Get Mystery Box with random crypto!

መዝሙረ ዳዊት

የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmurochh — መዝሙረ ዳዊት
የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmurochh — መዝሙረ ዳዊት
የሰርጥ አድራሻ: @mezmurochh
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.22K
የሰርጥ መግለጫ

🔔🔔🔔 መዝሙረ-ዳዊት 🔔🔔🔔

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት ይቀላቀሉ
☞ @mezmurochh
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት
☞ @Mezmuredawit_bot ላይ ያገኙናል

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-04-13 15:41:01 ◦   ጉልባን ◦

◦ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ነው፡፡ በጸሎተ ሐሙስ በቤት ውስጥ ከሚፈጸሙ ተግባራት አንዱ ጉልባን ማዘጋጀት ነው፡፡ ጉልባን እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ሲወጡ በችኮላ መጓዛቸውን የምናስታውስበት ከእስራኤላውያን የመጣ ትውፊታዊ ሥርዓት ነው፡፡ በአገራችን ኢትዮጵያ አብዛኞቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ይህ ሥርዓት ዛሬም በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዘንድ ይከበራል፡፡

ጉልባን እስራኤላውያን ከባርነት በወጡ ጊዜ አቡክተው፣ ጋግረው መብላት አለመቻላቸውን ያስታውሰናል፡፡ በወቅቱ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መመገብ፤ ንፍሮ ቀቅለው ስንቅ መያዝ የመንገድ ተግባራቸው ነበርና፡፡ ይህን ታሪክ ለማሰብም በሰሙነ ሕማማት በተለይም በጸሎተ ሐሙስ ቂጣና ጉልባን ይዘጋጃል፡፡ በጸሎተ ሐሙስ የሚዘጋጀው ጉልባንና ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡ ይኸውም ጨው ውኃ እንደሚያስጠማ ዅሉ፣ ጌታችንም በመከራው ወቅት ውኃ መጠማቱን ለማስታወስ ነው፡፡

ምንጭ፡-
ስምዐ ተዋሕዶ (ልዩ ዕትም ዘሰሙነ ሕማማት)

ቤተክርስቲያን ከጣራዋ እስከ መሬቷ
ሁሉም ሥርዓቷ ያስተምራል፤ ባህረ
ጥበብ ቤተክርስቲያን እየተናገረች
ታስተምራለች ሳትናገር ዝም ብላም
ታስተምራለች!!
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የሲኦል ደጆች አያናውጧትም
ቤተክርስቲያን አ..ት..ታ..ደ..ስ..ም!
ፀልዩ በእንተ ሰላም ቤተክርስቲያን
አሐቲ ቅድስት ጉባኤ እንተ ሐዋርያት
ርትዕት በኅበ እግዚአብሔር!
የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም
እንማልዳለን! (መጽሐፈ ሚስጢር)
ቤተክርስቲያን....
መሰረቷ ጉልላቷ እርሱ ነው
ሙሽራዋ መስቀል ላይ የሞተው
ዛሬም ነገም ያው ነው ለዘላለም
አትንገሩን አዲስ ጌታ የለም!
•••
እንበለ_ደዌ_ወሕማም
እንበለ_ጻም_ወድካም
አመ_ከመ_ዮም_ያብጽአነ_ያብጽአክሙ


╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
✥ 
@mezmurochh   ✥
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
2.5K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  12:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 07:20:24
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
@teksochina_meslochi
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
333 views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 07:19:22 ዘንድ ፈቃድ ያገኘንበት የነፃነት አዋጅ የታወጀበትም ዕለት ነው። ክቡር ሥጋው ቅዱስ ደሙን ቀምሶ ለሐዋርያቱ የሰጠበት ፣ የሰው ልጅ ነጻነት የተሰበከበት፣ ያጣናት ዕጸ ሕይወት(ሥጋ ወደሙ) ዳግም በስምዖን ቤት በተግባር የተሰጠችበት፣ ትህትና የተሰበከበት ፣ አዳምን በግዕዛን (በነጻነት) የፈጠረ አምላክ ከሐዋርያቱ (ከሐዋርያት ጋር ሕብረታችን አንድ ስለሆነ የሐዋርያትን እጅ እጅ አድርጎ "ከእርሱም ጋር በላን ጠጣን" አባ ሕርያቆስ እንዳለ)ከእኛም ጋር የበላበት ዕለት በመሆኑ የነጻነት ሐሙስ ትባላለች። ዮሐ(15፤15) (1ኛጴጥ2፤10)

በተዋሕዶ ሞትን፣ የሞት ፍርድንም ተቀበልን። ሰይጣን ዲያብሎስ እባብን ተዋሕዶ እባብን መስሎ ገነት በመግባት አዳምና ሔዋንን አሳስቶ አስፈረደባቸው። እኛም በተዋሕዶ ብንጠፋም በተዋሕዶ ዳንን። እግዚአብሔር ሰው ሆኖ አዳነን። " በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። #ቃልም_ሥጋ_ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ። " ዮሐ፣ 1፥1 እና 14።

6 የትዕዛዝ_ሐሙስ_ይባላል

የደቀ መዛሙርቱን እግር አጥቦ እኔን ጌታና መምህር ትሉኛላችሁ፣እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገ፟ባ፟ችኋል .... ።"አድርጉ ብሎ ያዘዘበት ዕለት በመሆኑ ትዕዛዝ ሐሙስ ይባላል ። ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተግታችሁ ጸልዩ ፣ መታሰብያየን አድርጉ ብሎ ያዘዘበት ዕለትም ነውና ትዕዛዝ ሐሙስ ይባላል ።

7 አረንጓዴው_ሐሙስ_ይባላል

ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጌተሴማኒ በአተክልቱ ቦታ ረዘም ላለ ሰዓት ስለጸለዬ ያንን ሥፍራ ለምለም ስለነበረ ለማስታወስ ሲባል ዕለቱን አረንጓዴው ሐሙስ ይባላል ። አንዲም በዲያብሎስ እስራት ደርቀን የነበርን እኛን የአዳም ልጆች ክርስቶስ ከእስራት ነፃ አውጥቶን ማንነታችን ያለመለምልን በመሆኑ አረንጓደው ሐሙስ ይባላል ።

8 የአገልግሎት_ሐሙስ_ይባላል

በዚህ ስያሜ የተጠቀሰው ጌታችን በፍጹም ፍቅር ፣በፍጹም ትህትና የደቀ መዛሙርቱን እግር ዝቅ ብሎ ያጠበበት የአገልግሎትን ነገር ያስረዳበት ስለሆነ የአገልግሎት ሐሙስ ይባላል ።

"እኔ ለእናንተ እንዳደረግኹ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለኹና።እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ባሪያ ከጌታው አይበልጥም።መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም።ይህን ብታውቁ፥ብታደርጉትም ብፁዓን ናችኹ። "ዮሐ ፲፫÷፲፭_፲፯

በዚህም ስናስተውል ሲያስተምረን አሳልፎ የሚሰጠው ጠላቱን ይሁዳንስ እንኳን እራሱን ዝቅ አድርጎ በፍጹም ፍቅር አጠበው ከምሥጢር ቢለየኝ ከሞቱ ገባሁ ብሎ እንዳያመካኝ ከምሥጢር ሁሉ አላጎደለውም።

ጌታችን መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ደግነትህን የምንገልጥበት ቋንቋ የለንምና ወደ ዝምታ ውቅያኖስ ገብተን እንሸሸጋለን።

ራስህን ፈትተህ (ቆርሰህ) እንካችሁ ብሉ ትለናለህ። ከራስህ ቀድተህ እንካችሁ ጠጡ ትለናለህ። እንደሞትህ ኾነህ ምሥጢረ ቁርባንን ትመሠርታለህ። አንተው ቀድሰህ አንተው መሥዋዕት ትኾናለህ። ሞተሀል ብለን እንዳንወሰን ሕያው ነህና መሥዋዕቱን ራስህ ትቀበላለህ። ከጎንህ በፈሰሰው ውኃ ልጆችህ ታደርገናለህ። ዝቅ ብለህ እግራችንን ታጥባለህ።

በደግነትህ ታስደምመናለህ። ስላንተ ምን ብለን እንናገር ዘንድ እንችላለን? ደግነትህ ከባሕር አሸዋ ከሰማይ ከዋክብት ከቁጥራቸው እልፍ ወትእልፊት ጊዜ በላይ ይበዛል። በዚህ ላይ አልተጠየፍኸንምና እናመሰግንሀለን።

እግዚአብሔር የዓለማት ሁሉ መጋብ ገዥ አምላክ ሆኖ ሳለ ዝቅ ብሎ የሐዋርያትን እግር ማጠቡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ አባቶች መምህራን ምዕመና እኔ የበላይ ኃላፊ ነኝ መስራት አይገባኝም፣ እነርሱ ይስሩ ማለት ሳይሆን እኛ ለሌሎች አርአያ እንድንሆን ለአባቶቻችን እንዲንታዘዝ ፣ በቅንነት ቅድስት ቤተክርስቲያን እንዲናገለግል፣ በፍጹም ፍቅር ፣የዋህነት ለምዕመናን ወንጌሉ እንድደርስ እንዲናገለግል ምሳሌ ሆኖ አስተማረን።

የፋስካ_ዝግጅት_በተደረገበት_በዚህች_ዕለተ_ሐሙስ_ጌታችን_መዲኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ:-
❖ ለደቀ መዛመርቱ የማጠቃልያ ትምህርት የሰጠበት
❖ ከፋስካ ጋር ሥርዓተ ሐዲስን የመሰረተበት
❖ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ለመጨረሻ ጊዜ አብሮ የነበረበት
❖ ስለ ሁሉ ራሱን በፊቃዱ አሳልፎ በመስጠት ፍቅሩን የገለጠበት
❖ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ ፍጹም ትህትናውን የገለጠበት
❖በአስቆሮቱ ይሁዳ ተላልፎ የተሰጠበት
❖ወታደሮቹ የያዙበት ዕለት በመሆኑ ይነገራል።
( ማቴ 26÷46 ማር 14÷42_52
ሉቃ 22÷ 1 ዮሐ 18÷1_12 )

"ክርስቶስ አምላክነ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ በህማማቲሁ ........"
አምላካችን ከዕለቱ ረድኤት በረከት ይክፈለን አሜን ።

እንበለ_ደዌ_ወሕማም
እንበለ_ጻም_ወድካም
አመ_ከመ_ዮም_ያብጽአነ_ያብጽአክሙ


የተሣተውን ፤ የተረሳው፤ የተገደፈውን፤ የነጠፈውን በቀና መንፈስ አቃንታቹ አንብቡት     
                             
ስለ ማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን

ለመቀላቀል  
      ┏━━° •❈• ° ━━┓
     @mezmurochh
    @mezmurochh
    @mezmurochh
      ┗━━° •❈• ° ━━┛
339 views••●◉ Estifanos ◉●••, 04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 07:19:22 የሰሙነ_ሕማማት_አራተኛ_ዕለት

ሐሙስ

የሰሙነ ህማማት አራተኛ ዕለት
ሐሙስ:- ❖ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል
❖ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል
❖የምስጢር ቀን ይባላል
❖የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል
❖የነፃነት ሐሙስ ይባላል
❖የትዕዛዝ ሐሙስ ይባላል
❖አረንጓዴው ሐሙስ ይባላል
❖የአገልግሎት ሐሙስ ይባላል

1 ጸሎተ_ሐሙስ_ይባላል

ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚች ዕለት ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን ለመግለጥ እና ለአርአያነት እንዴት እንደምን ጸልይ አስተማረን። ጸሐፍት ፈሪሳውያን የአይሁድ ካህናት ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በደብረ ዘይት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ" አባት ሆይ ብትፈቅድ ይችህ ጽዋ ከእኔ ውሰድ የእኔ ፍቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ሲጸልይ በማደሩ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።ማቴ ፳፮፥፴፮ ሉቃ ፳፪÷፵፪

ሥርዓተ ቁርባንን በሠራልን ጊዜ (ኅብስቱንና ጽዋውን በባረከ ጊዜ) መጸለዩን ለመግለጽ (" እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ" ሉቃስ 22፥ 19)፤ በዮሐ ፲፯ ላይ ያለውን ጸሎት ስለ ጸለየ እና ዕለቱ ሥርዓተ ጸሎት የሚበዛበት ስለሆነ ጸሎተ ሐሙስ ተብሎ ይባላል።

2 ሕጽበተ_ሐሙስ_ይባለል።

በዚህ ዕለት ትሕትና የባህርይ ገንዘቡ የሆነ መምህረ ትህትና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ሆኖ ሳለ ትሑቱ ጌታ ራሱን ዝቅ አድርጎ የሐዋርያትን እግር ያጠበበት በመሆኑ ዕለቱ ሕጽበተ ሐሙስ ተብሏል፡፡
"እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና" እንዳለ (ማቴ 11፥29 ዮሐ 13፥4-15 )

ጌታችን በዚህች ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግር በፍጹም ትሕትና ዝቅ ብሎ አጥቧል።
" ወሶበ ርእየ ጴጥሮስ ዘንተ ግብረ ግሩመ ደንገጸ ወይቤ አንተኑ ተኅፅበኒ እግዚኦ ዘኅፀብኮ ለዓለም በማየ አይኅ አይቴኑ እግዚኦ ተኅጽበኒ ዘኅጸብኮ ለዓለም በማየ ዮርዳኖስ አንጻሕኮሙ እምኅጢአቶሙ አንተኑ ተኅፅበኒ እግዚኦ ዘታወፅእ ማየ እምጥማቃት ሰሊሆም በነግህ ወታየብስ ወታሠርቅ ፀሐየ ወይከውን ፍሥሓ ወፈውስ ለሕሙማን ሶበ ሆኮ መልአክከ ( ርቱዐ ሃይማኖት)
ይህም የሚያሳየው የዓለምን ሁሉ ኃጢአት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው።ይህን ለማስታወስ ዛሬም ካህናት በተለይም ሊቃነ ጳጳሳትና የደብር አስተዳዳዳሪዎች " በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝቡን ኃጢአት እጠብ እኛም የአንተን አርአያ አንዘነጋም የሌላውን እግር እናጥባለን" ሲሉ በቤተ ክርስቲያን የተገኙትን ምእመናን እግራቸውን በወይንና በወይራ ቅጠል ያጥባሉ። በዚህ ቀን ጌታ የደቀ መዛሙርቱን እግር ስለ አጠበ በአዘዘን መሠረት ዛሬ በቤተ ክርስቲያናችን መታሰቢያው ስለሚደረግ ( ርቱዐ ሃይማኖት ገጽ - 129)

" እግራቸውንም ዐጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥እንዲህም አላቸው ፦ያደረግኹላችኹን ታስተውላላችኹን እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችኹ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችኹ።እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስኾን እግራችኹን ካጠብኹ፥እናንተ ደግሞ ርስ በርሳችኹ እግራችኹን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገ፟ባ፟ችኋል .... ።" ስል ተናግሯል።{ ዮሐ 13÷12_20}
ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።

3 የምስጢር_ቀን_ይባላል።

ጥንት በዕለተ ሐሙስ ለታውፅዖ ባሕር ዘቦ መንፈሰ ሕይወት ፣ውኃ ነፍስ ያላቸውን ተንቀሳቃሾችን ታስገኝ(ዘፍ 1÷20) ባለ ጊዜ ለሥጋውያን ምግብ የሚሆኑ እንሰሳትና አዕዋፍ ተፈጥረዋል። ድኅረ ሥጋዊ የመንፈሳውያን ምግብ የሚሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለበረከት የመጣለትን ኅብስት ሥጋ መለኮት ወይኑን ደመ መለኮት አድርጎ ለዘለዓለም የማያስርብና የማያስጠማ ምግብ ሕይወት ከ፯ቱ ምስጢራት አንዱ ምሥጢረ ቊርባንን የመሠረተበት ፤ እኛ ከእርሱ ጋር እርሱ ከእኛ ጋር አንድ የምንሆንበትን ምሥጢር ከጠላት ዲያብሎስ ሰውሮ ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ቀን በመሆኑ የተሰጠ ስያሜ ነው።
" ይህ ስለእናንተ በመስቀል ላይ የምቆረሰው ሥጋዬ ነው ሂንኩና ብሉ፣ ይህ ስለ እናንተ የሚፈሰው ደሜ ነው ከእርሱ ጠጡ " በማለት ምስጢረ ቁርባንን የጀመረበት ቀን በመሆኑ የምስጢር ቀን ይባላል። ይኸውም እኛ የሰው ልጆች ሥጋውን እና ደሙን ተቀብለን ከእርሱ ጋር አንድነት እና ህብረት እንድኖረን ጥንተ ጠላት ዲያብሎስ ድል ነስተን ሰማያዊ ርስት መንግስተ ሰማያት እንድንወርስ ለማስቻል ነው ። ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱

በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴ በጉልህ ድምጽ ሳይሆን በለሆሳስ ይቀደሳል። እንደ ቃጭል በመሆን የሚያገለግለውም ጽናጽል ነው፡፡ አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ ሲመጡ ድምፃቸውን ዝግ አድርገው በለሆሳስ እየተነጋገሩ መምጣታቸውን ለማሰብ ነው፡፡ በቅዳሴውም ላይ ኑዛዜ አይደረግም፡፡ ሥርዓተ ቁርባን ግን ይፈጸምበታል፡፡ ይህም ጌታችን የሰጠውን ዘለዓለማዊ ቃል ኪዳን ለማሰብ ነው፡፡ ስለሆነም መላው ህዝቤ ክርስቲያን በሕጽበት፣የምስጢር፣ የጸሎት ቀን በተባለው በዚህ ዕለት በንስሐ ታጥበው ሥጋው ወደሙ እንድቀበሉ ቤተ ክርስቲያን በአጽንኦት ታስተምራለች።

4 የሐዲስ_ኪዳን_ሐሙስ_ይባላል።

መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።
ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ለፋስካ የሚሆንውን እራት እንድያዘጋጁ ነግራቸው ስለማዘጋጀታቸው እና የደቀ መዛሙርቱን እግር አጥቦ "እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቈርሶም ሰጣቸውና፦ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ፦ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚኾን ዐዲስ ኪዳን ነው። ብሎ የሰጠበት ቀን በመሆኑ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል ።ሉቃ ፳፪፥፲፱_፳ በማለት ጌታችን ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ዘለዓለማዊ ቃል ኪዳን በራሱ ደም የፈጸመበት ፤ እኛም የቃል ኪዳኑ ፈጻሚዎችና ጠባቂዎች መሆን እንደሚገባን የተማርንበት ዕለት በመሆኑ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።

5 የነጻነት_ሐሙስ_ይባላል።

ከአዳም ውድቀት ጀምሮ 5500 ዘመን ያህል ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም የነጻነት ሐሙስ ይባላል።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ነፃነት ስናገር "ከእንግዲህ ወዲህ ባሪያዎች አልላችኹም ባሪያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና ወዳጆች ግን ብያችኋለኹ፥ከአባቴ የሰማኹትን ሁሉ ለእናንተ አስታውቄያችኋለኹና። " ብሎ ነፃነት ያወጀበት ዕለት ስለሆነ የነጻነት ሐሙስ ይባላል።ዮሐ ፲፭÷፲፭

"..መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።" ዘፍ 2፣ 17 የተባለውን በልቶ በመብል ምክንያት የሞተው አባታችን አዳም በመብል ምክንያት ነፃ እንደሚወጣ ( "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ፤ ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና። ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።" ዮሐ 6፣ 54-56) ብሎ አባታችን አዳሜና እኛም ልጆቹ ሥጋውን በልተን ደሙንም ጠጥተን የዘላለም ሕይወትን እንቀዳጅ

@mezmurochh
  
325 views••●◉ Estifanos ◉●••, 04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 19:36:49
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
@teksochina_meslochi
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
2.1K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 19:35:34 ወለዘወሀበነ ሥጋሁ ቅዱስ ወደሞ ክቡረ

      አባ ስብሐት ለአብ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

እንኳን ለጸሎተ ሐሙስ ለሕጽበት ሐሙስ አደረሳችሁ አደረስን

ግጽው ሕጽበት ወቅዳሴ ዘሐሙስ

ዘሕጽበተ እግር

ምንባባት

፩ቆሮ ም ፲፩ ቁ ፳-፴
፩ ዮሐ ም ፫ ቁ ፲፰
ግብ.ሐዋ ም ፬ ቁ ፳፬-፴፬

ምስባክ 

ትነዝኃኒ በአሕዛብ ወእነጽሕ
ተሐጽበኒ እምበረድ ወዕፅዓዱ
ታሰምዓኒ ትፍሥሕተ ወሐሤተ

ትርጉም

በሂሶጵ ርጨኝ እነጻማለኹ
እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለው
ሐሤትንና ደስታ አስማኝ

    መዝ ፶-፮
          50  6

ወንጌል

ዮሐ ም ፲፫ ቁ ፩ -፳
            13    1  20

ዘቅዳሴ ምንባባት

፩ ቆሮ ም ፲፩ ቁ ፫-፬
፩ ዮሐ ም ፪ ቁ ፲፩-ፍ.ም
ግብ.ሐዋ ም ፲ ቁ ፴፬-፵፬

ምስባክ

ወሠራዕከ ማዕደ በቅድሜሁ
በአንጻሪሆሙ ለእለ ይሣቅዩኒ
ወአጽሐድከ በቅብእ ርእስየ

ትርጉም

በፊቴ ገበታን አዘጋጀክልኝ
በጠላቶቼ ፊት ለፊት
ራሴን በዘይት ቀባህ

    መዝ ፳፪ -፮
            22   6

ወንጌል

ማቴ ፳፮ ቁ ፳- ፴
       26    20  30

ቅዳሴ

  ዘኤጲፋንዮስ

" በዚያች ሌሊት ለዐርብ አጥቢያ ኀሙስ ማታ በወዳጁ አልዓዛር ቤት በተቀመጠ ጊዜ "
        ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ
            ም ፩ ቁ ፶፰
                1     58

እናስተውል

በሕዝቡ ተስጥኦ አቀባበል ላይ

እግዚኦ ተሣሃለነ በሚለው ፈንታ "ስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ"ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም

"ምስለ መንፈስከ "በሚለው ፈንታ 'አቡነ ዘበሰማያት' ይባላል

ጮኾ ተስጥኦ መቀበል አይገባም

ይሄ ሁሉ በጸሎተ ሐሙስ የሚኖረው ሥርዓት ነው 

ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ህይወት አለው

      ዮሐ ም ፮-፶፬
                 6   54

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

  መዝሙረ ዳዊት

                  ✧ ምስባክ ✧

              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
          
@mezmurochh    
          
@mezmurochh    
          
@mezmurochh    
              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

        ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
2.0K views••●◉ Estifanos ◉●••, 16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 12:06:29
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
@teksochina_meslochi
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
2.7K views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 12:04:31 ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

መዝሙረ ዳዊት

          ◦   ዘለሰኛ መዝሙር  ◦

  መዝሙረ ዳዊት / በ ቴሌግራም/

              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
           
@mezmurochh    
           
@mezmurochh    
           
@mezmurochh    
              |❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:

✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
2.6K views••●◉ Estifanos ◉●••, 09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 08:55:30
╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮
@teksochina_meslochi
╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯
209 views••●◉ Estifanos ◉●••, edited  05:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 08:53:53 ◦"የሰሙነ ህማማት ረቡዕ"

◦ምክረ አይሁድ ይባላል፦ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን ነውና፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡/ማቴ. 26÷1-14፣ ማር. 14÷1-2፣ ሉቃ. 22÷1-6/ የሐዲስ ኪዳን ካህናትና ምእመናን በዚሁ ዕለት በቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ ሐዋርያት ከጌታችን መያዝ በኋላ በኀዘን በፍርሐት እንደነበሩ እያሰቡ መጻሕፍትን በማንበብ በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡

◦የመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል፦ ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት /ባለሽቱዋ ማርያም/ «ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ» ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ /በራሱ/ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ረቡዕ የመዓዛ ቀን ይባላል፡፡

◦የእንባ ቀንም ይባላል፦ ማርያም እንተ እፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡/ማቴ. 26÷6-13፣ ማር. 14÷9፣ ዮሐ. 12÷8/ ኃጢአትን በማሰብ ማልቀስና ራስን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ከምታስተምረን ማርያም እንተ እፍረት እንባን ለንስሐ ሕይወት ልንጠቀምበት ይገባል፡፡


የተሣተውን ፤ የተረሳው፤ የተገደፈውን፤ የነጠፈውን በቀና መንፈስ አቃንታቹ አንብቡት     
                             
ስለ ማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን

እንበለ ደዌ ወህማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።


ለመቀላቀል  
      ┏━━° •❈• ° ━━┓
     @mezmurochh
    @mezmurochh
    @mezmurochh
      ┗━━° •❈• ° ━━┛
246 views••●◉ Estifanos ◉●••, 05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ