Get Mystery Box with random crypto!

Meserete Ge'ez

የቴሌግራም ቻናል አርማ meseretegeez — Meserete Ge'ez M
የቴሌግራም ቻናል አርማ meseretegeez — Meserete Ge'ez
የሰርጥ አድራሻ: @meseretegeez
ምድቦች: ቋንቋዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 21.99K
የሰርጥ መግለጫ

“ ንዑ ንትመሀር ልሳነ ግእዝ ”
🔅ኑ የግእዝ ቋንቋ እንማር🔅
📜 የሀገራችን ቀዳማዊና ጥንታዊ ስለሆነው የግእዝ ቋንቋ መሠረታዊ ትምህርት የሚሰጥበት ቦታ ነው። እርስዎም አባቶቻችን ያቆዩልንን ቋንቋ በመማርና ለትውልድ በማስተላለፍ ኃላፊነትዎን ይወጡ።
ለጥያቄና አስተያየት
- @Geez202-
ስልክ ፦ 0977682046

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-04 08:31:30 ቋንቋ እና ሃይማኖት


በሮማውያን ዘመን ላቲን Latin (ሮማይስጢ) ሰውንና እግዚአብሔር ማግባባት የሚችል ብቸኛ ቋንቋ እንደሆነ ስለሚታሰብ ፤ ቃላዊ ሆነ ጽሑፋዊ ውዳሴ አምላክ ከላቲን ቋንቋ ውጪ ቢቀርብ "ባዶ ጩኸት" ነው ተብሎ ይታመን ነበር።

በዓረቡም ዓለምም ቢሆን የእሰልምናው ሥርዓተ አምልኮ፤ 'ሶላቱም' ሆነ ትምህርቱ በዐረብኛ ቋንቋ መቅረቡ መንፈሳዊ ዕሴት እንዳለው ስለሚታመን ቋንቋውን በማይናገሩ ሀገሮች ሳይቀር ሥራ ላይ ሲውል እንመለከታለን።

ይህ አስተሳሰብ በእኛም ሀገር ለብዙ ዘመናት ሰፍኖ መቆየቱ አያጠያይቅም። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ጸሎቱና ማኅሌቱ፣ ውዳሴውና ቅዳሴው ከግእዝ ቋንቋ ውጪ በሌላ ቋንቋ ቢቀርብ እንደዓለማዊ ጉዳይ የሚቈጠርበት ሁኔታ ነበረ።

ለምሳሌ በድሮ ጊዜ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ በቤተክርስቲያን አገልግሎት እንዳይሰጥበት አንዳንድ አባቶች ይከላከሉ እንደነበር አንድ ትውስታ ነው።

ከዚህም ሌላ በዐሥራ ዘጠኝ ኀምሳዎቹ መጨረሻ (1950's) አካባቢ ባንዳንድ የክፍለ ሀገር ከተሞች በ"ክብረ ተዋሕዶ" ወይም በ"ሃይማኖተ አበው" መዋቅር ሥር የተቋቋሙ ወጣቶች በቤተክርስቲያን ተሰባስበው የአማርኛ መዝሙሮችን መዘመር ሲጀምሩ ጊዜውን የታዘቡ ሰዎች ነበሩ።

ይህን ሁሉ የተነሣው፤ ልሳነ ግእዝ ከሃይማኖት ጋር መተሳሠሩ ያስገኘለት ፋይዳ አለ? ወይስ የለም? የሚለውን ለመመለስ ነው።


ቋንቋ ለሃይማኖት መስፋፋት፣ ሃይማኖት ለቋንቋ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ቀላል አለመሆኑን ሁሉም ሰው ይገነዘባል። የግእዝ ቋንቋ በከፍተኛ ደረጃ ወደ ብሔራዊ ቋንቋነት ሊያድግ የቻለ ከዐራተኛው ምእተ ዓመት (301 - 400) አጋማሽ ጀምሮ ባብዛኛው ጉዳያቸው ሃይማኖታዊ የሆነ ትርጉም ሥራዎች ስለተሠሩበት ነበር።

የሃይማኖትና የቋንቋ ቁርኝት ጥቅምም ድክመትም እንዳለው መረዳት እንችላለን። ለምሳሌ ዐረብኛ ቋንቋ ከሰባተኛው ምእተ ዓመት (601-700) ጀምሮ እስከ ዘመናችን ድረስ ግለቱ ሳይበርድ እምነቱን እያስፋፋ እሱም አብሮ እያደገ ነው። ላቲን እና ግእዝ ግን አልቀናቸውም።

መጽሐፍ ቅዱስ በእንግሊዝኛ እና በሌሎችም የአውሮፓ ቋንቋዎች መታተምና መሰበክ ሲጀምር ላቲን እየተዳከመ እንደመጣ ሁሉ ፤ የኛው ግእዝም አማርኛ የጽሑፍ ቋንቋና የሃይማኖት መስበኪያ እየሆነ ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ የላቲን ፈንታ ደርሶበታል።


ይቀጥላል...


◌◌◌□▢🪻መሠረተ ፡ ግእዝ🪻▢□◌◌◌
@MesereteGeez ◦ @MesereteGeez
@MGeez24
1.8K viewsedited  05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 08:45:38 Meserete Ge'ez pinned «

»
05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 17:13:03

1.1K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 23:22:06

1.8K views20:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 08:14:24
አዲስ መጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብር

መዝገበ አኀዝ ዘኢትዮጵያ

እሑድ መጋቢት ፲፯ ከቀኑ ፯ ሰዓት
በ፬ኪሎ ቅድስት ሥላሴ አዳራሽ

አዘጋጅ ፦ መጋቤ አእላፍ መ/ር በፍቃዱ መንገሻ

መጽሐፉን ለማግኘት በስልክ -
አልቦ ፱ -፺፰-አልቦ፭-፵፮ | አልቦ ፱-፵፬-አልቦ፮-፸፯-፺

        @MesereteGeez
@MesereteGeez @MesereteGeez
1.7K viewsedited  05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 17:35:54 Meserete Ge'ez pinned «

»
14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 17:06:41
እረ ልጄን አምጡልኝ!

* ጉድ ሆንኩ

#Ethiopia | ይህቺ የ2 ዓመት ጨቅላ ህፃን ሶልያና ዳንኤል ትባላለች።

የወንድማችን #Daniel Mulu ልጅ ናት።

ዛሬ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት አካባቢ ቤዛዊት በቀለ የተባለችዉ ሞግዚቷ ይዛት ተሰዉራለች:: ሞግዚቷ ከተቀጠረች 20 ቀናት ሆኗታል።

ወላጆች ለሥራ ሲወጡ ልጃቸው፣ ሞግዚቷና አያቷ በቤት ውስጥ ነበሩ።

እናትና አባት እያለቀሱ ጭንቅ ላይ ናቸው!

ንፋስ ስልክ ወረዳ 9 ፖሊስ መምሪያ - መጥፋቷን አመልክተናል።

በትራንስፖርትም ሆነ በመንገድ ላይ አጠራጣሪ ነገር ከተመለከታችሁ ደውሉልን።

+251-951-090999 - ዳንኤል
+251-947-365252 - የውብዳር

ወይንም

በአቅራቢያ ለሚገኝ ፖሊስ አሳውቁልን።

"ለልጄ ፀልዩልኝ " - እናት የውብዳር

"እረ ልጄን አምጡልኝ!" - አባት ዳንኤል
1.4K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 23:56:04

348 views20:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 15:02:20 https://youtube.com/shorts/YQAG8Prg0pw?feature=share
1.3K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 11:14:41
“ንግባእኬ ፡ ኀበ ፡ ጥንተ ፡ ነገር"

“ወደ ቀድሞ ነገር እንመለስ" በሚል ርእስ በሐመረ ብርሃን የብራና ሥራዎች ድርጅት ዐውደ ርእይ ተካሄደ ።

በዐውደ ርእዩ የብራና ሙሉ ዝግጅት እና የቅዱሳን ሥዕላት በብራና ላይ እንዴት እንደሚሳሉ የሚያሳይ ትዕይንት ሲሆን ፤ የሀገራችንን የቀድሞ የብራና ሥራ ዳግም ወደ አሁኑ ዘመን የሚመልስ ሥራ ነው ።

ሐመረ ብርሃን የተመሠረተው ከአራት ዓመታት በፊት ሲሆን ዋና ዓላማ አድርገው የተነሡት ከአባቶች የተማሩትን ጥበብ በማወቅ ለትውልድ እንዲተላለፍ ማድረግ ነው ። ወደፊትም ማኅበሩን ወደ ሥልጠና ማዕከል ለማሳደግም ትልቅ ሥራ እየሠሩ ይገኛሉ። በዚህ በአራት ዓመት ጊዜያቸውም አንድ ዓመት ከስድስተ ወር የፈጀ ውስጡ በሐረግና በሥዕላት የተዋበ መሉ የቅዳሴ መጽሐፍ በብራና አዘጋጅተዋል። በተጨማሪ የተለያዩ መጻሕፍትን እና ቅዱሳን ሥዕላትን በብራና አዘጋጅተው ለዕይታ አቅርበዋል።


የሐመረ ብርሃን አድራሻ ፦ ፒያሳ አሮጌው ፓስታ ቤት ግቢ ውስጥ


መጋቢት ፮ ቀን ፳፻፲፭ ዓመተ ምሕረት
................................
መሠረተ ፡ ግእዝ
@MesereteGeez
@MesereteGeez @MesereteGeez
1.6K views08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ