዕለት ማግሥት ያለው ቅዳሜ በተለያዩ ስያሜዎች ይጠራል:-

ቀዳም ሥዑር፡-

በዚች ዕለች ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው ቅዳሜ ትባላለች፡፡ የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ሥዑር /የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን አይመለከትም በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም ይጠናቀቃል፡፡በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡

ለምለም ቅዳሜ፡-

ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም ምእመናን እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል፡፡ በቀዳም ሥዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡

(የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ በመግባት ነው፡፡ ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን ያበሥሩበታል፡፡)

ቅዱስ ቅዳሜ፡-

ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት ነፍሳትም የዘለዓለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡

(ስምዐ ተዋሕዶ የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ዘሰሙነ ሕማማት ሚያዝያ 2004 ዓም)

የተሣተውን ፤ የተረሳው፤ የተገደፈውን፤ የነጠፈውን በቀና መንፈስ አቃንታቹ አንብቡት     
                             
ስለ ማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን

ለመቀላቀል  
      ┏━━° •❈• ° ━━┓
    
@mezmurochh
   
@mezmurochh
   
@mezmurochh
      ┗━━° •❈• ° ━━┛
2.6K views••●◉ Estifanos ◉●••, 04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 15:02:12
የስቅለት ዓርብ

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና ማቴ ፳፯፥፴፭ የስቅለት ዓርብ ይባላል።


╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
@teksochina_meslochi
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
3.6K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 15:01:31 ✥••┈┈●◉✞◉●••┈┈••✥

መዝሙረ ዳዊት

ሊቀ-መዘምራን ኪነ-ጥበብ ወልደ-ቂርቆስ

✤ ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ✤

✥ መዝሙረ ዳዊት / በ ቴሌግራም/ ✥

|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
@mezmurochh
@mezmurochh
@mezmurochh
|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

✥•┈┈●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
3.4K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 15:01:31 ✞ ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን

ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ
በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ
ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ
ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ

ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ
ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ
ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ
ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ

አዝ____

ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ
አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ
ማርና ወተትን ለሚመግበው
ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው

አዝ______

አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ
በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ
የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ
ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም

አዝ______

እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና
ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና
መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ
የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ

        መዝሙር
 ሊቀ-መዘምራን ኪነ-ጥበብ ወልደ-ቂርቆስ


   ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

      ╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
       ✥    
@mezmurochh    ✥
       ✥    
@mezmurochh    ✥
       ✥    
@mezmurochh    ✥
       ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯

      ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
3.2K views••●◉ Estifanos ◉●••, 12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 07:16:46
◦ጴጥሮስን ለታላቅ ንስሓ የቀሰቀሰው የዶሮ ጩኸት ነበር ... ‹የዶሮ ጩኸት ጴጥሮስን ለንስሓ አበቃው› የሚለው ታሪክ ከዶሮ ጩኸት አልፎ እልፍ ሰባኪያን ‹ንስሓ ግቡ› እያሉ ሲጮኹ እየሰማን ምንም ለማይመስለን ለእኛ ለልበ ደንዳኖቹ መልእክቱ ምን ይሆን? የዶሮዎቹን ጩኸት ሰምቶ በመመለስ ፈንታ የዶሮዎቹን የአጯጯህ ስልት እያወዳደርን ሰባኪያን ለምናማርጥ ለእኛ መልእክቱ በእርግጥ ምን ይሆን?

    በእርግጥ የዶሮውም እድል የሚያስቀና ነው፡፡ አንድ ጊዜ ጮኾ የወደቀውን ጴጥሮስ እንዲነሣ መቀስቀስ መቻሉ የታደለ ሰባኪ ያደርገዋል፡፡ ብዙ ጊዜ ስንጮኽ ውለን አንድ ሰው ለንስሓ ማብቃት ላልቻልን ሰባኪያን ይህ ዶሮ ምንኛ የሚያስቀና ነው? ለነገሩ በልማዱ ዶሮ ጮኾ ሌሎቹን ከማስነሣቱ በፊት እሱ ተነሥቶ ክንፉን እያርገበገበ ከፍ ከፍ ይላል፡፡ እኛ ግን ራሳችን በኃጢአት ተኝተን ሌላውን ለንስሓ ለመቀስቀስ የምንሞክር እንቅልፋም ዶሮዎች ስለሆንን በጩኸታችን የረበሽነው እንጂ የቀሰቀስነው ሰው የለም፡፡     

"ሕማማት" ከተሰኘው ባለ 528 ገጽ መጽሐፍ 2ኛ ምዕራፍ የተወሰደ
 
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
  ✥  @mezmurochh     ✥
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
3.8K views••●◉ Estifanos ◉●••, 04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 07:08:49 ❖ #አርብ #ዘጠኝ #ሰዓት(ጊዜ ተስዓቱ ስዓት)ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው በገዛ ስልጣኑ የለየበት ስዓት።  በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ። ኤሎሄ፥ ኤሎሄ፥ ላማ ሰበቅታኒ?  ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ትርጓሜውም አምላኬ፥ አምላኬ፥ ለምን ተውኸኝ? ማለት ነው፡፡ ነብስኑም በገዛ ፈቃዱ ሰጠ

✞ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስራ ሦስት ሕማማተ መስቀል ከተቀበለ በኋላ የሰው ልጅ ያጣውን ሕይወት በሞቱ ለመካስ መራራ ሞትን በፈቃዱ ተቀበለ፡፡ ነቢዩ ኢሳኢያስ ‹‹እግዚአብሔር የሁላችንን በደል በርሱ ላይ አኖረ

✞ ተጨነቀ፣ተሰቃየ፣አፉንም አልከፈተም ለመታረድም እንደሚነዳ ጠቦት በሸላቾች ፊት ዝም እንደሚል በግ እንዲሁ አፉን አልከፈተም ከኃያላን ጋር ምርኮን ይካፈላል ነፍሱንም ለሞት አሳልፎ ሰጥቷልና፡፡››ኢሳ52፤6-12/ (ማቴ.27፥50፣ ማር .15፥34፣ ዮሐ.19፥31)

❖ #አርብ #አስራ #አንድ #ሰዓት(ጊዜ ሠርክ)፡- የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ። ቅዱስ ሥጋው ከመሰቀል ወደ መቃብር የወረደበት ስዓት

✞ ከዓለት በወቀረው በአዲሱ መቃብርም አኖረው፥ በመቃብሩም ደጃፍ ታላቅ ድንጋይ አንከባሎ ሄደ። (ማቴ.27፥60)

☞ ሠርክ በሆነ ጊዜ ምዕመናን በአንድነት እግዚኦታውን በአንድ ላይ ከካህናት ጋር ካሉ በኋላ ወደቄሱ እየቀረቡ ስግደት እዲሰጣቸው ይጠይቃሉ፡፡ ቄሱም በወይራ ቅጠል እየጠበጠበ ቀን ሲሰግዱ ከዋሉት ሌላ ተጨማሪ ስግደት
ይሰጣቸዋል፡፡ ጥብጣቤው የጌታችን መስቀሉ ነው፡፡ ወይራ መሆኑ ወይራ ጹኑ እንደሆነ የጌታችን መከራ መስቀሉ ከባድ መሆኑ ለማስታወስ ነው፡፡ በስተመጨረሻ ንሴብሆ ተብሎ በሊቃውንት የአርብ ስግደት ይፈጸማል፡፡

እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም
አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ  
  ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር
        በፍስሐ ወበሰላም:: አሜን፡፡

የተሣተውን ፤ የተረሳው፤ የተገደፈውን፤ የነጠፈውን በቀና መንፈስ አቃንታቹ አንብቡት     
                             
ስለ ማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን

ለመቀላቀል  
      ┏━━° •❈• ° ━━┓
     @mezmurochh
    @mezmurochh
    @mezmurochh
      ┗━━° •❈• ° ━━┛
3.4K views••●◉ Estifanos ◉●••, 04:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 07:08:49 ዕለተ ዓርብ ስቅለተ ክርስቶስ (የድህነት ቀን)

ይህች ዕለት አዳም ኋላም ሔዋን የተፈጠሩባት፡ ከገነትም ተሰደው የወጡባት ዕለት ናት፡፡ ጌታም ቀደም የሥነ ፍጥረት ሥራውን እንደፈፀመበት። አሁንም የድህነት ሥራውን ፈጸመባት በዚች ዕለት በአምላካችን ላይ የተፈጸመው መከራ እጅግ አሰቃቂና በፍጡር ሊገለጹ የማይችሉ ናቸው፡፡

የክብርን ባለቤት ጭፍሮች ይዘው በሊቀ ካህናቱ ፊት አቀረቡት፡፡ሊቀ ካህናቱም ‹‹የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ እንደሆንክ ንገረኝ›› አለው ጌታም ‹‹ አንተ አልህ…የሰው ልጅ በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይ ደመና ሲመጣ ታያላችሁ ›› ሲለው ሊቀ ካህናቱ ‹‹ ተሳደበ›› በማለት ፊቱን ነጨ ልብሱን ቀደደ፡፡በኦሪት ሕግ እንዲህ ያደረገ ሊቀ ካህን ይሻር ትል ነበር፡፡ጌታ እንደተሸመበት እርሱ እንደተሻረበት ለማጠየቅ፡፡( ማቴ26፥57-65. ማር14፥47-54፣ ሉቃ22፥47-54፣ ዮሐ18፥1-24 )

✞ ጌታ እንደተናገረው ጴጥሮስ ደሮ እስኪ ጮህ ሦስተ ጊዜ ካደው በዚህም ጊዜ ደሮ ጮኸ፡ ጌታም ዘወር ብሎ ጴጥሮስን ተመለከተው፤ ጴጥሮስም። ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ እንዳለው የጌታ ቃል ትዝ አለው።  ጴጥሮስም ጌታ ያለውን አስታውሶ እንዲህ ሲል
አለቀሰ ‹‹ ከሁሉ ይልቅ እወደው ከሁሉ አስቀድሞ እኔ ልካደው››ብሎ ከልቡ ስላለቀሰ ንስሐውን ተቀብሎለታል፡፡ (ማቴ26፥6
9-75፣ ማር14፥67-72፣ ሉቃ22፥55-62፣ ዮሐ18፥25-27 )

❖ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጀመሪያ የተያዘባት ምሽት ሐሙስ ሦስት ስዓት ማታ  ይህንም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ መጣ፥  ከእርሱም ጋር ብዙ ሕዝብ ሰይፍና ጐመድ ይዘው ከካህናት። አለቆችና ከሕዝቡ ሽማግሎች ዘንድ መጡ። (ማቴ 26 ፥ 47 )

✿ ስለዚህ ይሁዳ ጭፍሮችንና ከካህናት አለቆች ከፈሪሳውያንም ሎሌዎችን ተቀብሎ በችቦና በፋና በጋሻ ጦርም ወደዚያ መጣ። ኢየሱስም የሚመጣበትን ሁሉ አውቆ ወጣና። ማንን ትፈልጋላችሁ አላቸው።

✿ የናዝሬቱን ኢየሱስን ብለው መለሱለት። ኢየሱስ። እኔ ነኝ አላቸው። አሳልፎ የሰጠውም ይሁዳ ደግሞ ከእነርሱ ጋር ቆሞ ነበር።
እንግዲህ። እኔ ነኝ ባላቸው ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው በምድር ወደቁ፡፡ (ዮሐ 18 ፥ 3 - 6)

❖ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የታሰረበት ጊዜ መንፈቀ ሌሊት (ሐሙስ ምሽት ስድስት ሰዓት)  እንግዲህ የሻለቃውና ጭፍሮቹ የአይሁድም ሎሌዎች ኢየሱስን። ይዘው አሰሩት፥(ዮሐ 18፥12) ❖ አስራ ሁለት ስዓት ጊዜ ነግህ (ዓርብ ጠዋት) ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በጲላጦስ። ፈት በፍርድ አደባባይ ቆመ

✞ ሲነጋም የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ሊገድሉት በኢየሱስ ላይ ተማከሩ፤  አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጴንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት  በፍጥረታት ሁሉ ላይ የሚፈርደው ሰማያዊ ንጉስ ለፍርድ አደባባይ ቆመ፡፡

✞ ጲላጦስም መርምሮ ለሞት የሚያበቃ አንዳች አጣበት ሕዝብ ግን ስቀለው ስቀለው እያሉ አብዝተው ጮኹ፡፡ የተባለችው የጲላጦስ ሚስት ክፉ እንዳያደርግበት ለባለ መልዕክት ላከች ስለእርሱ በህልሟ ስትሰቃይ አድራለችና፡፡

✞ ጲላጦስም ክርስቶስ የገሊላ ሰው መሆኑን ሲረዳ የገሊላ ገዥ ወደ ሆነው ሄሮድስ ሰደደው፡፡ጲላጦስና ሄሮድስ በግዛት እና በዳኝነት ይጣሉ ነበር አሁን ግን በጌታ ሞት ታረቁ፡፡
ሄሮድስም ገርፎ ለጲላጦስ መለሰለት፡፡( ማቴ 27፥1-14 ፤ ማር 15፥1-5 ፤ ሉቃ 23፥1-56፤ ዮሐ18 ፥28-38 )

❖ #አርብ #ሦስት #ስዓት(#ጊዜ #ሰለስቱ)፡- ጌታችን ከጲላጦስ ፊት ቀርቦ የተገረፈበት ስዓት  በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው።
ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤

✞ ሦስተኛም። ምን ነው? ያደረገውስ ክፋት ምንድር ነው? ለሞት የሚያደርሰው በደል አላገኘሁበትም፤ ስለዚህ ቀጥቼ እፈታዋለሁ አላቸው።  እነርሱ ግን እንኳን ሊራሩ " ጀርባዬን ለገራፊዎች ጕንጬንም ለጠጕር ነጪዎች ሰጠሁ፥ ፊቴንም ከውርደትና ከትፋት አልመለስሁም።"(ኢሳ 50 : 6) እንዳለ ነብዩ አርባ ጅራፍ ብቻ መግረፍ ሲኖርባቸው እየተፈራረቁ ክንዳቸው እስኪዝል ስፍር ቁጥር የሌለው ጅራፍ 6666 ጊዜ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪታይ ገረፉት፡፡ጲላጦስም ለስልጣኑ በመፍራት ንጹህ እንደሆነ እጁን በመጣጠብ እንዲሰቅሉት አሳልፎ ሰጥቷቸዋል፡፡ ( ማቴ 27 ፥ 24-26፤ ማር15፥6-15፤ ሉቃ23፥13-26፤ ዮሐ 19፥1ዮሐ 18፥28-38 )

❖ #አርብ #ስድስት #ስዓት (ጊዜ ስድስቱ ሰዓት)፡- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  እጁና እግሩን ተቸንክሮ በቀራኒወ አደባባይ የተሰቀለበት ስዓት ከዘበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥  ልብሱንም አለበሱት ሊሰቅሉትም ወሰዱት።  ከባዱን ዕፀ መስቀል መሸከሙ ከባዱን ኃጢአታችንን እንደተሸከመ የሚያጠይቀ ነው፡፡ቅ.ጴጥሮስ ‹‹ ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ ›› እንዳለ (1ጴጥ2፥22)፡፡

✞ ስምኦን የተባለ የቀሬና ሰው ነገር ፈርቶ ተሰውሮ ውሎ ነገር ተፈጽሞ ይሆናል ብሎ ሲመለስ አገኙትና አንተም የእርሱ ወገን
ነህ መስቀሉን ተሸከም ብለው አሸከሙት ምስጢሩ ግን ጌታ ከበረከተ መስቀሉ ሊያሳትፈው ስለፈለገ ነበር፡፡( ማቴ27፥27-31
፤ማር15፥16-20፤ ሉቃ23፥26-30፤ዮሐ19፥17 )

✞ ወንበዴ እንዲመስላቸው ‹‹ ደግ አደረጉ የስራውን ነው እንዲሉ›› በግራና በቀኝ ወንበዴዎችን አድርገው ሰቀሉት፡፡ ኢሳኢያስ በትንቢት‹‹ ከአመጸኞች ጋር ተቆጠረ››ያለው ተፈጸመ፡፡( አኢሳ 53፥12 )

✞ ጌታችን በፍጹም ያፈቀረውን የሰውን ልጅ ሊክስ መጥቷልና ወደ ዕጸ በለስ የገሰገሱ የአዳምን እግሮች ለመካስ እግሮቹ ተቸንክረው ዋሉ፣የበለስን ፍሬ የቀጠፉ እጆቹን ለመካስ እጆቹ ተቸንክረው ዋሉ፣ጣፋጩን የበለስን ፍሬ መቅመሱን ለመካስ መራራ ሐሞት ቀመሰ፡፡

✞ ጲላጦስ አይሁድ ተመቅኝተው ለሞት አሳልፈው እንደሰጡት ያውቅ ነበርና ‹‹የአይሁድ ንጉስ የናዝሬቱ ኢየሱስ ›› የሚል ጽሁፍ
በሦስት ቋንቋ በጽርዕ ግሪክ፣ በዕብራይስጥ፣ በሮማይስጥ በመጻፈ መስቀሉ ላይ አኖረ፡፡[ ማቴ26፥37፤ ማር15፥27፤ ሉቃ23፥38፤ ዮሐ19፥19-22 ]

☞ ቅዱስ ማርቆስ በምዕ.15፥25 ላይ ጌታችንን ‹‹በሰቀሉት ጊዜ ሦስት ሰዓት ነበር፡፡›› ይበል ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ በምዕ.19፥14 ላይ ስድስት ሰዓት መሰቀሉን ገልጦልና፡፡ በዚህ የተለያዩ አይደሉም፡፡ ነገር እንደ ዮሐንስ ነው ቅዱስ ማርቆስ ግን 3 ሰዓት ማለቱ የጌታችን የመስቀሉ ነገር የተበየነው (የተወሰነው) በ3 ሰዓት በመሆኑ ነው የተወሰነበት ሰዓት ይዞ
ከተወሰነ መሰቀሉ እንደማይቀር አውቆ 3 ሰዓት አለ፡፡

╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
  ✥  @mezmurochh     ✥
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
3.4K views••●◉ Estifanos ◉●••, 04:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 22:12:54 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

እንኳን ለጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ስቅለት አደረሳችሁ አደረስን

ሥርዓት ጸሎተ ወስግደት ዘዕለተ ዐርብ

ዐርብ ዘነግህ (፩) ሰዓት

ቅድመ ወንጌል

ተንሥኡ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ፣ ወዘኢየአምር ነበቡ ላዕሌየ፣ ተንሥኡ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ

መዝ ፴፬፥፲፩-፲፪

የሚነበቡ የወንጌል ክፍሎች

ዘማቴዎስ ፳፯፥ ፩-፲፬
ዘማርቆስ ፲፭፥ ፩ -፭
ዘሉቃስ ፳፫፥ ፩-፪
ዘዮሐንስ ፲፥ ፳፰-፵

ዐርብ ዘሠለስቱ (፫) ሰዓት

ግፍዖሙ እግዚኦ ለእለ ይገፍዑኒ፤ ጽብኦሙ እግዚኦ ለእለ ይጸብኡኒ ፤
ግፍዖሙ እግዚኦ ለእለ ይገፍዑኒ

    መዝ ፴፬፥ ፩-፪

ቅድመ ወንጌል

ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን፤ ወአኃዙኒ ማኀበሮሙ ለእኩያን፤ ዐገቱኒ ከለባት ብዙኃን

    መዝ ፳፩፥ ፲፮

ዘማቴዎስ ፳፯፥ ፲፭-፳፮
ዘማርቆስ ፲፭፥ ፲፭
ዘሉቃስ ፳፫፥፲፫-፳፭
ዘዮሐንስ ፲፱፥ ፩-፲፪

ዐርብ ዘስድስቱ (፮) ሰዓት

"ለመስቀልከ ንስግድ ኦ ሊቅነ
ወለትንሤኤከ ቅድስት ንሴብሖ ኩልነ ይእዜኒ ወዘልፈኒ"

ቅድመ ወንጌል

ቀነዉኒ እደውየ ወእገርየ።ወኆለቄ ኩሎ አዕፅምትየ።ቀነዉኒ እደውየ ወእገርየ

    መዝ ፳፩፥፮

ዘማቴዎስ ፳፯፥፳፯-፵፭
ዘማርቆስ ፲፭፥፲፮-፴፫
ዘሉቃስ  ፳፫፥፳፯-፵፬
ዘዮሐንስ ፱፥፲፫-፳፯

አምንስቲቲ ሙኪርያ አንቲ ፋሲልያሱ፤
አምንስቲቲ ሙኣግያ አንቲ ፋሲልያሱ
አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋልሲያሱ

"ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ፣ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ፣ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ "
    
     ሉቃ ፳፥፵፬

ዐርብ ዘተሰዓቱ(፱) ሰዓት

" ኦ ዘጥዕመ ሞተ በሥጋ፣ኦ ዘጥዕመ ሞተ በሥጋ በሥጋ፣ኦ ዘጥዕመ ሞተ በሥጋ

     ፩ ጴጥ ፫፥፲

ቅድመ ወንጌል

ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልዕየ፣ወአሰተዩኒ ብሒዓ ለጽምዕየ፤ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልዕየ

       መዝ ፷፰፥፳፩

ዘማቴዎስ ፳፯፥፵፯-፶
ዘማርቆስ ፲፭፥፴፬-፴፮
ዘሉቃስ  ፳፫፥፵፭-፵፮
ዘዮሐንስ ፲፱፥፳፰-፴

ዐርብ ዘሠርክ (፲፩) ሰዓት

እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ፬ (አራት  ) መቶ ጊዜ በቅብብል ይደርሳል

በቅብብል የሚደገሙ የዳዊትና የነቢያት ክፍል፦ ጸሎተ ሙሴ፣ ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ፣ ፻፴፭፤ ፻፰፤፩ ይደርሳሉ

ይ.ሕ ለይሁዳ ወልዱ ወለወልዱ ወልዱ ይደምሰስ

( ከዚህ በሃላ መሬት ላይ የተጣለውን መብራት ሁሉም ይመታዋል )

በመጨረሻም
" ንሴብሖ "የሚለው ወረብ በኀብረት ቤተክርስቲያን እየተዞር ይዘመራል

ተፈፀመ

ዘዕለተ ዐርብ

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

  መዝሙረ ዳዊት

                  ✧ ምስባክ ✧

              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
          
@mezmurochh    
          
@mezmurochh    
          
@mezmurochh    
              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

        ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
1.1K views••●◉ Estifanos ◉●••, 19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 15:43:30
ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ

╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
@teksochina_meslochi
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
2.5K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  12:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ