Get Mystery Box with random crypto!

ኢስላማዊ እውነታ

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamictrueth — ኢስላማዊ እውነታ
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamictrueth — ኢስላማዊ እውነታ
የሰርጥ አድራሻ: @islamictrueth
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.31K
የሰርጥ መግለጫ

ኢስላማዊ እውነታዎችን የምንገልፅበትና የምናብራራበት ቻላል!

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-27 18:38:54
የሐጅ ተግባራት አፈፃፀም እለት በእለት

(ክፍል–3)

የሶስተኛው እለት ተግባር
እሱም ከዙል–ሒጃ ወር አስረኛው የዒድ ቀን ነው።

ሚና ሲደርስ ወደ ጀምረተል—ዓቀባ በመሄድ "አላሁ አክበር " እያለ በማከታትል ሰባት ጠጠሮችን ይወረውራል።
ሀድይ ወይም የመቃረቢያ መስዋእት ካለው ያርዳል።
ፀጉሩን ይላጫል ወይም ያሳጥራል።

እነዚህን ተግባራት በመፈፀሙ የመጀመሪያ ደረጃ መፈታት (ተሀሉለል—አወል) ይከሰትለታል። በመሆኑም ከግብረ—ስጋ ግንኙነት ውጭ በኢህራም ላይ በመሆኑ የተነሳ ክልክል ሆነውበት የነበሩ ነገሮች ሁሉ ይፈቀዱለታል።
ወደ መካ መሄድና ጠዎፈል— ኢፋዷህ ማድረግ፦
ወደ መካ ይሄድና ጠዎፈል— ኢፋዷህን (የሐጅ ጠዎፍን) ያደርጋል። ሙተመቲዕ (በሐጅ ወራት ዑምራን ፈፅሞ በዚያው ጉዞ ሐጅን የሚያደርግ) የሆነና እንዲሁም ሙተመቲዕ ባይሆንም በመጀመሪያ የመግቢያ ጠዎፉን ሲያደርግ አሰከትሎ በሰፋና መርዎ መካከል ሰዕይ ያላደረገ ከነበረ የሐጅን ሰዕይ ያደርጋል።
በዚህ ተግባሩም ሁለተኛ ደረጃ መፈታት (ተሀሉለል አስ–ሳኒ) ይከሰታል። በመሆኑም የግብረ—ስጋ ግንኙነትን ጨምሮ ሌሎቹም በኢህራም ላይ በመሆኑ የተነሳ ክልክል ሆነውበት የነበሩበት ነገሮች ሁሉ ይፈቀዱለታል።
ወደ ሚና በመመለስ አስራ አንደኛውን ሌሊት በዚያ ያድራል።

ይቀጥላል…

ለሌሎች በማስተላለፍ የመልካም ስራ አጋር ይሁኑ… አላህ ያግራልን!

*ጣሀ አህመድ

https://t.me/tahaahmed9
761 views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 18:38:54
የሐጅ ተግባራት አፈፃፀም እለት በእለት

(ክፍል–2)

የሁለተኛው እለት ተግባር
እሱም ከዙል–ሒጃ ወር ዘጠነኛው የዓረፋ–ቀን ነው።
ፀሐይ ከወጣች በኋላ ወደ ዓረፋ ይጓዛል። የዙህርና የዓስርን ሰላቶች ሁለት ሁለት ረከዓ በማድርግ አሳጥሮ እንዲሁም አስቀድሞ በዙሁር ሰላት ወቅት ይሰግዳል። ፀሐይ ከአናት ከመዘንበሎ በፊት እዚያ ከደረሰና ከገራለት የሰላቱ እና የኹጥባው ስነ–ስርአት እሰኪጠናቀቅ ነሚራ በምትባለው አሁን መስጂድ በተሰራበት ቦታ ያርፋል።
ከሰላት በኋላ ፀሐይ እሰክትጠልቅ ያለውን ጊዜ ለዚክር እንዲሁም ወደ ቂብላ አቅጣጫ በመዞር እጆችን ወደ ላይ ከፍ አድርጎ በመዘርጋት ለሚፈፅመው የዱዓእ ስነ–ስርአት ያውለዎል።
ፀሐይ ከጠለቀች በኋላ ወደ ሙዝደሊፋ ያቀናል። መግሪብን ሶስት ዒሻን ሁለት ረከዓ አድርጎ እዚያ ሲደርሰ ይሰግዳል። ጎህ እሰከሚቀድ ድረስም ለሊቱን በዚያው ያሳልፋል።
ጎህ ከቀደደ በኋላ የፈጅር ሰላትን ይሰግዳል ከዚያ በኋላ በደንብ መንጋቱ እስኪታወቅ ድረስ ያለውን ጊዜ ለዚክር እና ዱዓእ ያውለዎል።
ከዚያም ፀሐይ ከመውጣቶ በፊት ወደ ሚና ጉዞ ይጀምራል።

ይቀጥላል…

ለሌሎች በማስተላለፍ የመልካም ስራ አጋር ይሁኑ… አላህ ያግራልን!

ጣሀ አህመድ

https://t.me/tahaahmed9
908 views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-26 11:14:13 አረፋህ ሊመን አረፈህ!

ነገ ቤት የማፅጃ ወይ መጋረጃ የማውረጃ ቀን አይደለም። የኢድ ሸመታም ሆነ የመዝናኛ እንዲሁ!

ነገ አላህ የሰማይ ባለሟሎች ላይ በአረፋ ሰዎች የሚኩራራበት፤ የሰው ልጆች ከእሳት በገፍ ነፃ የሚባሉበት ከሁሉ በላይ ዱአዎች በሙሉ ተቀባይነት የሚያገኙበት እለት ነው።

ለይለቱል ቀድር ባትታወቅ የውሙ አረፋ ትታወቃለች። በለይለቱል ቀድር መላእክት ቢወርዱ በአረፋ አላህ (እሱን በሚመጥን አወራረድ) የሚወርድበት ነው!

ነገ አላህ በጊዜ ፀጋ ላጣቀማችሁ አንድ to do list ላካፍላችሁ

ጠዋት

ከፈጅር በፊት ከለይሉ ጥቂቱን መስገድ፣ ስሁር መመገብ እና ኢስቲግፋር ማብዛት!

ከሰላት በኋላ ቀጥታ ተክቢራ መጀመር ከዛም ፀሀይ እስክትወጣ ቁርአን፣ተህሊል፣ተህሚድ በአጠቃላይ በዚክር ማሳለፍ(አዝካረ ሰባህ ሳይረሳ)

ፀሀይ ስትወጣ የፀሃይ መውጣትን ሰላት እዛው ከመስገጃችን ሳንነሳ በመከወን ከረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ሀጅ የማድረግን ምንዳ እንዲጎናጸፍ

ለቀን ኢባዳ ያግዘናል ብለን ካሰብን መጠነኛ እኝቅልፍ እንተኛ። ስንነሳ በትንሹ 4 ረክኣ ሰላተ ዱሃ እንስገድ!

ከሰአት

ከዝሁር ሰላት በኋላ ቁርዐናችንን እንቀራለን። የአረፋ ኹጥባ(ከመስጂደ ነሚራህ የሚተላለፈውን) መልእክት በጥብቅ መከታተል

ልባችንን ሊያረጥብ የሚችል መፅሐፍ ወይም ቪድዮ እየተመለከትን እራሳችንን እናርጥብ!

ከአስር በጥሎ እንዲሁ በቁርአን እና በዚክር መግሪብ 1 ሰአት አቅራቢያ እስኪቀረው ማሰለፍ!

የእለቱ ወሳኝ ሰአት ይህ ነው።

የተሰበረ የሚጠገንበት፤ የታመመ የሚፈወስበት፤ ተስፋ የቆረጠ ተስፋው ነፍስ ሚዘራበት ድንቅ ሰአት!

ዱኣ!!! ዱኣ ብቻ!

በዚህ ቀን ከእሳት ነፃ አለመባል ኪሳራ ነው። ምኞት ኖሮን ምኞታችንን ሳናሳካ መቅረት ቂልነት ነው!

ነገ አላህ አልመረጥንም እና እየተመለከታቸው ከሚኮፈስባቸው ጌታቸውን ለማላቅ በነጭ ተውበው ከአረህማን ድግስ ከሚታደሙት አልሆንም!

"አረፋ ተራራ ላይ መቆም ያልቻለ
አላህ ያሳወቀው ድንበር ላይ ይቁም

ሙዝደሊፋ ላይ ማደር ያልቻለ
በአላህ ትእዛዝ ላይ ይደር...ያቀርበዋልና!

ሚና ላይ እርዱን መከወን ያልቻለ
ምኞቱን ይረድ! ከፍ ይላልና።

ወደ ቤቱ በርቀት ምክንያት መድረስ ያልቻለ ከደም ስሩ ቅርብ ወደ ሆነው የቤቱ ጌታ ይከጅል!" ኢብኑ ረጀብ

እርቅ ይበጀናል!

Huzeyfa Sultan
1.2K views08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-26 11:12:41
1.1K views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-25 10:36:17
1.3K views07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-24 14:00:05
የሐጅ ተግባራት አፈፃፀም እለት በእለት

ይህ የሐጅን ተግባራት አፈፃፀም እለት በእለት የሚያብራራ አጭር ጽሁፍ በሸይኽ ሙሐመድ ሷሊህ አል–ዑስይሚን ተዘጋጅቶ ወደ አማርኛ ተመልሶ የተሰራጨ ነው።
በአላህ ፍቃድ የየእለቱን የሐጅ ተግባር ከዚህ ቀጥሎ ከፋፍለን እናቀርባለን:–

(ክፍል–1)

የመጀሪያው ቀን ተግባር
እሱም ከዙል–ሒጃ ወር ስምንተኛው ቀን የውመ አት–ተርዊያ በመባል የሚታወቀው ነው።
ለሐጅ ኢህራም ወይም ኒያ ማድረግ
በመካ ከተማ እና በዙሪያዎ ያለ ሰው ካለበት ቦታ ታጥቦ፣ (አካሉን) ሽቶ ተቀብቶ፣ የኢህራም ልብሱን ለብሶ እና "ለበይከ ሀጀን፤ ለበይከ አላሁመ ለበይክ፤ ኢነልሀምደ ወኒዕመተ ለከ ወልሙልክ ላ ሸሪከ ለከ" በማለት ኢህራም(ኒያ) ያደርጋል። ከዚህ ቀን በፊት መካ ያልመጣና ከሚቃት ክልል ውጪ ለሀጅ ወይም ዑምራ የሚመጣ ሰው የሚቃት ክልሉን ያለ ኢህራም(ኒያ) ማለፍ የለበትም።* *ወደ ሚና መጓዝ*
ወደ ሚና ይጓዛል እዚያም የዘጠነኛው ቀን ጸሐይ እስኪወጣ ድረስ ይቆያል። የስምንተኛውን ቀን የዙሁርን፣ የዓስርን፣ የመግሪብን እና የዒሻን እንዲሁም የዘጠነኛውን ቀን ፈጅር ሰላቶች በየወቅታቸው እና አራት አራት ረከዓ የሆኑትን የዙህር የዓስርና የዒሻእ ሰላቶች ሁለት ሁለት ረከዓ በማድረግ አሳጥሮ ይሰግዳል።

ይቀጥላል…

ለሌሎች በማስተላለፍ የመልካም ስራ አጋር ይሁኑ
አላህ ያግራልን!

ጣሀ አህመድ

https://t.me/tahaahmed9
1.6K views11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-22 11:30:43
1.7K views08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 19:33:45
2.3K views16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 17:13:39
አስሩ ወርቃማ ቀናቶች!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿مَا مِنْ أَيَّامٍ الْعَمَلُ الصَّالِحُ فِيهِنَّ أَحَبُّ إِلَى اللَّهِ مِنْ هَذِهِ الْأَيَّامِ الْعَشْرِ﴾

“በነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈፀም መልካም ስራዎች በበለጠ መልካም ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆንባቸው ቀናት የሉም።”

ቲርሚዚ ዘግበውታል: 757

ጆይን፦ https://t.me/BuhariMuslimAmharic
2.4K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 13:48:02 ነገ ሰኞ June 19/ ሰኔ 12 ወይም ማክሰኞ የዙል-ሒጃ ወር ብሎ ይጀምራል። አላህ ካላቃቸው እና ካከበራቸው አራት ወራቶች መካከል የዙልሒጃ ወር አንዱ ነው።


ከቀናቶች ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስር ቀናቶችም ያሉት በዚሁ በተከበረው የዙልሒጃ ወር ውስጥ ነው። በዚህ የዙል-ሒጃ ወር ውስጥ የመጀመሪያዎቹ ቀናት ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጭ ናቸው።


በእነዚህ ቀናቶች የሚሰራ መልካም ስራ ከሌሎቹ ቀናቶች ከሚሰሩ መልካም ስራዎች በእጥፍ ድርብ ይበልጣል። መልካም ሥራ ከዙል-ሒጃ አሥርቱ ቀናት በልጦ አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነበት ቀናት የለም።


ለዛሬ ስለ ዙል–ሒጃ አሥርቱ ቀናትና በውስጡ መሰራት ስለሚገባቸው መልካም ስራዎች እናኛለን፡-

ሁሌም ቢሆን ስለ ዲናችን ወቅቱን የጠበቀ ትኩረት ሊኖረን ይገባል። ረመዳን ሲመጣ ስለረመዳን፣ በሐጅ ወቅት ስለሐጅ ወዘተ ብናተኩርና ብንማማር በዚያ ጉዳይ የበለጠ እንድንጠቀም ያደርገናል።





እነዚህ ቀናቶች ከዱንያ ቀናት ሁሉ በላጭ ናቸው፣ ረሱላችን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- "ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጩ (የዙል-ሒጃ) አሥሩ ቀናት ናቸው”። ( ሶሒሕ አል-ጃሚዑ ሰጊር 1133)


በእነዚህ ቀናቶች የሚሰራ መልካም ስራ ከሌሎቹ ቀናቶች ከሚሰሩ መልካም ስራዎች በእጥፍ ድርብ ይበልጣል ለዚህም ረሱል (ﷺ) በእነዚህ ቀናቶች የሚሰሩ መልካም ስራዎች አላህ ዘንድ በሌሎች ቀናቶች ከሚሰሩ ስራዎች የበለጠ ተወዳጅ እንደሆነ እንድህ ሲሉ ተናግረዋል፡-


ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ማለታቸውን አስተላልፈዋል፡-

«አላህ ዘንድ መልካም ስራ ተወዳጅ የሆነበት ከእነዚህ አስር ቀናቶች የበለጠ ማንም ቀን የለም። ሶሐቦች አንቱ የአላህ መልእክተኛ ሆይ በአላህ መንገድ መታገል (ጅሃድ እንኳ) ቢሆን አሉ፣ ረሱልም (ﷺ)፡-

«በነፍሱም በገንዘቡም ጅሃድ ወጥቱ ከእርሱ በምንም ያልተመለሰ ሰው ሲቀር በአላህ መንገድ ላይ መታገል (ጅሃድ) እንኳ ቢሆን (በእነዚህ አስር ቀናቶች ከሚሰራ መልካም ስራ አይበልጥም)» አሉ። (ቡኻሪ (2/457) እና ሌሎችም ዘግበውታል)





በነዚህ በተከበሩ ቀናቶች ወንጀልን መራቅ አለብን፣ ኢብኑ ረጀብ እንድህ ይላሉ:-

«ወንጀልን ተጠንቀቁ እርሷ በሚታዘንባቸው አጋጣሜዎች መሀርታን ትከለክላለች» «ወንጀል (አላህን ማመፅ ከአላህ እዝነት) የመራቅ እና የመባረር ሰበብ ስለሆነች ተጠንቀቁ» (ለጧኢፉል መዓሪፍ (254)


በእነዚህ ቀናቶች ውስጥ ሁሉም መልካም ስራ ይወደዳል ስለዚህ ከእነዚህ መልካም ስራዎች የተገራልንን በመስራት የብዙ አጅር ባለቤት ለመሆን እንጣር። ይህ በእኛ ላይ የተዋለለን የአላህ ትልቅ ኒዕማ እንደሆነ ማወቅ እዚህ ትልቅ ኒዕማ ላይ ጤና እና እድሜ ሰጥቶን በሰላም ከደረስን ይህን ኒዕማ ሳናባክን ሌሎችን በሞት ወይ በበሽታ እንዳለፋቸው እኛንም የሚያልፍብን ቀን ሳይመጣ የተሰጠን እድል ሳያልፍ በአግባቡ እንጠቀም





በእነዚህ ቀናት ከሚሰሩ መልካም ስራዎች መካከል፡-


ሐጅና ዑምራህ፡-

ሐጅ ማድረግ በነዚህ ቀናት ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች መካከል ሐጅ ማድረግ ይገኝበታል፤ በነዚህ አስር ቀናት አቅሙ ለቻለ ሰው የሐጅ ዒባዳ ላይ ተገኝቶ በተገቢው መልኩ ከፈጸመው በአላህ ፍቃድ ክፍያው ጀነት ነው


"ዑምራህ ቀጣዩ አመት ዑምራ እስኪመጣ ድረስ (በመሃል ለተፈጸሙ ጥቃቅን ኃጢአት) ማስተሰረያ ነው፣ ትክክለኛ ሐጅ ደግሞ ከጀነት ውጪ ክፍያ የለውም”። (ቡኻሪና ሙስሊም)





ጾም፡-


የፈለገ ሙሉውን ዘጠኝ ቀን፣ ካልሆነም የቻለውን ያክል መጾም ይችላል

"መልካም ስራ ከዙል-ሒጃ አስርቱ ቀናት በልጦ አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነበት ቀናት የለም፡፡" በዚህ ሐዲሥ መሠረት ጾም "መልካም ሥራ" የተባለው ሐዲሥ ውስጥ ስለሚካተት በጾሙ የቻለውን ያክል መበርታት


በዙል-ሒጃ ወር 9ኛው ቀን፣ የዐረፋ ቀን ነው፣ አቢ ቀታዳህ እንዳሉት የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡-

"የዐረፋ ቀን ጾም የሁለት ዐመት (ያለፈውንና የሚመጣውን) ኃጢአት ያስምራል" (ከቡኻሪ በስተቀር ሁሉም የዘገበው)





አላህን ማውሳት፡-


ዚክር ማብዛት: አልሐምዱሊላ ተክቢር (አሏሁ አክበር) ተሕሊል (ላኢላሀ ኢለላህ) ተስቢሕ (ሱብሓነላህ) እና ቁርኣን መቅራትን ማብዛት። ኢባዳዉን ለማስታወስና የአላህን ስም ከፍ ለማድረግ በተለያዩ አጋጣሚዎች ድምጽን ከፍ አድርጎ እነዚህን ዚክሮች ማድረግ ይወደዳል


ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ባስተላለፉት ሐዲሥ ላይ ነቢዩ (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) እንዲህ ብለዋል፡-

"በነዚህ ቀናት ውስጥ ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢልለሏህ)፤ ተክቢር (አላሁ አክበር)፤ ተሕሚድ (አል-ሐምዱ ሊላህ) ማለትን አብዙ" (አህመድ 7/224)


ዐብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁም) ወደ ገበያ በመውጣት በተክቢራ ሲያሞቁት ሰዎቹም እነሱን ተከትለው ተክቢራ ይሉ ነበር (ኢርዋዑል-ገሊል: አልባኒይ 651)


በእነዚህ ቀናት እኔን አስታውሱባቸው ብለዋል አላህ፡-


۞ "ለነሱ የሆኑ ጥቅሞችን ይጣዱ ዘንድ፣ በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከማለዳ እንሰሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ፣ (ይመጡሃል)፤ ከርሷም ብሉ፤ ችግረኛ ድኻንም አብሉ።" ۞ ( ሱረቱል-ሐጅ 28)


"የታወቁ ቀኖች" የተባሉት እነዚሁ አሥርቱ ቀናት እንደሆኑ ሙፈሲሮች ያስረዳሉ፡፡ ታዲያ አላህን በማንኛውም ጊዜ ማውሳትና ማወደስ ከመቻሉ ጋር በነዚህ ቀኖች አወድሱት ብሎ ቀኖቹን ለይቶ መጥቀሱ የተለየ ደረጃና ክብር እንዳላቸው ይጠቁማል





ተውበት ማብዛት፡-


۞ "…ምእምናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ።" ۞ ( ሱረቱል አሕዛብ 31)


መልካም ሥራዎችን ማብዛት፡-


በኢስላም የመልካም ሥራ በሮች ብዙ ናቸው፡፡ ተቆጥረው አይዘለቁም፡፡ ከኛ የሚጠበቀው ስራው ላይ ተሳታፊ መሆን ነው፡፡ ከቤተሰብ ጀምረን እሰከ ሩቅ ሰው ድረስ አቅማችን የቻለውን ያህል በመርዳት ወደ አላህ እንቃረብ።


ኡዱሕያ፡-

በነዚህ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደ አላህ መቃረብ ነው። ኡድሂያን ለማረድ ያቀደ ሰው የዙልሂጃ ወር ከገባ ጥፍሩንና ጸጉሩን መቁረጥ የለበትም።

የኡድሑይያህ የእርድ ቀናት ከዒዱ ቀን ሶላት መጠናቀቅ ጀምሮ (የውሙ–ነሕር 10ኛው ቀን ማለት ነው) እስከ አያሙ–ተሽሪቅ የመጨረሻው ቀን (11፣ 12 እና 13ኛው ቀን ፀሀይ መግባት ድረስ) የሚቆይ ይሆናል





በዒባዳህ መጠናከር፡-


ነፍል (ትርፍ ግዴታ ያልሆኑ) ዒባዳዎችን ማብዛት ለምሳሌ ሱና ሶላቶችን ማብዛት፤ ቁርኣንን ማንበብና ማዳመጥ


ከሐራም መቆጠብ፡-

ከላይ የተጠቀሱት መልካም ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የአላህን ተውፊቅ ያላገኘ ሰው ቢያንስ ከወንጀል ይታቀብ። እሱም ትልቅ ተውፊቅ ነውና

በነዚህ ውድ ቀናቶች ከተጠቀሱት ውጪ ያሉትንም መልካም ስራዎች በሙሉ መስራት ምንዳው ላቅ ያለ ነው። ከመልካም ፈገግታ ጀምሮ በኸይር ስራ ሚዛን ላይ ሊያመዝንልንና ሊጠቅመን የሚችልን ነገር ከመተግበር ወደ ኋላ አንበል።


http://t.me/khalidzemen
1.9K views10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ