2023-05-06 20:49:18
----------- -------------
★ለፍቅር ፊዳ★
----------- -------------
★ክፍል አስራ ዘጠኝ★
«በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ»
…እየተመናቀረች ስትሄድ ሁኔታዋ አስቆት እየተመለከታት ነበር ድንገት ፊት ለፊት ያላየችው ውሀ አንሸራቷት ልቶድቅ ስትል ሩጦ ሄዶ ወገቧን ያዛት እሷም ሸሚዙን ጨምድዳ ያዘቸው የህንድ ፊልም ሚሰሩ ይመስል ተቃቅፈው ይፋጠጣሉ ሁለቱም መላቀቅ የፈለጉ አይመስሉም እንደፈራና እንደደነገጠ ሰው አስመስለው ይፋጠጣሉ ሰው ያየናል ብለው ያሰቡም አይመስል ተመሳስጠዋል በመሀል የሀፍሲ እናት ኡዱእ ለማድረግ ሲወጡ ጉዳቸውን ተመልከተው ከመቆጣት ይልቅ ሳቃቸውን ለቀቁት እነሱም የሰሙት ሳቅ አባኗቸው ተላቀቁ ሀፍሲ እናቷን ማየት አፍራ ምንም ሳትል አጎንብሳ ከግቢ ወጣች ልጁም ስራው አሳፍሮት ለሀፍሲ እናት ለማስረዳት ይንተባተባል
"ማ…ማዘር ማለቴ የሚፍታህ እናት ወላህ ሌላ ነገር አይደለም ውሀ አንሸራቷት ልቶድቅ ስትል ነው የያዝኳት"
"አይዞህ ልጄ አትጨነቅበት እንደፈለክ አርገህ ያዘት ግን ወደ ሀላል መንገድ አምጡት ብቻ"አሉ ሳቃቸውን ገታ አድርገው ወደ ፈገግታ ለውጠው ሰሚርም ለስራው ኢስቲግፋር እያደረገ ሊሰግድ ገባ…ሀፍሲ እነ ማያ ቤት እስክትደርስ ድረስ የሰሩት ነገር በሀሳቧ እየተመላለሰ አንዴ ስፈግግ አንዴ ደሞ የእናቷ ማየት እያሸማቀቃት በሀሳብ እንደነጎደች እነ ሀፍሲ ቤት ደረሰች አሁን ግዴታ ሀሳቧን መሰብሰብ ስለነበረባት ሀሳቧን በሙሉወደ ወንድሟ አዞራ በሩን አንኩዋኳች ሰሞኑን የማያ አባት ብቻ ስለነበር እየመጣ ሚፍታህን የሚያየው የማያን መልክ ራሱ ሳትረሳው አትቀርም አሁን ምን እንደምትላት ራሱ አታቅም ሰው ላይ ከተናደደች በንግግር ሰውን እንደምታስቀይም ታቃለች እንደምንም ራሷን አረጋግታ ለማናገር አሰበች ከደቂቃዎች ቡሀላ በሩ ተከፈተ ኻዲማቸው ነበረች የከፈተችው
"እንዴ የጠፋ ሰው አሰላሙ አለይኩም ምንድነው እንደዚ መጥፋት አንቺዬ"አስገብተዋት በሩን ዘግተው ኻዲማቸው ነበረች ሁሌ ቤታቸው ስትመጣ ከርማ የሰሞኑ መጥፋቷ ጨንቋቸው? ነበር
"ወአለይኩም አሰላም ሀቢብቲ ትንሽ ወንድሜ ታሞ መውጣት ስላልቻልኩ ነው የጠፋሁት ደና ናቹ እናንተ"
"እኛስ ደና ነን አላህ ያሽርልሽ በይ ግቢ ውስጥ አሉ እነ ባባ"
"አረ አልገባም ባይሆን ማያን ፈልጌያት ነበር አለች?"
"ካልሽ ኸይር አሷስ አለች ግን…እኔ ምልሽ እንደው የሰሞኑ ፀባዯ ልክ አይደለም ምግብ በስርአት አትበላም ከክፍሏ ብዙም አትወጣም አንቺን ስላጣች ይሁን እንዴ?"
ሀፍሲ የሰማችው ነገር ገርሟት በውስጣ‘ደሞ ምን ሆንኩ ልትል ነው እሷ ምኗ ተነካ ወይስ ፀፀት ይዟት ነው’
"እኔጃ አክስቴ ጥሪያት እስቲ"
"ለምን ገብተሽ አታወሪያትም"
"አረ ቸኩላለው ሰላም ብያት ለመሄድ ብቻ ነው"
"እሺ በቃ"ብላ ልትጠራት ገባች በመሀል የማያ አባት ወተው ሰላም አሏት
"እንድ ሀፍሲዬ አሰላሙ አለይኪ ደና ነሽ"
"ወአለይኩም አሰላም ደና ነኝ ባባ አንተ ደና ነህ"
"እኔስ ደና ነኝ እኔ ምለው ልጄ እንደው ከማያ ጋር እንደተቀያየማቹ ልከርሙ ነው"አሏት እሷም የምፀት ፈገግታ እያሳየች አንገቷን አቀረቀረች
"እኔ ዝምድናን እንቀጥል የአላህ ራህመት እናገኛለን ብል እናነት በትንሽ ነገር ትቀያየማላቹ"
"እሺ ምን ላርግ ባባ ወንድሜ ሞቶ ቢሆንስ በሷ ምክኒያት ሆኖ ሊቀር ያለኝን አንድ ወንድሜን ባጣስ"
"እሺ እንድታገባው ላስማማት እና አፉ ተባባሉ"
"ሳትወደው አግብታው ሰላም ባይኖራቸውስ"
"ተይ እንጂ ልጄ አሁን ከመስመር እያለፍሽ ነው በቀደር እያመንሽ እንዲ ቢሆንስ ይባላል ተይ እንጂ ሀፍሲ"
"እሺ ባባ" ብላ ስትዞር ማያ በአንድ እጇ ሺቲዋን ወደላይ ሰብስባ ይዛ በአንድ እጇ ፀጉሯን እያከከች ወደነሱ እየመጣች ነው ሀፍሲ ስታያት የወንድሟ ነገር ትዝ ብሏት ልትኮሳተር ብላ መልሳ የይምሰል ፈገግታዋን መለሰች ማያም እነሱ ጋር ስደርስ መሬት እያየች በእጇ አንገቷን ይዛ "አቤት"አለቻት በደከመ ድምፅ የማያ አባት ያወሩ ብሎ ትቷቸው ገባ
"ደና ነሽ ማያ"
"ደና ነኝ"አጭር መልስ ሰጠቻት
"አንድ ነገር ላስቸግርሽ ነበር የመጣሁት"
"ምችለው ከሆነ እሺ"
"እ…ምን መሰለሽ አውቃለው በወንድሜ ምክኒያት እንዳስቀየምኩሽ ነገር ግን አንቺም የራሽን ስሜት ብቻ ማዳመጥ አልነበረብሽም የሱን ስሜት መረዳት ነበረብሽ ማያ ወላሂ እሱ ማንንም ሴት አፍቅሮ አያቅም ደሞ ባትወጂው ራሱ እኮ አብረሽው ሆነሽ ደስተኛ ብታረጊው ራሱ ትልቅ ነገር ነው እሱ ከህመሙ ገና እንደነቃ ራሱ ከኛ ይልቅ አንቺን ፈልጎ ሲያጣሽ ልቡ ሲደማ ማየት ትችይ ነበር ከህመሙ ሳይድንም እሷን ጥሪልኝ ማለት አላቆመም ምግብ ራሱ በስርአት ከበላ ወር ሆኖታል ወላህ ማያ ብታየው ከሰውነት አለም ወቷል ልክ አንቺ ለካሊድ እንደሆንሽው…"አይኖቿ በእንባ ታጥበው መናገር አቃታት ማያም ሳታስበው እያለቀሰች ነበር ሀፍሲም ቀጠለች
"በአላህ ማያ ልለምንሽ ከጎኑ ሁኚለት ቢያንስ ደስታውን ልመልከት"ማያም እንባዋን እየጠረገች ፈገግ እያለች
"ታቂያለሻ ሀፍሲ እኔም ታላቅ እህት ብትኖረኝ እንዲ እንዳቺ ቁማ እንደምትከራከርልኝ እሺ ለሱ ባስብ እኔስ ልቤስ እ…ንገሪኝ እኔስ አላሳዝንሽም"
"ከሱ ጋር ስለሆንሽ ምን ትሆኛልሽ ውበት ከሆነ ማንኛውም ሴት እንደምትፈልገው አይነት ቁመና አለው ኢማን፣ ገንዘብ ፣የተማረ ምን ጎደለው ንገሪኝ እስቲ"ሳታስበው ጮሀች
"ምን ቢሆን አልችልም!"
"ምን አልሽ…
★ይቀጥላል★…
ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶ ያጋሩ!!
Join and share
@ikhlasstudents
@ikhlasstudents
5.9K viewsHãyú, 17:49