ተነግሮ የማያልቅ ተነግሮ የማያልቅ ነው ጸጋህ/2/ በጸሎት የተጋህ የሐይማኖት ፍሬ ተክለ-ሃይማኖት የእምነቱ ገበሬ /2/ በወንጌል ብርሀን ሕዝቡን የመራኸው የኃጢአቱን ባህር ከፍለህ ያሻገርከው ኢትዮጰያዊው ሙሴ በመስቀልህ ባርከን ፍሬ እንድናፈራ ንጹሕ ዘር አድርገን /2/ አዝ----------- ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለሃይማኖት ወንጌል ያስተማርከን ለክርስቶስ መንግስት ፀበልህ እንዲምረን ውረድ አባታችን በእጣንህ መአዛ ይፈወስ ደዌአችን /2/ አዝ----------- ለማጠን የበቃህ የሥላሴን መንበር ሰይጣን ከቶም አይደርስ በሄድክበት ሀገር ለህሙማን ሁሉ የሆንካቸው ፈውስ ጠብቀን ተክልዬ በሥጋም በነፍስ/2/ አዝ----------- በጣሙን የበዛ ትሩፋት ምግባርህ ፀሎትህን ያልተውክ ቢቆረጥ አንድ እግርህ ምዕራፈ ቅዱሳን የወንጌል ገበሬ እኛንም አድነን ከዚህ አለም አውሬ /2/ ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥ ╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮ ✥ @mezmurochh ✥ ✥ @mezmurochh ✥ ✥ @mezmurochh ✥ ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯ ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥ 3.0K views••●◉ Estifanos ◉●••, 09:56