Get Mystery Box with random crypto!

Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

የሰርጥ አድራሻ: @ibnumunewor
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 77.25K
የሰርጥ መግለጫ

كناشة ابن منور

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2024-04-02 07:13:08 በሱጁደ ቲላዋ ላይ ኢማሙ ምን ላይ እንዳለ ያላወቀ ሰው ምን ያድርግ?
~
በቁርኣን ውስጥ በሶላት ውስጥም ይሁን ከሶላት ውጭ በሚቅቀሩ ጊዜ ሱጁድ የሚወረድባቸው 15 አንቀፆች አሉ። በርግጥ ሱጁዱ ግዴታ አይደለም። ነገር ግን ኢማሙ ሱጁድ ከወረደ መከተሉ ግዴታ ነው።
በሶላት ውስጥ ኢማሙ እነዚህን አንቀፆች ቀርቶ ተክቢራ ሲያደርግ እሱን በእይታ መከታተል የማይችሉ ሰዎች (በተለይም ሌላ ክፍል ውስጥ የሚሆኑ ሴቶች) ኢማሙ ሩኩዕ ላይ ይሁን ወይም ሱጁድ ላይ ይሁን ለመለየት የሚቸገሩበት ጊዜ አለ። በዚህን ጊዜ ምን ያድርጉ?

1ኛ፦ ኢማሙ ሱጁድ ወርዶ ሳለ ተከታዩ ሩኩዕ ከመሰለው

1.1. ኢማሙ ሱጁድ ወርዷል። ተከታዩ ግን ሩኩዕ መስሎት እንዳጎነበሰ ከሩኩዕ ሳይነሳ ኢማሙ ሱጁድ ላይ መሆኑን ካወቀ ኢማሙን ይከተላል። ወደ ሱጁድ ይወርዳል።
1.2. ኢማሙ ሱጁድ ላይ እንደነበር ያወቀው ከተነሳ በኋላ ከሆነ ኢማሙን ተከትሎ ያጠናቅቃል። ሱጁዱ ግዴታ ስላልሆነ ምንም ማድረግ አይጠበቅም።

2ኛ፦ ኢማሙ ሩኩዕ ላይ ሆኖ ሳለ ተከታዩ ሱጁድ ከወረደስ?

2.1. ኢማሙ ሩኩዕ ላይ እንደነበር ካወቀ ተከታዩ ከሱጁድ ተነስቶ ቀጥ ብሎ ከቆመ በኋላ አጠር አድርጎ ሩኩዑን በመፈፀም ይከተለዋል። ሆን ተብሎ የተፈፀመ ስህተት ስላልሆነ ምንም ማድረግ አይጠበቅበትም።
2.2. ተመልሶ ሩኩዑን ሳያስገኝ ከቀረ ግን ሩኩዕ የጎደለው አንዱ ረከዐ ስለማይቆጠር መጨረሻ ላይ አንድ ረከዐ ይጨምራል።

ከዚህ ሁሉ ግን ኢማም የሆነ ሰው የተከታዮቹን ሁኔታ ከግምት ቢያስገባ ጥሩ ነው። የኢማሙን ተግባር ማየት የማይችሉ በመሆናቸው የተነሳ ሰዎች ሊሳሳቱ እንደሚችሉ ከገመተ ወይ ሱጁድ በሌላባቸው አንቀፆች ቢብቃቃ ወይ ደግሞ ሱጁደ ቲላዋውን ቢተወው የተሻለ ነው። ወሏሁ አዕለም።
=
የቴሌግራም ቻናል
t.me/IbnuMunewor
13.0K views04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 17:21:02 የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ነውረኛ ተግባር
("ሼር" አድርጉት)
~
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከዒድ ጋር በሚጋጭ መልኩ የፈተና ፕሮግራም አውጥቷል። ዩኒቨርሲቲው በቅድሚያ ካሌንደር አይቶ ፕሮግራሙን ማዘጋጀት ነበረበት። ነገር ግን ዩኒቨርሲቲው ያወጣው ፕሮግራም ከዒድ ጋር በመግጠሙ እንደሚቸገሩ ሙስሊም ተማሪዎች ቢያሳውቁትም አሻፈረኝ እንዳለ ነው። ይሄ ውሳኔው ምናልባትም ጥፋቱ ሆን ተብሎ የተፈፀመ እንደሆነ እንድናስብ የሚያደርግ ነው። ምናልባት ጥፋቱ በአንድ ወይም በተወሰኑ አካላት የተፈፀመ ከሆነ የሚመለከተው ክፍል እንዲያስተካክል እንጠይቃለን።
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ደረጃቸውን የሚመጥን ቁመና ሊኖራቸው ይገባል። በኛ ሃገር ተጨባጭ ግን ዩኒቨርሲቲዎች ማለት በአመዛኙ ለሌሎች ክፍሎች ጥላቻ ያረገዙ አካላት ጭቆና የሚያራምዱባቸው የግፍ አፀዶች ናቸው። በተለይ ደግሞ የነዚህ ተቋማት ቀዳሚ ሰለባዎች ሙስሊሞች ናቸው። ይሄ መቋጫ ያጣና የረባ መሻሻል የሌለው ልማድ ለሌላው የህብረተሰብ ክፍል ምሳሌ መሆን የነበረባቸው ምሁሮች ተራማጅ ያልሆኑ ፍፁም ኋላቀሮች እንደሆኑ እንዲሁም የሃገር ተስፋ መሆን የነበረባቸው ተቋማትም የበሰበሰ መዋቅር የታቀፉ እንደሆኑ ያሳያል።
ለማንኛውም ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ እንዲህ አይነቱን ለሌሎች እሴት ንቀትን የሚያንፀባርቅ ኋላ ቀር አካሄድን ሊያርም ይገባል። በዚህ ጉዳይ ላይ የሚመለከታችሁ ሁሉ ሃላፊነታችሁን እንድትወጡ እናስታውሳለን። የዩኒቨርሲቲው ተግባር አንድምታው ከፕሮግራም ማዛባት ያለፈ ነው።

ሁላችሁም "ሼር" አድርጉት ባረከላሁ ፊኩም።

Bahir Dar University, Ethiopia
Ministry of Education Ethiopia
=
የቴሌግራም ቻናል
t.me/IbnuMunewor
21.5K viewsedited  14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 14:25:11 የወር ደሞዝተኛ ዘካ
~
የወር ደሞዝተኛ ገንዘብ ዘካ ግዴታ የሚሆንበት የሚከተሉትን መስፈርቶች ሲያሟላ ነው።

① ለዘካ መነሻ መጠን (ኒሷብ) ሲደርስ።
ከኒሷብ በታች የሆነና በየጊዜው ወጭ የሚደረግ ገንዘብ ዘካ አይመለከተውም።

② ኒሷብ ከደረሰ በኋላ አመት ሲቆይ። አመት ያልሞላው ከሆነ መጠኑ ከፍ ያለ ቢሆንም ዘካ የለበትም።

ስለዚህ ለዘካ መጠን ደርሶ አመት ሲሞላው ዘካ ያወጣል። ለማውጫ ጊዜ ይሆነው ዘንድ አመቱ ከሞላ በኋላ በራሱ አንድ ቀን መርጦ ይወስናል። ከዚያም እስከ መጨረሻው ወር ከተጠራቀመው አጠቃላይ ገንዘብ ላይ 2•5% ያወጣል።

ውስብስብ አሰራር ውስጥ ከመግባት በዚህ መልኩ መጠቀም የተሻለ ነው። ወላሁ አዕለም።
=
ኢብኑ ሙነወር
የቴሌግራም ቻናል
t.me/IbnuMunewor
14.3K viewsedited  11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 06:31:42 ሰበር ሰበር ሰበር

አሁን ከምሽቱ 3:30 አካባቢ ጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አካባቢ እየተደረገ በነበረ ከባድ የቶክስ ልውውጥ በተራዊህ ሰጋጅ ወንድሞቻችን ላይ በሁለቱ ላይ የቦምብ በአንዱ ደግሞ የጥይት ጥቃት የደረሰ ሲሆን አንደኛው ወንድማችን አሁን ሆስፒታል እንደደረሰ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል ።

ተፃፈ በ የጎንደር ሙስሊሞች ድምፅ
መጋቢት 22/2016 አ ል
=
የነዚህ ሰዎች ትግል ግን አይገርማችሁም? አጣብቂኝ ውስጥ ባሉበት ሰዓት ሙስሊሙ ላይ የማያባራ ጥቃት ካደረሱ ተሳክቶላቸው አገር ቢቆጣጠሩ ምንድነው የሚያደርጉን? ይበልጥ የሚገርመው ደግሞ እነዚህን በኢስላምና በሙስሊሞች ጥላቻ የታወሩ አካላት የሚደግፉ ሙስሊሞች መኖራቸው ነው። ችግሩ ምን ሲደርስ ይሆን የሚነቁት?

ማሳሰቢያ፦

1- በጎንደርም ይሁን በሌሎች ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች ያላችሁ ወገኖች በዚህ ወቅት ለምን የተራዊሕ ሶላቱ አይቀርባችሁም? ተጨማሪ ጉዳት ከመድረሱ በፊት ፈጥናችሁ ብትወስኑ መልካም ነው።
2- ሌሎቻችን ደግሞ ሼር በማድረግ ድምጻቸውን ብናስተጋባላቸው መልካም ነው። ዱዓም እናድርግላቸው።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
21.8K views03:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 18:15:17 አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ።

ውድ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ይህ አዲስ የተከፈተ የጀመዐችን ቻናል ነው። የተከፈተበት አላማ ጀማዐው ላይ ያሉ የተለያዩ ፕሮግራሞችን ለመለጠፍ እና ጠቃሚ ነጥቦችን ለመተዋወስ ነው። ለምታውቋቸው የጀማዐችን ልጆች ሊንኩን forward በማድረግ ከቻናሉ እንዲጠቀሙ እንዲሁም ቻናሉንም እንድታጠናክሩ እንጠይቃለን።
بارك الله فيكم
https://t.me/Wku_ms_Official_Channel
17.4K viewsedited  15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 14:44:07 ጥቂት ወሳኝ ነጥቦች በለይለተል ቀድር ዙሪያ
~
ለይለቱል ቀድር ማለት ትልቅ ደረጃ ያላት ሌሊት ማለት ነው። ከፊል ዓሊሞች ዘንድ ደግሞ ፍጡራንን የሚመለከቱ የአመቱ ውሳኔዎች የሚተላለፍባት ሌሊት ማለት ነው።

1. የለይለተል ቀድር ደረጃዎች፦

* ቁርኣን የወረደባት ሌሊት ነች። ጌታችን “እኛ (ቁርኣኑን) በለይለተል ቀድር አወረድነው”ብሏል። [አልቀድር፡ 1]
* በሷ ውስጥ የተፈፀመ ዒባዳ ከሌሎች ሌሊቶች ምንዳው የበለጠ ነው። አላህ “የመወሰኛዋ ሌሊት ከሺህ ወር በላጭ ናት” ይላል። [አልቀድር፡ 3]
* በሷ ውስጥ መላእክት ኸይርን ይዘው ወደ ምድር ይወርዳሉ። ጌታችን “በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ (ጂብሪል) በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ” ብሏል። [አልቀድር፡ 4]
* ሌሊቷ ዒባዳ የሚበዛባት፣ ሰላም የሚሰፍንባት ለሊት ናት። ጌታችን “እርሷ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት” ብሏል። [አልቀድር፡ 5]
* የተባረከች ሌሊት ናት። ጌታችን “እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው” ብሏል። [ዱኻን፡ 3]
* በዚች ሌሊት አላህ በአመቱ ውስጥ ያሉ የፍጡራኑን የእድሜና የሲሳይ ልኬታዎችን ይፅፋል። “በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል” ብሏል አላህ። [ዱኻን፡ 4]
* በዚያች ሌሊት ምድር ላይ የሚኖሩት የመላእክት ብዛት ከጠጠሮች ብዛት የበዛ ነው። [አልባኒይ ሐሰን ብለውታል]
* ለተጠቀመባትና አጅሩን ከአላህ ላሰበ ሰው ከወንጀል መማርያ ሌሊት ነች። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- “ለይለተል ቀድርን አምኖና አስቦ የቆመ ሰው ያለፈ ወንጀሉ ይታበስለታል።” [ቡኻሪና ሙስሊም]
ስለዚህ ይህቺን ወሳኝና እጅግ የላቀ ዋጋ ያላት ሌሊት ለማገኘት የምንችለውን ሁሉ ልንጣጣር ሌሎችንም ልናበረታታ ይገባል። ኢብኑል ቀይም ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “ለይለተል ቀድር በአመት ውስጥ የምትገኝ አንዲት ቀን ብትሆን እሷን ለማገኘት ስል አመቱን ሁሉ እቆም ነበር። በ(ረመዳን) አስር ሌሊቶች ውስጥ ከሆነችማ ምን ነካህ? (እንዴት እዘናጋለሁ?!)” [በዳኢዑል ፈዋኢድ፡ 1/55]

2. ለይለቱል ቀድር የምትገኘው በየትኛው ጊዜ ነው?

የምትገኘው በረመዷን ብቻ ነው። ከረመዷንም በመጨረሻዎቹ አስሮች ውስጥ። ነብዩ ﷺ “ይቺን ሌሊት እየፈለግኩ የመጀመሪያውን አስር ኢዕቲካፍ አደረግኩኝ። ከዚያም መካከለኛውን አስር ኢዕቲካፍ አደረግኩኝ። ከዚያም (የሆነ አካል) መጥቶኝ ‘እሷ በርግጥም የመጨረሻው አስር ላይ ናት’ አለኝ” ማለታቸው ይህን ያስረግጣል።
ይቺ ታላቅ ሌሊት እንዳታልፈን የምንችለውን ሁሉ ልንጣጣር ይገባል። ነብዩ ﷺ በሐዲሣቸው እንዲህ ብለዋል፡- “በሱ ውስጥ ከአንድ ሺ ወር የምትበልጥ ሌሊት አለች። የሷን ኸይር የተነፈገ በእርግጥም (ትልቅ ነገር) ተነፍጓል።” [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 2247]

3. መቼ እንፈልጋት?

ይበልጥ የሚገመተው 27ኛዋ ሌሊት ናት። ይሁን እንጂ “ለይለተል ቀድርን በ23ኛዋ ሌሊት ፈልጓት” ማለታቸው እንዲሁም “ለይለተል ቀድርን በመጨረሻዎቹ አስሩ (ሌሊቶች) ፈልጓት። ከተረታችሁ በመጨረሻዎቹ 7 ላይ አትረቱ” ማለታቸው ለይለተል ቀድር ሁሌ በአንድ ሌሊት ላይ እንደማትገደብ ያስረዳል። በተለይ ደግሞ በዊትሮቹ (21፣ 23፣ 25፣ 27፣ 29) የመሆን እድሏ ሰፊ ነው። ይህን አስመልክተው ነብዩ ﷺ “ለይለተል ቀድርን ከረመዷን በመጨረሻዎቹ አስሩ (ሌሊቶች) በዊትሮቹ ፈልጓት” ብለዋል። [ቡኻሪይና ሙስሊም]
ይህ ማለት ግን ከነጭራሹ በሸፍዕ ለሊቶችም (22፣ 24፣ 26፣ 28፣ 30) አትሆንም ማለት አይደለም። ምክንያቱም ነብዩ ﷺ “ከረመዷን የመጨረሻዎቹ አስሮች ውስጥ ፈልጓት። ዘጠኝ ሲቀረው፣ ሰባት ሲቀረው፣ አምስት ሲቀረው” ብለዋልና። ወሩ 29 ቀን ከሆነ 9፣ 7፣ 5 ሲቀር ዊትር የሚሆኑት ከመጨረሻ ወደ ኋላ ሲቆጠር ነው። ከመጀመሪያ ለሚቆጥር ግን ዊትር ሳይሆን ሸፍዕ ቁጥር ነው የሚሆኑት። ይህም ሸፍዕ ሌሊቶችም ላይ የመሆን እድል እንዳለ ያስረዳናል። ቢሆንም ግን “ከ(መጨረሻው አስር) በዊትሩ ፈልጓት” ስላሉ ዊትሩ ላይ ይበልጥ ማተኮር ይገባል።

4. በለይለተል ቀድር ምን ይጠበቅብናል?

ዒባዳ ማብዛት። ነብዩ ﷺ “ለይለተል ቀድር አምኖና አስቦ የቆመ ሰው ያለፈ ወንጀሉ ይታበስለታል” ይላሉ። [ቡኻሪና ሙስሊም] እናም በዚች ሌሊት ታላቅነትና መደንገግ አምኖ፣ ከዚያም ለታይታ፣ ለጉራና መሰል አላፊ ኒያ ሳይሆን አጅሩን ከአላህ በማሰብ እንደ ሶላት፣ ዱዓእ፣ ቁርኣን መቅራት፣.. የፈፀመ ሰው ወንጀሉ ይታበስለታል ማለት ነው።

5. ምልክቶቿ

1. “በዚያን ቀን ማለዳ ላይ ፀሀይዋ ነጭ ሆና ጨረር ሳይኖራት ትወጣለች።” [ሙስሊም]
2. በዚያን ሌሊት ዝናብ ሊዘንብ ይችላል። [ቡኻሪና ሙስሊም]
3. ቀጣዩ ቀን አየሩ ሞቃትም ብርዳማም ሳይሆን የተስተካከለ ይሆናል። ፀሀይዋም ደካማና ቀይ ትሆናለች። [ሶሒሑል ጃሚዕ]
እነዚህ ምልክቶች ግን አንፃራዊ ናቸው ይላሉ ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ። በአካባቢው ባለው የአየር ሁኔታ ሊወሰን ይችላል። ስለሆነም በትክክል ለይለተል ቀድር በተከሰተበት ጊዜም እነዚህን ምልክቶች ብዙ የማያያቸው ሊኖር ይችላል።

6. ለይለተል ቀድር ለሰጋጆች ብቻ አይደለችም!

የወር አበባ ላይ፣ የወሊድ ደም ላይ ያሉ፣ መንገደኞች፣ … የዚች ሌሊት ትሩፋት አያልፋቸውም። ማስረጃው ጠቅላይ ነውና። ባይሆን ከሶላት ውጭ ባሉ ዒባዳዎች ላይ ሊበራቱ ይገባል። በዚያች ሌሊት ዱዓእ ማብዛት ጥሩ ነው። እንዲያውም ሱፍያኑ ሠውሪይ ረሒመሁላህ “በሌሊቷ ከሶላት ይልቅ ዱዓእ እኔ ዘንድ የተወደደ ነው” ይላሉ።

7. ለይለተል ቀድር በአይን ትታያለች?

አንዳንዶች በረመዷን የመጨረሻው አስር ሌሊት ላይ እግራቸውን ዘርግተው፣ እያወሩ ሰማይ ሰማይ ያንጋጥጣሉ። የሚጠባበቁት ተወርዋሪ ኮከብ ነው። እሱን ሲያዩ “አኑረን አክብረን” ብለው ይንጫጫሉ። ይሄ ባዶ እምነት ነው። ለይለተል ቀድር አላህ በአንዳንድ ባሮቹ ቀልብ ላይ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የመረጋጋት ወይም የመለየት ስሜት ከማሳደሩ ውጭ በአይን የሚታይ ነገር አይደለም። የሚታየው ምልክቶቿ እንጂ እራሷ አይደለችም። ሰዎች የሚጠበቅባቸውን ከተወጡ ሌሊቱ ለይለተል ቀድር መሆኑን ባያውቁ እንኳን ትሩፋቷን አያጡም።

8. ለይለተል ቀድር እንደሆነ ውስጡ ያደረ ሰው ምን ያድርግ?

በተለይ ደግሞ ሌሊቱ ለይለተል ቀድር እንደሚሆን ውስጣችንን ከተሰማን ይበልጥ ልናተኩርበት የሚገባን ዱዓእ “አሏሁመ ኢነከ ዐፉውዉን ቱሒቡል ዐፍወ ፈዕፉ ዐኒ” (“ጌታዬ ሆይ! አንተ በርግጥም ይቅር ባይ ነህ። ይቅር ማለትን ትወዳለህ። ስለሆነም ከኔ ይቅር በለኝ” የሚለው ነው። [አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል] ስለዚህ ዋናው ትኩረታችን የአላህን ይቅርታ ለማግኘት ይሁን።

9. ግን ለምን አላህ ለይለተል ቀድርን ስውር አደረጋት?

ዑለማዎች እንደሚሉት ታላላቅ ትሩፋቶች በሚገኝባቸው የረመዷን የመጨረሻ ሌሊቶች ሙስሊሞች በዒባዳ ይበራቱና ይጠናከሩ ዘንድ ነው አላህ ይቺን ሌሊት ስውር ያደረጋት። እናም ለይለተል ቀድርን እንዳታመልጣቸው ሲጣጣሩ ለይተው ቢያውቋት ሊኖራቸው ከሚገባው በበለጠ ለዒባዳ ይተጋሉ። በዚህም ይበልጥ ይጠቀማሉ። ለይተው ቢያውቋት ግን እሷ ብቻ ላይ አነጣጥረው ሌሎቹ ሌሊቶች ላይ ይዘናጉ ነበር። እናም መሰወሯ ነብዩ ﷺ እንዳሉት ለኛ ኸይር ነው። [ቡኻሪይ]
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሰኔ 29/2007)
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
18.6K views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 14:44:00
13.3K views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 07:03:36
#3ልጆቼን_ሳልሞት_አገናኙኝ
(ሼር ማድረግ ሶደቃ ነው ወገን። ወገኑን የሚረዳ የአላህ እርዳታ ከሱ ጋር ነው።)
~
ወ/ሮ ሐሊማ ሰይድ እባላለሁ ሰሜን ወሎ ወልድያ ከተማ ነው የምኖረው። ከባለቤቴ ሙሀመድ ሁሴን (አባናኖ) ጋር ተጋብተን አ. አ. እንንኖር ነበር ከዛም አረብ ሀገር በመሄድ #ሁለቱን_ልጆቻችንን ወለድን። #ሶስተኛዋ አ. አ. ተወለደች።
ልጆቼ
1ኛ አብዱልመጅድ ሙሀመድ ሁሴን
2ኛ ፎዝያ ሙሀመድ ሁሴን
3ኛ መሬም ሙሀመድ ሁሴን

አ.አ. አየር ጤና አካባቢ እንኖር የነበረ ሲሆን ባለመግባባትችን እና በኑሮው መክበድ ምክንያት በ1994 ተመልሼ ወደ አረብ አገር ስሄድ ልጆቼን አክስታቸው ጋ ሰጥቼ ብሄድም አባታቸው ከአክስታቸው ቀምቶ ወሰዳቸው።

አረብ ሀገር እያለሁ ለልጆቼ የምችለውን እያደረኩ የነበረ ቢሆንም ለምን ጥለሽ ሄድሽ በሚል ልጆቼን ከ1997 ጀምሮ ሊያገናኘኝ አልቻለም።

ትልቁ ልጄ አብዱልመጅድ በ1997 አ.አ ዳንዲቦሩ ትምርት ቤት እየተማረ ትምርት ቤቱ እየሄድኩ አገኘው የነበረ ቢሆንም በሌላ ጊዜ ስሄድ ትምርት ቤቱን ለቋል ተብሎ ላገኘው አልቻልኩም።

ለማግኘት ብዙ ግዜ አ.አ ተመላለስኩ እንኖርበት የነበረው ሰፈር ጠየቅኩ ላገኛቸው አልቻልኩም። በእናትነት አንጀት ይህን ሁሉ አመት እነሱን እያሰብኩ አለሁ አባታቸው አልፎ አልፎ ቢደውልም ልጆቹን ግን እንዳገኛቸው አይፈቅድም።

ሲደውል ልጆቹ ትልቁ ልጄ አብዱልመጅድ ጂማ ዩንቨርሲቲ መካከለኛዋ ፎዝያ ጎንደር ዩንቨርሲቲ እንደተማሩ ነግሮኛል።
ልጆቼን ከ 20 አመት በላይ ሳላገኛቸው እዬኖርኩ ነው እባካችሁ ይህን የምታዩ ሁሉ ሳልሞት ልጆቼን እንዳገኛቸው አግዙኝ።

ስልክ
0921568570
0910633833
17.0K views04:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-30 19:48:10 የሌሊት ሶላት
~
ተራዊሕ፣ ተሀጁድ እና የሌሊት ሶላት የሚባሉት ለተለያዩ ሶላቶች የተሰጡ የተለያዩ ስያሜዎች አይደሉም። ይሄ የኢስጢላሕ ጉዳይ ነው። ትኩረት ልንሰጥ የሚገባው ከቃሉ ይልቅ ጭብጡ ላይ ነው። የሌሊት ሶላት የሚለው ተሀጁድንም፣ ተራዊሕንም ይገልፃል። ተራዊሕ የሚለውን ቃል ዑለማኦች በረመዷን ወር ከዒሻእ በኋላ በጀማዐ የሚሰገደውን ሶላት ለመግለፅ ይጠቀሙታል። ልብ በሉ! ከአፈፃፀሙ በስተቀር አመቱን ሙሉ ካለው የሌሊት ሶላት የተለየ አይደለም።
ተሀጁድ ሰዎች ሌሊት ተነስተው የሚሰግዱት ሶላት ነው። የሌሊት ሶላት ወቅቱ ከዒሻእ ሶላት በኋላ ጀምሮ እስከ ፈጅር ድረስ መሆኑ ይታወቃል። ስለዚህ እነዚህ ሶስት ስያሜዎች (ተራዊሕ፣ ተሀጁድ እና የሌሊት ሶላት) የአንድ ሶላት መጠሪያዎች ናቸው ማለት ነው።
በዚህ ጉዳይ ላይ ትንሽ ማለት የፈለግኩት አመት ጠብቆ መነታሪኪያ ስለሚሆን ነው። ነጥቡን ለማጥራት ከመሞከሬ በፊት አንድ ቀዳሚ ነጥብ ላንሳ። እሱም በርእሱ ላይ የትኛውንም አቋም ብንይዝ ሃሳባችን ቢለያይ እንኳ በልክ እንሁን። ዑለማኦች የተለያዩበት፣ ከመለያየታቸውም የጎሪጥ ያልተያዩበት ጉዳይ እንደሆነ አውቀን እነሱ በያዙት መጠን እንያዘው። ዑለማኦች ብቻ ሳይሆኑ ራሳችንም በጉዳዩ ላይ ያለን አቋም ሊቀያየር ይችላል። ከስሜት ነፃ እስከሆን ድረስ ይሄ የሚጎዳ አይደለም። ወደ ነጥቦቹ ልግባ፦

1. የተራዊሕ ሶላት "መልካም" ቢድዐ ሳይሆን በቀጥታ ከነብዩ ﷺ የተገኘ ሱና ነው። [ቡኻሪይ፡ 872] [ሙስሊም፡ 1271] ከዚያም በአንድ ጀማዐ መስገዱ ተቋርጦ ከፊሉ በጥቂት በጥቂት ተከፋፍሎ ከፊሉ ደግሞ በተናጠል ሲሰግድ ከቆየ በኋላ ልክ በነብዩ ﷺ ኢማምነት ተጀምሮ እንደነበረው በአንድ ጀማዐ በዑመር አማካኝነት ተሰብስቧል። [ቡኻሪይ፡ 2010]
2. ቁጥሩ ከነብዩ ﷺ በተግባር የተገኘው እስከ 11 ረከዐ ድረስ ነው። ይህንን ይዘው ጭማሪው ቢድዐ ነው ያሉ አሉ፤ የብዙሃን ዑለማእ ምርጫ ባይሆንም። የነብዩን ﷺ ቃላዊ መረጃዎች እና የቀደምቶችን አፈፃፀም ለተመለከተ ግን ጉዳዩ በቢድዐ ለመግለፅ የሚያስደፍር አይደለም። ስለዚህ ከአንድ አቅጣጫ ጥናት በመውጣት ጠለቅ ብሎ በማየት ጥንቃቄ ቢኖረን ይመረጣል። ከመሆኑም ጋር አፈፃፀማችንን ከነብዩ ﷺ ተግባራዊ አፈፃፀም ማለትም 11 ረከዐ ጋር ብናጣጥም የበለጠ ነው፣ ወላሁ አዕለም።
3. በረመዷን የመጨረሻው 10 ላይ ሌሊት ላይ ተነስቶ መስገዱ ቢድዐ ይደርሳል? በፍፁም!
3.1. ከጊዜ አንፃር፦ ሙሉ ሌሊቱ የሶላት ወቅት ነው። እንዲያውም ለሚችል ሰው የሌሊቱ መጨረሻ ከመጀመሪያው በላጭ ነው። በላጭ በሆነ ወቅት ላይ መሰባሰቡ ከቢድዐ ጋር የሚገናኝበት ነጥብ የለም።
3.2. አፈፃፀም፦ በጀማዐ መስገድም ቢሆን ተጨባጭ መረጃ የመጣበት ስለሆነ በዚህም በኩል ክፍተት የለም።
3.3. በመጨረሻው አስር ላይ ትጋት መጨመሩ፦ ተጨባጭ መረጃዎች የመጡበት ነው። አንድ ሁለት ልጥቀስ፦
ከእናታችን ዓኢሻ ተይዞ እንዲህ ብላለች፦
كان رسول الله صلى الله عليه وسلم إذا دخل العشر أحيا الليل، وأيقظ أهله، وجدَّ وشدَّ المئزر
"የአላህ መልእክተኛ ﷺ የመጨረሻው አስር ሲገባ ጊዜ ሌሊቱን በንቃት ያሳልፉ፣ ቤተሰባቸውን ያነቁ፣ በእጅጉ ይጣጣሩና ትጥቃቸውን ያጠብቁ ነበር።" [ቡኻሪይ፡ 2024] [ሙስሊም፡ 1174]
* ሌሊቱን በንቃት ያሳልፉ ነበር ማለት በዒባዳ ንቁ ሆነው ማለት ነው።
* ቤተሰባቸውን ያነቁ ነበር ማለት ለሌሊት ሶላት ነው።
* ትጥቃቸውን ያጠብቁ ነበር ማለት ከሴት ያገሉ ወይም ዒባዳ ላይ ያላቸውን ትጋት ከቀደመው ይጨምሩ ነበር ማለት ነው። [ፈትሑልባሪ፡ 4/316]

በሌላም መረጃ እናታችን ዓኢሻ እንዲህ ብላለች፦
كان رسول الله صلى الله عليه وسلم يجتهد في العشر الآخر ما لا يجتهد في غيره
"የአላህ መልእክተኛ ﷺ በመጨረሻው አስር ላይ በሌላው ላይ የማይተጉትን በተለየ ይተጉ ነበር።" [ሙስሊም፡ 1175]
3.4. ቁጥሩ፦ ከ11 በላይ መስገድ ይቻላል የሚል ሰው እዚህ ላይ ጥያቄ ሊያነሳ አይገባም። አይቻልም ለሚል አካል ግን ዐምር ብኑ ዐበሰህ ረዲየላሁ ዐንሁ "የትኛው የሌሊቱ ክፍል ነው ይበልጥ ለዱዓእ ተቀባይነት በላጭ የሆነው?" ብለው ሲጠይቋቸው ነብዩ ﷺ እንዲህ ሲሉ መልሰዋል፦
فصلِّ ما شئتَ فإنَّ الصَّلاةَ مشْهودةٌ مَكتوبةٌ حتّى تصلِّيَ الصُّبحَ
"ያሻህን ስገድ። በዚህ ጊዜ የሚሰገድ ሶላት መላእክት የሚጣዱባት ነችና። ፈጅር እስከምትሰግድ ድረስ።" [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1277]
በተጨማሪም እንዲህ ብለዋል፦
صلاة الليل مثنى مثنى فإذا خشي أحدكم الصبح صلى واحدة توتر له ماقد صلى.
"የሌሊት ስግደት ጥንድ ጥንድ ነው። አንዳችሁ ንጋትን ከሰጋ የሰገደውን ዊትር ታደርግ ዘንድ አንድ ረከዐ ትሰግዳለህ።" [ቡኻሪይ፡ 472] [ሙስሊም፡ 749]
3.5. በአንድ መስጂድ ላይ ድጋሚ ጀማዐ መቋቋሙም ቢሆን ለተቃውሞ የሚቀርብ አይደለም። ምክንያቱም ዑመር በአንድ እስከሚሰበስቡት ድረስ በአንድ መስጂድ ውስጥ የተለያዩ ጀማዐዎች ሲቋቋሙ ነበርና።
ስለዚህ ማታ ለሰገደም ይሁን ላልሰገደ ሌሊት ላይ በጀማዐም ይሁን ለብቻ መስገድ ይችላል። ከዊትር በኋላ መስገድም መረጃ መጥቶበታል። ባይሆን ሁለት ጊዜ ዊትር አይሰገድም። "በአንድ ሌሊት ሁለት ዊትር የለምና።" [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 7567]
ወላሁ አዕለም!
=
* ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
* ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
* ዋትሳፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
15.3K viewsedited  16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-30 15:14:32 ዘካተል ፊጥርን ወደ ሃገር ውስጥ መላክ
~
ውጭ ሃገር ያላችሁ ወገኖች ዘካተል ፊጥርን ወደ አገር ቤት ብትልኩ ነው የሚሻለው፡፡ በአሁኑ ጊዜ የሃገራችን ህዝብ በጣም ችግር ላይ ነው ያለው። የዋጋ ንረቱ እሳት ሆኗል። የሰላሙ መጥፋት ችግሩን ይበልጥ አባብሶታል። አእላፍ ወገን ተፈናቅሎ አውላላ ሜዳ ላይ ፈስሷል። ስለዚህ ውጭ ያላችሁ ወገኖች በተቻለ መጠን ዘካችሁን ወደ አገር ቤት ብትልኩ ትንሽም ቢሆን ትደጉማለች። እንዲያውም የ 2 እና 3 ኪሎ ዱቄት ዋጋ ከምትገደቡ በራሳችሁ ፈቃድ ጨመርመር ብታደርጉት ከአላህ ዘንድ የበለጠ ታተርፉበታላችሁ።
እንደሚታወቀው ዘካተል ፊጥርን በተመለከተ በላጩ አንድ ሙስሊም በፆመበት ሃገር መስጠቱ ነው። በሰዎች ወይም በድርጅቶች አማካኝነት ከመስጠትም በራስ መፈፀሙ የተሻለ ነው። ምክንያቱም ወኪሎች ምናልባት ጊዜውን ጠብቀው ለመስጠት የማይጠነቀቁበት፣ ወይም አስገዳጅ ሁኔታ በሌለበት በገንዘብ የሚሰጡበት፣ ወይም ደግሞ በማይገባ ቦታ ላይ የሚያውሉበት ሁኔታ ሊገጥም ይችላልና።

ነገር ግን አንድ ሙስሊም በሆነ ምክንያት በራሱ መፈፀም ከቸገረውና እምነት የሚጥልበት ሰው ካለው በውክልና እንዳይፈፅም የሚከለክል ምንም ማስረጃ የለም፣ ምንም! እንዲያውም አስገዳጅ ሁኔታ ባይኖር እንኳ ፍላጎቱ ከሆነ በታማኝ ወኪል ቢያስፈፅመው ምንም የሚከለክለው ማስረጃ የለም። ይህንን የማነሳው አንዳንዶች ክልክል የሆነ አስመስለው ስለሚያቀርቡት ነው። ልብ በሉ! በዚህ ላይ የሚጠቀሱ የዑለማዎች ንግግሮች ከጥንቃቄ አንፃር የተሰነዘሩ ምክረ ሃሳቦች እንጂ ከልካይ መረጃ ሆነው የመቅረብ አቅም የላቸውም። ሐራም ማለት ሸሪዐ ሐራም ያለው ብቻ ነው። እንዲያውም ዛሬ ዛሬ በውክልና ለማስፈፀም አስገዳጅ ሁኔታዎች የሚገጥሙበት ጊዜዎች አሉ።
ስለዚህ በዚህ ጉዳይ በራሳችሁ ለመፈፀም የተቸገራችሁ ሙስሊሞች በምታምኗቸው ወኪሎች አማካኝነት ለማስፈፀም ተንቀሳቀሱ። "ዘካተል ፊጥርን አንድ ሰው ተሰዶ በሚኖርበት ሃገር ነው የሚያወጣው ወይስ በነባር ሃገሩ ነው? " ተብለው የተጠየቁት ሸይኹል አልባኒይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ሲሉ መልሰዋል፦
إذا كان لديه فقراء فيجوز ، كما أنه يجوز أن يوكل غيره بأن يخرج الزكاة في بلده الأصيل
"እሱ ዘንድ ድሃዎች ካሉ (ተሰዶ በሚኖርበት ማውጣት) ይፈቀድለታል። ልክ እንዲሁ ሌላን ወክሎ ዘካውን በነባር ሃገሩ እንዲያወጣለት ማድረግም ይፈቀዳል።" [ሲልሲለቱል ሁዳ ወኑር: 694]
ይህንን ከግንዛቤ በማስገባት ዘካችሁን ወደ ሃገር ቤት ብትልኩ የተሻለ ይሆናል። ወላሁ አዕለም።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
13.7K viewsedited  12:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ