Get Mystery Box with random crypto!

ኢስላማዊ እውነታ

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamictrueth — ኢስላማዊ እውነታ
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamictrueth — ኢስላማዊ እውነታ
የሰርጥ አድራሻ: @islamictrueth
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.31K
የሰርጥ መግለጫ

ኢስላማዊ እውነታዎችን የምንገልፅበትና የምናብራራበት ቻላል!

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-03-13 10:38:26 #ረመዳን ነክ ጉዳዩች

#የመንገደኛ ፆም

ሐዲስ ①

አነስ (رضي ﷲ عنه) እንዲህ ይላል፦

﴿كُنّا نُسافِرُ مع النبيِّ ﷺ فَلَمْ يَعِبِ الصّائِمُ على المُفْطِرِ، ولا المُفْطِرُ على الصّائِمِ.﴾

“ከረሱል (ﷺ) ጋር መንገድ እንወጣ ነበር። የሚፆመው ያፈጠረውን (የማይፆመውን) አያነውርም። የማይፆመው የሚፆመውንም እንደዛው።”

ቡኻሪ ዘግበውታል: 1947

ሐዲስ ②

ጃቢር (رضي ﷲ عنه) እንዲህ ይላል፦

﴿كانَ رَسولُ اللَّهِ ﷺ في سَفَرٍ، فَرَأى زِحامًا ورَجُلًا قدْ ظُلِّلَ عليه، فَقالَ: ما هذا؟، فَقالوا: صائِمٌ، فَقالَ: ليسَ مِنَ البِرِّ الصَّوْمُ في السَّفَرِ.﴾

“ከረሱል (ﷺ) ጋር ጉዞ ላይ ነበርን።
ሰዎች ከበውት ያጠለሉለትን ሰው አይተው ይህ ምንድን ነው? ብለው ጠየቁ። ‘ፆመኛ ነው’ አሉዋቸው። ጉዞ ላይ ሆኖ መፆም መልካም አይደለም አሉ።”

ቡኻሪ ዘግበውታል: 1946

ሐዲስ ③

ከአዒሻ (رضي ﷲ عنها) ተይዞ: ቢን ዐምሪ አልሰለሚይ ለነቢዩ (ﷺ) እንዲህ አላቸው፦

﴿أأَصُومُ في السَّفَرِ؟ - وكانَ كَثِيرَ الصِّيامِ -، فَقالَ: إنْ شِئْتَ فَصُمْ، وإنْ شِئْتَ فأفْطِرْ.﴾

መንገደኛ ሆኜ እፆማለሁን? ብዙ ይፆም ነበር። ነቢዩም (ﷺ) አሉት፦ ከፈለክ ፁም። ከፈለክ ደግሞ አፍጥር።

ቡኻሪ ዘግበውታል 1943

ጆይን፦ https://t.me/BuhariMuslimAmharic
874 views07:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 10:38:25
728 views07:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 11:12:05 የድግምት ህክምና መንገዶች

ድግምትን ከተደገመበት ግለሰብ ላይ መፍታትና ማከም “አል-ኑሽራ” ተብሎ ይጠራል፡፡

ሸይኽ ሱለይማን ቢን አብደላህ ቢን መሐመድ ቢን አብድልወሀብ ከአቢ አልሰዓዳት “ተይሲሩ አል አዚዝ አል ሀሚድ” ከተባለው መፅሐፍ ላይ በመውሰድ ሲያብራሩ፦

«አል ኑሽራ ጂን የተለከፈውን ግለሰብ የማከምና ሩቃ የማድረግ ሂደት ነው፡፡ አል ኑሽራ ተብሎ የተጠራበት ምክንያት በሽታው ለውጦት የነበረውን ግለሰብ ስለሚያስወግድለት ነው» ብለዋል፡፡።ሸይኽ መሐመድ ቢን አብድልወሀብ ከኢብኑ አልቀይም እንዳወሩት “አል ኑሽረቱ” ድግምትን ከተደገመበት ግለሰብ ማላቀቅ ነው፡፡ እሱም ሁለት አይነት ነው፡፡

አንደኛው፦ ድግምት በድግምት መፍታት ይህ የሰይጣን ተግባር ነው፡፡ የሀሰን ንግግርም “አል ኑሽራ ከድግምት ነው” የሚለውና “ድግምትን ደጋሚው እንጂ ማንም አይፈታውም” የሚለው ንግግር የሚተረጐመው በዚህ ነው፡፡ ድግምት አድራጊውና ድግምት የተሰራበት ግለሰብ ሰይጣን ወደሚወደው ነገር በመቃረብ ድግምቱ ውድቅ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡ የተፈቀዱ ንባቦችን መጠበቂያዎችንና መድሃኒቶችን በመጠቀም መፍታት የተፈቀደ ነው፡፡ የመጀመሪያው አይነት በጃቢር ሀዲስ የተጠቀሰውን ትርጉም የያዘ ነው፡፡

ነብያችን ﷺ ስለ አል ኑሽራ ተጠይቀው «እርሱ የሰይጣን ተግባር ነው» ብለዋል፡፡ ይኸውም ድግምትን በድግምት መፍታት ነው። ይህ አይነቱ ድግምት ወደ ሰይጣን በመቃረብ ካልሆነ በስተቀር አይሟላም ምክያቱም ሰይጣናትና ደጋሚዎቹ እስካልታዘዟቸውና በአላህ እስካልካዱ እና በዚህ ተግባራቸው ወደ እነርሱ ካልተቃረቡ በስተቀር አይታዘዟቸውም፡፡ ስለዚህ አንድ ግለሰብ ድግምቱ እንዲፈታለት ወደ ደጋሚው ጋር ሲሄድ ለሰይጣን እንዲያርድ ወይም በማንኛውም መቃረቢያ ወደ ሰይጣን እንዲቃረብ ያዘዋል፡፡ ይህ አይነት ተግባር የተከለከለ ለመሆኑ ማንም አይጠራጠርም፡፡ ምክንያቱም በአላህ ላይ መካድና ማጋራት ነው፡፡

የአላህ መልዕክተኛ(ﷺ) እንዳሉት “እርሱ የሰይጣን ተግባር ነው” ይህም በሽታን እንጂ ሌላን አይጨምርላቸውም፡፡ ምክንያቱም ደጋሚ እርኩስ ነው እርኩስ የሆነ ደግሞ የሰውን ጉዳት እንጂ ማስተካከልን አያስብም፡፡ ደጋሚው የወንድሙን ድግምት መፍታት አይሆንለትም ምክንያቱም በወንጀል ላይ አንድ ናቸውና፡፡ ነገር ግን ግራ ሊያጋባውና ለሰይጣን ስለት የገባውን ይሞላ ዘንድ በሽታውን ረገብ ያደርግለታል፡፡ ከዚያም በድጋሚ ይመለስበታል፡፡

ሁለተኛ አይነት፡- የተፈቀደ ህክምና ሲሆን ይኸውም የተፈቀደ ሩቃ ከቁርአን፣ ከአዝካር፣ ከትክክለኛ ዘገባ ከነብያችን በተገኙ መጠበቂያዎች፣ የተፈቀዱ መድሃኒቶችን፣ የዘምዘም ውሃን የመሰለ፣ ጥቁር አዝሙድ፣ የዘይቱን ዘይት፣ የመዲና ተምር መጠቀም ይቻላል፡፡ እነዚህ መድሃኒቶች ሁሉ በትክክለኛ ዘገባ ከነብያችን(ﷺ) የተገኙ ናቸው፡፡

ድግምትን ለመከላከል የሚረዱ የመድሃኒት ዓይነቶችና የአጠቃቀማ ሁኔታ!

1) የዘምዘም ውሃን ከሲድር ጋር ከተነበበት በኃላ መታጠብ ፣ ሰባት የሲድር ቅጠል በመቀጠንስ እናቀርባለን ከዚያም በደንብ አድርገን እንፈጨዋለን ከዚያም በዘምዘም ውሃ ውስጥ እንከተዋለን፡፡ ሲድር በተደባለቀበት ውሃ ውስጥ ሩቃ ሸርዒያ (የተፈቀደ ሩቃ) እና በሲህር ዙሪያ የሚናገሩ ቁርአናዊ አንቀፆች እናነባለን፡፡ ከዚያም በሽተኛው ሶስት ጊዜ ከተጐነጨ በኃላ በየቀኑ ለሰባት ቀን ያህል ይታጠብበታል፡፡ ይህን ካደረገ በአላህ ፍቃድ ይፈወሳል፡፡ ሲህርን በመፍታትና ቋጠሮን በማስፈታት ተሞክሮ ውጤታማ የተሆነበት ነው፡፡

2) ማርና የተፈጨ ጥቁር አዝሙድ

አንድ ኪሎ ትኩስ የሆነ ማር እናዘጋጃለን፡፡ በሻይ ማንኪያ አንድ የተፈጨ ጥቁር አዝሙድ በደንብ አድርገን ከማሩ ጋር እንለውሳለን፡፡ ከዚያም የተፈቀደውን ሩቃ እና ከሲህር ጋር ተዛማጅነት ያላቸውን ቁርአናዊ አንቀፆችን እናነባለን፡፡ ከዚያም ዘውትር ጠዋት ከምግብ በፊት በሾርባ ማንኪያ አንድ እንወስዳለን፡፡ ይህ በአላህ ፍቃድ በመጠጣት ወይም በመብላት ድግምት ለተሰራበት ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡

3) የመዲና ተምር

ዘውትር ጠዋት ምግብ ከመመገብ በፊት ሰባት ፍሬ የመዲና ተምር መመገብ፡፡ አላህ በዚህ ሰበብ ድግምትም እንዳያገኘው ይጠብቀዋል፡፡ ነብያችን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዳሉት፦

«ዘውትር ጠዋት ሰባት ፍሬ የመዲና ተምርን የበላ በዛ ቀን በመነደፍና በድግምት አይጠቃም፡፡» [አህመድ ዘግበውታል]

4) የዘይቱን ዘይት

ንፁህ የዘይቱን ዘይት ማዘጋጀት ከዚያም የተፈቀደውን ሩቃ ማንበብ ከዚያም በሽተኛው ዘውትር ከመተኛቱ በፊት ሰውነቱን መቀባት። በአላህ ፍቃድ ድግምትን ለመከላከል የሚረዱ ናቸው!

አላህ እኛንም ቤተሰባችንን እንዲሁም ሙስሊሙን ዑማ ከዚህ መጥፎ በሽታ እንዲጠብቀን እንለምነዋለን!

#ሺፋእ

ሼር በማድረግ ሙስሊሙን ዑማ በብዛት እየጎዳ ያለውን የሲህር በሽታ ለመከላከል የበኩሎን አስተዋፅዖ ያበርክቱ!

https://t.me/islamictrueth
583 views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 11:12:02
525 views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 10:39:58
508 views07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 21:12:06
ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለአዲስ አበባ ሙስሊም ማህበረሰብና ለመስጂድ ጀመዓዎቸ የተላለፈ ጥሪ

ነገ እሁድ መጋቢት 3 | 2015 ከጠዋቱ 12:30 ሰዐት ጀምሮ ጉለሌ በሚገኘው የሙስሊሞች መካነ መቃብር ቅጥር ግቢየማይቀርበት ቀጠሮ ይዘናል።

ቀጠሮው ወጣት ወንዶችን ይመለከታል።

ስራው ወደጫካነት ተለውጦ የጅቦች መራቢያ፣ የሌቦች መደበቂያ፣ የሱሰኞች መነሀሪያ የሆነውን ጉለሌ መካነ መቃብርን ጫካውን በመመንጠር ምቹ የቀብር ስፍራ ማድረግ ነው።

በዚህ ትልቅ አጅር በሚያስገኘው በጉልበታችን ብቻ በሚሰራው ኸይር ስራ ላይ ወላጆች እና ሴቶች ወንድ ልጆቻችሁን እና ወንድሞቻችሁን በመላክ እና በማበረታታት የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ።

ነገ በፍፁም አይቀርም ጠዋት 12:30 ሰዐት ላይ ጉለሌ የሙስሊም መቃብር እንገናኝ።

አድራሻውን ለማታውቁ

ከፒያሳና አካባቢው ለምትመጡ:-

እንቁላል ፋብሪካ አደባባዩን አልፋችሁ ወደ ጎጃም በረንዳ በሚወስደው መንገድ በስተ ግራ በኩል

ከአለም ባንክ፣ ጦርሀይሎችና አካባበከው ለምትመጡ:- ከአውቶብስተራ ወደ ፓስተር ስትሄዱ በስተቀኝ በኩል ሁለተኛ አስፓልት ቂያስ ወደ ሀግቤስ በሚወስደው መንገድ ላይ ወደ ግራ በሚወስደው በመታጠፍ በስተቀኝ በኩል ቀብሩን ታገኙታላችሁ

ከአስኮና አካባቢው ለምትመጡ:- ከፓስተር አደባባይ እንዳለፋችሁ ኖክ ማዲያ ፊትለፊት በስተቀኝ በኩል ወደ ጨው በረንዳ ስትታጠፉ ቀብሩን በግራ በኩል ታገኙታላችሁ

ከጥቁር አንበሳና አካባቢው ለምትመጡ ደግሞ አንዋር መስጂድን አልፋችሁ በቀኝ በኩል ወደ አዲሱ ገበያ የሚወስደውን አስፓልት አልፋችሁ ወለጋ ሆቴል በሚገኝበት አስፓልት ወደቀኝ በመግባት ውሀ ልማቱ ፊት ለፊት ታገኙታላችሁ።

ለበለጠ መረጃ

0962 38 37 37
0911 11 42 42

ይደውሉ
711 views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 09:55:54
297 views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 12:23:56
433 views09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 17:33:07
405 views14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 17:49:38 ዛሬ March የሴቶች ቀን ነው አሉ የሴቶች ነፃነት በሚል ሰበብ፣ ግርማ ሞገስ ያለውን አለባበሷን ማስጣል እና በቤት እመቤትነቷና በባሏ ላይ እንድትሸፍት ማድረግ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡


ብቻ አላማቸው የሴቶችን መብት ማክበር እንዳልሆነ ከሙስሊም ሴቶች አንፃር ያላቸው ፖሊሲ በተጨባጭ አይን ላለው ሁሉ እያሳየ ነው፡፡


እርቃንነትን እስከ ጥግ እየፈቀዱ ሙስሊሟን ግን አለባበሷን ምክኒያት በማድረግ፣ ከትምህርት ገበታ፣ ከስራ ቦታ ማፈናቀሉን ተያይዘውታል፡፡





እነዚህ ናቸው እንግዲህ ስለ ሴቶች መብት የሚያቀነቅኑት፡፡ ከባህልም ከሞራልም ያፈነገጡ አለባበሶች ላይ ትንፍሽ ሳይሉ ለሙስሊሟ ሲሆን ግን በየመንገዱ ይጎነትላሉ፡፡


አልፈውም ህገ-ደንብ ያወጣሉ፡፡ ፖሊሲ ያረቃሉ፡፡ ከዚያም አያፍሩም ስለ ሴቶች መብት ይደሰኩራሉ፡፡ “የምትለብሺውን እኔ ካልመረጥኩልሽ” ከማለት በላይ ምን አፈና አለ?!!


እህቴ ሆይ! ተጠንቀቂ!! ብዙዎቹ የሴቶች “ነፃ አውጪዎች” የሰይጣን ተልእኮ አራማጅ የሆኑ የሀሰት ጥሩ ንባዎች ናቸው፡፡ እውነት ተቆርቁሮልሽ እንዳይመስልሽ፡፡





ቢሆንማ ለእርቃን እሩብ ጉዳይ መሆንን ፈቅዶ መልበስሽን ለምን ይቃወምሻል እውነት ለመብትሽ ተሟጋች ከሆነ ስትራቆቺ ገልፍጦ ስትለብሺ ለምን ደሙ ይፈላል


ለምንስ በየመንገዱ ይጎነትላል ለምንስ ከየተቋሙ ያባርራል እመኚኝ “ነፃ ውጪ” የሚለው በየጎዳናው በነፃነት በነፃ ወይም በርካሽ እንዲያገኚሽ ነው፡፡


ለሰው ልጆች አጥፊና አውዳሚ ከሚባሉት ሁለት ፈተናዎች ውስጥ አንዱ የሆነውን የስሜትን ፈተናን በሂጃብ ልጎም እንዳታስሪው እስልምና ያስተምርሽል፣ ከዚህ ፈተና መጠበቁ ዋነኛ ተጠቃሚውም ተጎጂዋም አንቺ ነሽ





አስተውይ! ልብስሽን ስለጣልሽ ነፃ አትወጭም፡፡ ነፃ መሆን ልብስ በመጣል ከሆነ ነፃ ሰዎች ማለት እብ - ዶች ናቸው፡፡ የሚጮኸው ስለ ክቡር ማንነትሽ ሳይሆን ስለ እርቃን ገላሽ ነው፡፡


ሸሪዐውን የተከተለ ኢስላማዊ አለባበስ የአማኝ ሴት መገለጫ የንጽህናሽ ማስታወቂያ ነው። እንዳትደፈሪና ክብርሽ እንዳይነካ መከላከያሽ ነው።


ሂጃብ በመልበስሽ ወንዶች እንቺን አይተው ከመፈተን ይጠበቃሉ፡፡ ኧረ እንዲያውም አይናቸውን ሰበር ለሚያደርጉ ብርቅዮዎች ብቻ ሳይሆን ላይ ታቹን ለሚያማትሩትም አደብ ታስገጂበታለሽ





በተቃራኒው የምትገላለጪ ከሆነ የፈተና የጥፋት በር በማይዘጋ መልኩ ይበረገዳል፡፡ በዘመናችን ያለውን ሁኔታ ያስተዋለ አላህ ያዘነላት ካልሆነች በስተቀር ሴት ልጅ በገዛ እራሷ ክብሯን አሽቀንጥራ ወርውራዋለች፡፡


አይንሽ፣ ከንፈርሽ፣ ዳሌሽ ብለው በማማለል የማይረግብ ስሜታቸው ማርኪያ ሎሌ ያደርጉሻል፡፡ አንቺም ፊቴ አምሮ ቅርፄ ተስተካክሎ ይሆን እያልሽ የነሱ የወሲብ ማርኪያ ትሆያለሽ


መገላለጥ አንዱ የቂያማ መድረስ ምልክት ነው፣ ሰዉነታቸዉን አግባብ ባለዉ ልብስ ያልሸፈኑ ሴቶች በስፋት መታየት። ከፊል ገላቸውን ይሸፍናሉ። የሰውነታቸው ቅርፅ ለይቶ የሚያሳይ ጥብቅብቅ አልባሳትን ይለብሳሉ።





የነቁበት ነቅተውበት እየተመለሱ ነው፡፡ ይሄውና በምዕራቡ አለም ከሚሰልሙት ውስጥ 80% ሴቶች ናቸው፡፡ ብዙዎች የምዕራቡን “ነፃነት” ሸሽተው ወደ ኢስላም “ጭቆና” ይጎርፉ ይዘዋል፡፡


በጊዜ ንቂ፡፡ ብልጥ ማለት በሌሎች ላይ ከደረሰው ቀድሞ የሚማር ነው፡፡ ምሳሌሽን በትክክል ምረጪ፡፡ በአኢሻ ስብእና እያፈርሽ አሊሻን መሆን ካማረሽ


ንቂ! ሙስሊም ወንድምሽ ስለበደለሽ በኢስላም ላይ ብታምጪ ኢስላምን ቅንጣት ታክል አትጎጂውም፡፡ ብቻ በዱንያም ላታተርፊ ሁለቱንም አገር የከሰርሽ ከሁለት ያጣሽ ትሆኛለሽ፡፡





እራስሽን ሁኚ፡፡ የገደል ማሚቶ አትሁኚ፡፡ ሌሎች ስለሳሉ አትሳይ ስላነጠሱም አታነጥሺ፡፡ የተፈጠርሺው ለክቡር አላማ ነው፡፡


ተጠንቀቂ!! ከሸሪዐው አጥር ውጭ ያለ የመብት ጥያቄ አትጠይቂ፡፡ የፈጠረሽ ጌታ አንቺ እራስሽን ከምታውቂው በላይ ያውቅሻል፡፡ ላንቺም ከተኩላው “እንባ ጠባቂ” ቀርቶ ከራስሽም በላይ ያዝንልሻል፡፡


ደግሞም አትዘንጊ፡፡ ህይወት ማለት የአኺራ ህይወት ነው፡፡ አላህ አድሎሽ ሰማንያ ዘጠና አመት ብትኖሪ እንኳ በጊዜ ከኢስላም ባቡር ውስጥ ካልተሳፈርሽ ሲመሽ ይቆጭሻል፡፡





ምን ብትኖሪ ህይወትሽ መጨረሻ አለው፣ ሞት፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ ዘላለማዊ ህይወት፡፡ የዛሬው ተቆርቋሪ ለዚያ ቀርቶ ለዱንያ እንኳ ጤነኛ ህልም የለውም፡፡


ለአኺራማ እንኳን ላንቺ ለራሱም አይሆንም፡፡ ጆሮሽን ሰጥተሽ?! ቦታ ከሰጠሽውማ የአለም እዝነት የሆኑትን ነብይ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጠላትሽ እንደሆኑ ቀስ እያለ እያዋዛ ያሰርፅብሻል፡፡


በጊዜ ካልነቃሽ መውጣት ከማትችይበት ውስጥ ይነክርሻል፡፡ ተቆርቋሪ መስሎ ስለቀረበ እንዳያታልልሽ፡፡ ውሃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው፡፡





ግን እስቲ እኔ ልጠይቅሽ እውነት ነብዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ላንቺ ስለማይቆረቆሩ ነው ከ1400 አመት በፊት ሶሐቦቻቸው በተሰበሰቡበት ታላቅ ቀንና ታላቅ ቦታ ላይ “የሴቶችን ነገር አደራ” እያሉ አዋጅ ያሰሙት


እርግጥ ነው ብዙ በደል አለብሽ/አለብን፡፡ ግን አስተውይ ከበደሎቹ ሁሉ የከፋው ዘላለማዊ ክብር የሚያጎናፅፍሽን ኢስላምሽን እንዳታውቂ መደረግሽ ነው፡፡


እናም እልሻለሁ በMarch 8 ሳይሆን ከኢስላም መብትሽን ፈልጊ፡፡ ለወዳኛው ህይወትሽም ትጊ፡፡

የአላህ ሰላም ላንቺ ይሁን፡፡





ሼር በማድረግ ለእህቶች እንዲደርሳቸው ያድርጉ አላህ ሆይ፣ ቅኖችና ለሌሎችም መቀናት ምክንያት የሚሆኑ ሰዎች አድርገን

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል:- “ወደ ቅን መንገድ የተጣራ ሰው፣ የተከተሉት ሰዎች ሁሉ የሚያገኙት አጅር ምንም ሳይጎድልባቸው ለሱም ይኖረዋል…" (ቡኻሪና ሙስሊም)


ቴሌግራም t.me/khalidzemen


463 views14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ