Get Mystery Box with random crypto!

🔴 ምክረ አበው MEKRA ABAW™

የቴሌግራም ቻናል አርማ mekra_abaw — 🔴 ምክረ አበው MEKRA ABAW™ ም
የቴሌግራም ቻናል አርማ mekra_abaw — 🔴 ምክረ አበው MEKRA ABAW™
የሰርጥ አድራሻ: @mekra_abaw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 17.06K
የሰርጥ መግለጫ

#አባቶችን_ጠይቅ_ይነግሩሃል
● ጠቢብ ከሰነፍ ጋር ቢጣላ፥ ሰነፍ ወይም ይቈጣል ወይም ይስቃል፥
ደምን ለማፍሰስ የሚሹ ሰዎች ፍጹሙን ሰው ይጠላሉ፥ ደግሞም የቅኑን ሰው ነፍስ ይሻሉ።
ሰነፍ ሰው ቍጣውን ሁሉ ያወጣል፤ ጠቢብ ግን በውስጡ ያስቀረዋል።
○ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕ. 29 ○
ሀሳብ ካላችሁ @habmisget

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-10 14:23:20 ላሐ ማርያም በግዕዝና በአማረኛ

መጽሐፈ ላሐ ማርያም ስለ ጌታ ሕማማተ መስቀልና እመቤታችን የተወደደ ልጂ ወዳጇን መንገላታት እያየች በኀዘን ስለአፈሰሰችው የአንብዐ ላሕ (የለቅሶን እንባን) መሪር ጽንዐ ኀዘን የሚናገር ቅዱስ አባ ሕርያቆስ የደረሰው ነው ::
ሼር ይደረግ
በvideo ለማግኘት
https://www.youtube.com/channel/UCfWtKqb7qsxjXey4kN_tykg?sub_confirmation=1
ዘወትር ምክረ አበውለማግኘት ሰማያዊውን ነክታችሁ ተቀላቀሉ ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ
@mekra_abaw
@mekra_abaw
@mekra_aba
957 views▂▃▄▅▆░ Hab mis ░▆▅▄▃▂, edited  11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 14:23:20 ድርሳነ ማሕየዊ

" መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ ። " /ማቴ ፫:፫ /
ሼር ይደረግ
በvideo ለማግኘት
https://www.youtube.com/channel/UCfWtKqb7qsxjXey4kN_tykg?sub_confirmation=1
ዘወትር ምክረ አበውለማግኘት ሰማያዊውን ነክታችሁ ተቀላቀሉ ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ
@mekra_abaw
@mekra_abaw
@mekra_aba
965 views▂▃▄▅▆░ Hab mis ░▆▅▄▃▂, edited  11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 14:23:19 በሰሙነ ሕማማት ከሚነበቡ የጸሎት መጻሕፍት በከፊል
714 views▂▃▄▅▆░ Hab mis ░▆▅▄▃▂, 11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 14:19:47 ዕለተ ሠሉስ
ዕለተ ተስዕሎ/የጥያቄ ቀን

ይህ ቀን ጌታችን በዕለተ ሰኑይ/ሰኞ/ በተናገረውና ባደረገው ላይ አይሁድ ጥያቄ ያቀረቡበት እርሱም መልስ በመስጠት ያስተማረበት ዕለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የጥያቄ ቀን ይባላል። ከዚህ በተጨማሪም በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስም ረጅም ትምህርት ስላስተማረ የትምህርት ቀንም ይባላል፡፡ ይኸውም ከሃይማኖት የራቁትን፣ ከፍቅረ እግዚአብሔር የተለዩትን አስተምሮ ማቅረብ፣ መክሮ መመለስ እንደሚገባ ሲያስተምር ነው፡፡

በዚህ ዕለት አይሁድ ጌታን የተንኮል ጥያቄ ጠይቀውታል። ጌታም አይሁድን ጥይቋቸዋል። አይሁድ የጠየቁት ጌታ ባደረገው አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ምክንያት ለጸሐፍትና ፈሪሳውያን ይኸውም ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታትን በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ?» የሚል ነበር፡፡

በዕለተ ሠሉስ(ማግሰኞ ዕለት) ፍጥረትን(ዕፅዋትን) በቃሉ የፈጠረውን አምላክ በዕለተ ሠሉስ አይሁድ ጠየቁት። ቀዳሜ ፍጥረት አዳም በዚህች ዕለት የተፈጠረቺውን ዕፀ በለስን በልቶ ከእግዚአብሔር ፊት በተሸሸገ ጊዜ " አይቴ ሀሎከ አዳም?" "አዳም ሆይ ወዴት ነህ" ብሎ አዳምን በገነት የጠየቀውን አምላክ አይሁድ በምድር ጠየቁት።

"ዘስልጣኑ ዲበ መትከፍቱ" የተባለውን አምላክ አይሁድ "ይህን በማን ስልጣን ታደርጋለህ?" አሉት።

ለሐዋርያት ስልጣነ ክህነትን የሰጠ፤ ነሥታትን የሚሾም፣ የሚሽረውን አምላክ አይሁድ ግን ስለስልጣኑ ጠየቁት። "ነገሥታት በእንቲአከ ይገድፉ ጌራ ወእጠቆሙ ይፈትሁ ሐራ(ነገሥታት ስላንተ ዘውዳቸውን ያወርዳሉ። ሰራዊቶቻቸውም ትጥቃቸውን ይፈታሉ።) የተባለለትን ጌታ አይሁድ ግን ከሮም መንግስት ሊያጋጩት የተንኮል ጥያቄ ጠየቁት። ይህን የታገሰ የጌታችኝ ትሕትና ምን ይደንቅ፣ ምን ይረቅ።

አይሁድ ይህን "ይህን በማን ስልጣን ታጀርጋለህ?" ብለው መጠየቃቸው የሚያደርጋቸውን ተግባራት ዅሉ በራሱ ሥልጣን እንዲያደርግ አጥተውት አልነበረም፤ ልቡናቸው በክፋትና በጥርጥር ስለ ተሞላ እንዲሁም ጌታችን ሲያደርጋቸው የነበሩ ተአምራትና ድንቅ ድንቅ ሥራዎች የካህናት አለቆችን ስላስቀኗቸው ጌታችንን ከሮማ መንግሥት ባለ ሥልጣናት ጋር ለማጋጨት የቀየሱት ስልት ነበር። ጌታ ይህንን በራሴ ስልጣን አደርጋለሁ ብሏቸው ቢሆን ገበያ መፍታት፣ ነጋድያንን ማባረር የመንግስት ድርሻ ነው። ይሄስ በሮማ መንግሥት ላይ የተነሳ ነው ብለው ለመክሰስ ነበር አላማቸው።

"እግዚአብሔርሰ ልበ ይሬኢ/እግዚአብሔርስ ልብን(የልብን ሐሳብ) ያያል" እንዲል እግዚአብሔር ወልድ የተባለ ማዕምረ ኅቡዓት የሆነ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጸሐፍት፣ ፈሪሳውያንን የልባቸውን ሐሳብ እውቆ እንዲህ ብሏቸዋል።


"እኔ ደግሞ አንዲት ነገር እጠይቃችኋለሁ፤ እናንተም ያችን ብትነግሩኝ እኔ ደግሞ እነዚህን በምን ሥልጣን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ" ብሎ አንዲት ጥያቄ ጣየቃቸው። "የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይን ወይስ ከሰው?" አላቸው። እነርሱም እርስ በርሳቸው ሲነጋገሩ። ከሰማይ ብንል። እንኪያስ ስለ ምን አላመናችሁበትም? ይለናል፤ ከሰው ግን ብንል፥ ዮሐንስን ሁሉም እንደ ነቢይ ያዩታልና ሕዝቡን እንፈራለን አሉ።
ለኢየሱስም መልሰው። አናውቅም አሉት። እርሱም ደግሞ። እኔም በምን ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ አልነግራችሁም አላቸው።" ማቴ 21 ÷ 24-27
ጌታም እንዲህ ብሎ ከመለሰላቸው በኋላ አንድ ምሳሌ ነገራቸው ቅዱስ ማቴዎስ እንዲህ ይተርከዋል።

----------
28፤ ነገር ግን ምን ይመስላችኋል? አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት፤ ወደ አንደኛው ቀርቦ። ልጄ ሆይ፥ ዛሬ ሂድና በወይኔ አትክልት ሥራ አለው።

29፤ እርሱም መልሶ። አልወድም አለ፤ ኋላ ግን ተጸጸተና ሄደ።

30፤ ወደ ሁለተኛውም ቀርቦ እንዲሁ አለው እርሱም መልሶ። እሺ ጌታዬ አለ፤ ነገር ግን አልሄደም።

31፤ ከሁለቱ የአባቱን ፈቃድ ያደረገ ማን ነው? ፊተኛው አሉት። ኢየሱስ እንዲህ አላቸው። እውነት እላችኋለሁ፥ ቀራጮችና ጋለሞቶች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በመግባት ይቀድሙአችኋል።

32፤ ዮሐንስ በጽድቅ መንገድ መጥቶላችሁ ነበርና፥ አላመናችሁበትም፤ ቀራጮችና ጋለሞቶች ግን አመኑበት፤ እናንተም ይህን አይታችሁ ታምኑበት ዘንድ በኋላ ንስሐ አልገባችሁም።"

ከላይ ጌታ ለአይሁድ የነገራቸውን ምሳሌ ሊቃወንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ተርጉመውታል። ታላቅ ልጅ የተባሉት ጸሐፍት ፈሪሳውያን ናቸው። ታናሽ ልጅ የተባሉት ደግሞ ኃጥአን መጸብሐን ናቸው። ታላቁ ልጅ እሄዳለሁ ብሎ እንደቀረ ጸሐፍት ፈሪሳውያንም ኦሪትን ተቀብለው በወንጌሉ ሳያምኑ ቀርተዋልና። ታናሹ ልጅ ደግሞ አልሄድም ብሎ እንደሄደ ኃጥአን መጸብሐንም ሕጉን ካፈረሱ በኋላ በወንጌል አምነዋልና።

እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር ለብርሃነ ትንሣኤሁ በፍስሐ ወበሰላም።
ምክረ አበው
በቴሌግራም
@mekra_abaw
በዩቲዩብ ማግኘት ለምትፈልጉ
https://www.youtube.com/channel/UCfWtKqb7qsxjXey4kN_tykg?sub_confirmation=1
827 views▂▃▄▅▆░ Hab mis ░▆▅▄▃▂, 11:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 14:18:13 ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ በሰሙነ ሕማማት ሰኞ የተሰጠ ትምህርት

ርግመተ በለስ
584 views▂▃▄▅▆░ Hab mis ░▆▅▄▃▂, 11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 14:18:13 የሰሙነ_ሕማማት_ሰኞ

መርገመ_በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው

ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግሥቱም ከቢታኒያ ሲመጡ ተራበ፡፡ (ማር.11፤11-12) ቅጠል ያላት በለስ ከሩቅ አይቶ ወደ በለሲቱ ቀረበ፤ ነገር ግን ከቅጠል በቀር አንዳች ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ከአሁን ጀምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ረገማት። በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ናት፤ ፍሬ የተባለች ሃይማኖትና ምግባር ናት፤ ከእስራኤል ፍቅርን፤ ሃይማኖትን፤ ምግባርን ፈለገ አላገኘም፤ እስራኤል (ሕዝበ እግዚአብሔር) መባልን እንጂ፤ ደግ ሰው አይገኝብሽ ብሎ ረገማት፤ በመርገሙ ምክንያት እርሱ ከለያቸው በስተቀር ደግ ሰው ጠፋባት፡፡

በለስ ኦሪት ናት፤ ኦሪትን በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛት ኦሪትና ነቢያትን ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ በማለት ፈጸማት፤ ሕገ ኦሪትን ከመፈጸም በቀር በእርሷ ድኅነት አላደረገባትምና፤ ፍሬ በአንቺ አይሁን አላት፤ ደኅነት በአንቺ አይደረግብሽ ብሏታልና እንደመድረቅ ፈጥና አለፈች፡፡

በለስ ኃጢአት ናት፤ የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነች ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አገኛት፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል፤ ቆይቶ ግን ይመራል፤ ኃጢአትም ሲሰሩት ደስ ደስ ያሰኛል፤ ኋላ ግን ያሳዝናል፤ ወደ እርሷም ሄዶ ማለትም ከኃጥአን ጋር ዋለ፤ ኃጥእ ከመባል በቀር በአንደበቱ ሐሰት፤ በሰውነቱ ክፋት እንዳልተገኘበት ለማመልከት ፍሬ አላገኘባትም አለ፤ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም፤ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ለማለት ነው፤ ስትረገም ፈጥና መድረቋም፣ በአዳም ምክንያት ያገኘችን ዕዳ በደል በእርሱ ካሣነት እንደጠፋችልን ለመግለጽ ነው፡፡

አንጽሆተ_ቤተ_መቅደስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፦

ጌታችን በለስን ከረገማት በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ፤ ቤተ መቅደስ፣ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተ ምስያጥ (የንግድ ቤት) ሆኖ ቢያገኘው ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፤ እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት ብሎ የሚሸጡበትን ሁሉ ገለበጠባቸው፤ ገርፎም አስወጣቸው፤ ይህም የሚያሳየው ማደሪያው ቤቱ የነበርን የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታችንን ሁሉ እንዳራቀልን የሚገልጽ ነው፡፡

በዚህ በሰሙነ ሕማማት ካህናትና ምእመናን በቤተክርስቲያን ተገኝተው ወዛቸው ጠብ እስኪል ድረስ በነግህ፤ በሠለስተ፣ በስድስቱ ሰዓት፤ በተሰዓቱ ሰዓትና በሠርክ መላልሰው ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ፤ በተለይም ካህናት በማንኛውም አገልግሎት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፤ ምክንያቱም የደረሰብን መከራ ኀዘኑን እና 5ሺ ከ5መቶ ዘመን የሰው ልጅ በጨለማ ይኖር እንደነበረ ለማዘከር ነው፡፡
664 views▂▃▄▅▆░ Hab mis ░▆▅▄▃▂, 11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 14:17:40 በዚህ ሰሞን በምንሰግድበት ጊዜ የምጠራቸው ቃላት

“ ናይናን ፤ እብኖዲ ፤ ታኦስ ፣ ማስያስ ፤ ትስቡጣ፣ አምነስቲቲ ፣ ሙኪርያቱ፣ ሙዓግያ ፣ሙዳሱጣ "


እኒህም ቃላት ከዕለተ ሰኞ የሕማማት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ እስከ ዕለተ ዓርብ ድረስ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሲነበብ በሚሰነብተው ግብረ ሕማማት በተባለው ነገረ ሕማማቱን መዝግቦ ካስቀመጠው ታላቅ የቤተክርስቲያን መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው የሚገኙና ከመጀመሪያ ጊዜ ጀምሮ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ እንደወረደ ሳይለወጡ ተጽፈው የምናገኛቸው የዕብራይስጥ፣ የቅብጥና የግሪክ ቃላት ናቸው።

•••
ናይናን

ናይናን የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም በግዕዙ “መሐረነ” በአማርኛው “ማረን” ማለት ነው፡፡

•••
እብኖዲ

እብኖዲ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም “አምላክ” ማለት ነው፡፡ “እብኖዲ ናይናን” ሲልም “አምላክ ሆይ ማረን” ማለቱ ነው

ታኦስ

ታኦስ የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም “ ጌታ፣ አምላክ” ማለት ነው፡፡ “ታኦስ ናይናን” ማለትም በአማርኛ ትርጉሙ “ጌታ ሆይ ማረን” ማለት ነው፡፡

ማስያስ

ማስያስ ማለትም የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙም በእነርሱ ቃል “ መሲሕ” ማለት ነው፡፡ “ማስያስ ናይናን” ሲልም ” መሲሕ ሆይ ማረን” ማለት ነው።

ትስቡጣ

“ዴስፓታ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም “ደግ ገዥ” ማለት ነው።

አምነስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ- አቤቱ
በመንግሥትህ አስበኝ»ማለት ነው፡፡

አምንስቲቲ ሙዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን.«ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ - ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው።

አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡

•••
በአቅራቢያችን ቤተክርስቲያን ባይኖርም ሰዓት እየጠበቅን እንዲህ እያልን የጌታን ሕማሙን እያሰብን አቅማችን በፈቀደ መጠን ባለንበት ስፍራ እንዲህ እያልን እንስገድ።
•••

•ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን
•ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን #እብኖዲ #ናይን ኪርዬ ኤለይሶን
•ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን #ታኦስ ናይን ኪርዬ ኤለይሶን
•ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን #ማስያስ ናይን ኪርዬ ኤለይሶን
•ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን #ኢየሱስ ናይን ኪርዬ ኤለይሶን
•ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን #ክርስቶስ ናይን ኪርዬ ኤለይሶን
•ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን #አማኑኤል ናይን ኪርያ ላይሶን
•ኪርዬ ኤለይሶን ኪርዬ ኤለይሶን #ትስቡጣ ናይን ኪርዬ ኤለይሶን

•••

እንበለ ደዌ ወሕማም
እንበለ ጻማ ወድካም
አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ
እግዚአብሔር በሰላም
።
ፋሲል ግቢ ጉባዔ
@fasil_gibi_gubae_official

መልእክት ወይም አስተያየትና ጥያቄ ካሎት @Fasil_gibi_gubae_bot ላይ ላኩልን።
https://t.me/fasil_gibi_gubae_official
626 views▂▃▄▅▆░ Hab mis ░▆▅▄▃▂, 11:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 13:43:37 ምክረ አበው MEKRA ABAW pinned «በሕማማት የማይፈጸሙ ተግበራት እና ሥርዓቱ ሼር በማድረግ ያድርሱ መስቀል መሳለም የፍትሐት ጸሎት ታቦት ማውጣት ከጸሎተ ሐሙስ በስተቀር ቅዳሴ መቀደስ መሳሳም ዕልልታና ጭብጨባ ሥርዓተ ማኅሌትና ከበሮ ዝማሬ ታቦት ማውጣት የኑዛዜ ጸሎት በሰሙነ ሕማማት በሌሊት የጸሎትና የስግደት ሥርዓት ሌሊት ከስድስት ሰዓት ጀምሮ ካህናትና ምዕመናን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገቡ መጀመርያ የራሳቸው…»
10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 13:18:01 በሕማማት የማይፈጸሙ ተግበራት እና ሥርዓቱ
ሼር በማድረግ ያድርሱ
መስቀል መሳለም
የፍትሐት ጸሎት
ታቦት ማውጣት
ከጸሎተ ሐሙስ በስተቀር ቅዳሴ መቀደስ
መሳሳም
ዕልልታና ጭብጨባ
ሥርዓተ ማኅሌትና ከበሮ
ዝማሬ
ታቦት ማውጣት
የኑዛዜ ጸሎት

በሰሙነ ሕማማት በሌሊት የጸሎትና የስግደት ሥርዓት
ሌሊት ከስድስት ሰዓት ጀምሮ ካህናትና ምዕመናን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገቡ መጀመርያ የራሳቸው ጸሎት ያደርሳሉ
ዲያቆኑ ሦስት ጊዜ እየዞረ ቃጭል ያሰማል
ይህም የሁሉም ዕለታት የጸሎት መጀመርያ ምልክት ነው
ከዚህ በኋላ በጋራ ሆነው ጸሎቱን ይጀምሩ
ካህኑ የአስርቆት ጸሎት ካደረሰ በኋላ
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐኒ ያብጽሕክሙ አመ ከመ ዮም ብሎ አቡነ ዘበሰማያት ይሰጣል ከዚህ ቀጥለው ሰላም ለኪ ብለው ውዳሴ ማርያም ከአንቀጸ ብርሃን ጋር ይድገሙ
መልክዓ መልክዓ ማርያምና መልክዓ ኢየሱስ አይደገምም
ካህኑ ከውዳሴ ማርያም በኋላ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐኒ ያብጽሕክሙ አመ ከመ ዮም ብሎ አቡነ ዘበሰማያት ይሰጣል

አቡነ ዘበሰማያት ከተሰጠ በኋላ በመሪ እየቀደመ በተመሪ እየተከተለ
ለከ ኃይል ይላሉ መሪና ተመሪ በግራና በቀኝ እየተቀያየሩ ያደርሳሉ
የለከ ኃይል ጸሎትና ስግደት ካለቀ በኋላ ምንባባት ይነበባሉ
ምንባባቱ ካለቁ በኋላ ምንተኑ አአስየኪ እሴተ ይባልና በሰላመ ገብርኤል መልአክን ሃሌ ሉያ ለአብንና ናሁ አግብርትኪ ከተባለ በኋላ
በአራራይ እንደ ሥርዓቱ መቅድመ ተአምርንና ተአምረ ማርያምን ተአምረ ኢየሱስስን ያንብቡ

ከተአምረ ኢየሱስ በኋላ ዲያቆኑ ምስባክ ይላል ቀጥሎ ካህኑ ወንጌል ያነባል ቀጥሎ ድኅረ ወንጌል ቀጥሎ ጸልዩ በእንተ ጽንዓ ዛቲ መካን ይላል

በመሪ በኩል አያይዘው ኪርያ ላይሶን ጸሎትና ስግደት እንደ ሥርዓቱ ይደርሳል ቀጥሎ የሰዓቱ መልክዓ ሕማማት ይደርሳል

ወንጌል ያነበበ ካህን ድምፁን አሰምቶ አርባ አንድ ጊዜ ኪርያላይሶን እንበል ይላል

ዲያቆኑ በዘማ ማኅዘኒ በወርድ ንባብ ሑሩ በሰላም ውስተ አቢያቲክሙ ንዑ ወተጋብኡ በጊዜ...........ሰዓተ ሌሊት(ሰዓተ መዓልት) ለጸሎት ብሎ ያውጃል
ይህ የሙሉ ሳምንት ሥርዓት ነው

በሰሙነ ሕማማት ዘነግህ
የጸሎትና የስግደት ሥርዓት
ጧት በአንድ ሰዓት ካህናትና ሕዝበ ክርስቲያን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገቡ መጀመርያ እንደ ተለመደው ደወል ያሰማል ዲያቆኑ ቃጭሉን እያሰማ ሦስት ጊዜ ይዞራል
ካህኑ አሥርቆት ያደርሳል ከዛ ቀጥሎ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐኒ ያብጽሕክሙ አመ ከመ ዮም እግዚአብሔር በሰላም ብሎ አቡነ ዘበሰማያት ከሰጠ በኋላ ወዳሴ ማርያም አንቀጸ ብርሃን ይደረሳል ካህኑ አቡነ ዘበሰማያት ከሰጠ በኋላ

ኦሪት ካለ መሪ አቡን ይመራል ኦሪት ከሌለ ውዳሴ ማርያም እንደ ጸለየ አያይዘው 12 ጊዜ ለከ ኃይል ይባላል በመሪ እየቀደ በተመሪ እየተከተሉ ከዘለቁ በኋላ

በመሪ ወገን ኦሪት ያንብቡ ቀጥሎ መጻሕፍተ ነቢያት ይነበባሉ ለሰዓቱ የተሰሩ ምንባባት ሁሉ ከተነበቡ በኋላ ካህኑ ምንተኑ ብሎ ስምዑ እነግረክሙ ብሎ አንድ ተአምር ያንብብ ከተአምረ ማርያም በኋላ በነግህ ብቻ ሁሉምተአምራት ይነበባሉ

ከዚህ ቀጥሎ ምስባክ ይሰበካል
ካህኑ ወንጌል ያነባል ቀጥሎ ድህረ ወንጌል ቀጥሎ በእንተ ጽንዓ ዛቲ መካን ከተነበበ በኋላ
በመሪ ክርሰቶስ አምላክነ ዘመጽ ወሐመ በእንቲአነ ወበሕማማቲሁ ቤዘወነ ይላሉ
በተመሪ ንሰብሖ ወናልዕል ስሞ ህቡረ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በሐማማተ ዚአሁ

ቀጥሎ ኪርያ ላይሶን ይባላል
ኪርያ ላይሶን ኪርያላይሶን እብኖዲ ናይን ኪርያ ላይሶን
ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ታዖስ ናይን ኪርያ ላይሶን
ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ትሱጣስ ናይን ኪርያ ላይሶን
ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ማስያስ ናይን ኪርያ ላይሶን
ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ኢየሱስ ናይን ኪርያ ላይሶን
ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ክርስቶስ ናይን ኪርያያ ላይሶን
ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን አማኑኤል ናይን ኪርያ ላይሶን
ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ኪርያላይሶን
በመሪ 21 ጊዜ
በተመሪ 20 ጊዜ =41 ይሆናል
እስከ ዕለተ ዓርብ ድረስ በዚህ መንገድ የየሰዓቱ ስግደትና ምንባብ ይከናወናል

በአራቱ ወንጌላት ያለው ምርሃት
በማቴዎስ ወንጌል የሚመራው
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ስምዕዎኬ ለእግዚእነ ኩልክሙ አብያተ ክርስቲያናት ከመ ዘአክበሮሙ ለኦሪት ወለነቢያት በወንጌለ መንግሥት እንዘ ይብል ክርስቶስ ወልደ ዳዊት አሜን አሜን እብለክሙ እስከ አመ የሐልፍ ሰማይ ወምድር የውጣ እንተ አሐቲ ሕርመታ ወአሐቲ ቅርፀታ ኢተሐልፍ እምኦሪት ወእምነቢያት እስከ ሶበ ኩሉ ይትገበር ወይከውን ይቤ እግዚእ ዘበእብራይስጢ ልሳን በወንጌለ ማቴዎስ ብርሃን ዘእምብርሃን

በማርቆስ ወንጌል የሚመራው
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ስምዕዎኬ ለእግዚእነ ኩልክሙ አብያተ ክርስቲያናት ከመ ዘአክበሮሙ ለኦሪት ወለነቢያተ በወንጌለ መንግሥት እንዘ ይብል ክርስቶስ ወልደ ዳዊት ኢይምሰልክሙ ዘመጻእኩ እስአሮሙ ለኦሪት ወለነቢያት ወኢ ከመ እንስቶሙ አላ ዳእሙ ዘእንበለ ከመ እፈጽሞሙ ይቤ እግዚእ በወንጌለ ሰላሙ አማኑኤል ስሙ ማርያም እሙ

በሉቃስ ወንጌል የሚመራው
ሃሌ ሉያ ይቤ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ኤንዘ ይሜሕረነ በወንጌለ ሉቃስ ወባሕቱ ይቀልል ሰማይ ወምድር ይኅልፍ እምትደቅ አሐቲ ቃል እምኦሪት

በዮሐንስ ወንጌል የሚመራው
ሃሌ ሉያ ስብሐት ለአብ ወወልድ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ በወንጌል ለዘመሐረነ በኦሪት ወበነቢያት ለዘናዘዘነ በከመ መሐረነ እግዚእነ ስብሐት ለእግዚአብሔር ከመ ናምልኮ ለዘፈጠረነ

የሰላም አምላክ ሰላሙን ያድለን

ጸልዩ በእንተ ሰላም
ስለ ሰላም እንጸልይ
ስለ ሀገራችን እንጸልይ
በጭንቅ በመከራ ስላሉት እንጸልይ
በጽኑ ሕመም ተይዘው ስላሉት እንጸልይ
ስለ ቤተ ክርስቲያን እንጸልይ
የሰላም አምላክ ሰላሙን ይስጠን

አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
ዝዋይ ገዳም -ኢትዮጵያ
02/08/2015
ሼር ይደረግ
በvideo ለማግኘት
https://www.youtube.com/channel/UCfWtKqb7qsxjXey4kN_tykg?sub_confirmation=1
ዘወትር ምክረ አበውለማግኘት ሰማያዊውን ነክታችሁ ተቀላቀሉ ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ
@mekra_abaw
@mekra_abaw
@mekra_abaw
1.0K views▂▃▄▅▆░ Hab mis ░▆▅▄▃▂, 10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 10:07:41
እነሆ ወቅቱ የአብይ ጾም የ ሕማማት ሳምንት በመሆኑ ለሳምንቱ የተመረጡ መንፈሳዊ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ይቀላቀሉ

https://t.me/+miSpxL_BU8o3MTBk
44 viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 07:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ