Get Mystery Box with random crypto!

ሀላል ትዳር👫💍

የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የቴሌግራም ቻናል አርማ hayu_abdi — ሀላል ትዳር👫💍
የሰርጥ አድራሻ: @hayu_abdi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.54K

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-08-23 18:56:50 ከተራራው ላይ
ክፍል ስድስት
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹እህህም ሲደላ፣ ሺህ ስቃይ ቢከበኝ ማንባት የት ተገኝቶ፣
የሆዴን ረመጥ፣ መታገስ ነው እንጂ በብሶት ተሞልቶ፣
አይነገር ነገር!››
***
ቅዳሜ ማታውን አብዱኬ ስልኩን ይዞልኝ መጣ፡፡ በጣም የሚያምር አዲስ ስልክ ነው፡፡ ከቤተ-መፅሀፍቱ እየወጣን አብዱኬ ‹‹ስሚ ይኼ አዲስ ሞዴል ነው፡፡ እነሱ አራት ሺህ ብር ካገኙበት በቂያቸው ነው፡፡ አንቺ በደንብ አትርፈሽበት ትሸጪዋለሽ፡፡ ከቤቱ አስራአምስት ምናምን የሚሸጥ ስልክ ነው፡፡›› አለኝ፡፡
ከፍቼ ሳየው ውስጡ ላይ ምንም የለውም፡፡ ‹‹አስፈሮርምተኸው ነው እንዴ?››
‹‹አዎ ፓተርን ምናምን ነበረው፡፡ በቃ አሁን ከቤቱ ሲወጣ እንዳለው ነው! አያስፎግርም!››
‹‹ግን ምን ብዬ ልሸጠው ነው?››
‹‹ከውጪ ተልኮልኝ ነው ምናምን እያልሽ ነዋ! ግን ደግሞ ሰው እየመረጥሽ!››
ስልኬ ጠራ፡፡ የማላውቀው ቁጥር ነበር፡፡ አነሳሁት፡፡
በጣም በተረጋጋ ድምፅ ‹‹አብርሼ ደህና አመሸህ …… ምህረት ነኝ፡፡›› አለች፡፡
‹‹ደህና አመሸሁ! ደህና አመሸሽ?››
‹‹ደህና …… ይቅርታ በዚህ ሰዓት ስለደወልኩ …… ጠዋት ያለንን ቀጠሮ አልረሳኸውም አይደል?››
‹‹አዎ! ለማህሌት እኮ ነግሬያት ነበር፡፡ ውሀውንም ገዝቻለሁ፡፡ እና ደግሞ አቤላ ላይብረሪው ጋር ይጠብቃችኋል! እንዳይጠፋችሁ እሱ ይዟችሁ ይመጣል!››
‹‹እሺ አብርሽዬ በጣም እናመሰግናለን፡፡ በቃ አስራሁለት ሰዓት ሰፈራችሁ ለመድረስ እንሞክራለን!››
ተሰነባብተን ስልኩ ተዘጋ፡፡ አብዱኬ ማናት በሚል አይን ተመለከተኝ፡፡ ነገርኩት፡፡
‹‹እና ነፍ ቺኮች ሰፈራችንን ሊያስጨንቁት ነዋ? …… ኧረ ይኼማ አያመልጠኝም! ነገ ስራ ከሰዓት እሄዳለሁ፡፡››
አሳቀኝ፡፡ በቀጣዩ ቀን ጠዋት ላይ እኔና አብዱኬ ታች ወርደን ጠበቅናቸው፡፡ በሶስት የቤት መኪና ተከታትለው መጡ፡፡
‹‹ስሚ ኢቦ ህብረት ምናምን ናቸው አላልሽም እንዴ?›› አብዱኬ ከመኪናቸው የሚወርዱት ልጆች ላይ አይኑን እንደጣለ ጠየቀኝ፡፡
በእርግጥ እኔም የጠበቅኩት ብዙ ሰው ነበር፡፡ አቤል ሳይቆጠር በጥቅሉ ከመኪናዎቹ የወረዱት አስር ብቻ ነበሩ፡፡ ሁለት ወንዶች አሉ በተረፈ ሁሉም ሴቶች ናቸው፡፡ ሴቶቹ ለመንቀሳቀስ የሚመቹ ቀሚሶችን አድርገዋል፡፡ ሰላም ተባብለን ማህሌትና ምህረት እየተቀባበሉ ሌሎቹን አስተዋወቁኝ፡፡ ሁሉም ረጋ ያሉ ናቸው፡፡
‹‹ስሙ ቀሚስ አድርጋችሁ ነው እንዴ የምትወጡት? ወይስ ልትቀይሩ ነው?›› አብዱኬ ከፊት ከፊት እየሄደ ይጠይቃቸዋል፡፡
ምህረት ሰልፊ ስቲኳ ላይ ስልኳን እያሰረች ‹‹እኛ እኮ ሱሪ አንለብስም!›› አለችው፡፡
‹‹ጴንጤ አይደላችሁ እንዴ …… ለምን አትለብሱም?››
‹‹ጴንጤ አይደለንም …… ሐዋሪያት ነን!›› ፈገግ አለች፡፡
አብዱኬ ወደኋላ ዞር አለና በግርምት ‹‹ሐዋርያት የሚባል እምነት አለ?›› አለ፡፡ ፈገግ አለችለት፡፡
‹‹ገባሻ እኔ ፌሎው ምናምን ሲሉ የምሰማው እነሱን ስለሆነ ነው፡፡ ኮንትራት ምናምን ጉዞ እንወስዳቸው ስለነበር እንደዛ ነበር የመሰለኝ!››
‹‹ልክ ነህ ብዙ አይደለንም …… በተለይ ወደዚህ ደግሞ የለንም ማለት ይቻላል፡፡››
የኛ ቤት ቅያስ ጋር ስንደርስ እኔና አቤላ ሮጥ ብለን ውሀውን ይዘን ደረስንባቸው፡፡ አብዱኬ እያሳሳቃቸው እኔና አቤላ ውሀውን እያከፋፈልን ማህሌት የቤቶቹን አቀማመጥ በግርምት ማየት ጀመረች፡፡
‹‹እነዚህ የኤሌክትሪክ ገመዶች የሚሰሩ ናቸው?›› ማህሌት በአጠና የተቀሰቱትን ገመዶች እያየች ጠየቀችኝ፡፡
‹‹የሚሰሩ ናቸው …… ሁሉም ቤት ቆጣሪ የለም ለዛ ነው፡፡ ከአንድ ቦታ ነው ስበን የምንጠቀመው!››
‹‹ዝናብ ሲዘንብ እንዴት ነው የምትንቀሳቀሱት? …… me even አሁን ራሱ በጣም ከብዶኛል!››
‹‹ያው ህይወትሽ ሲሆን ትለምጂዋለሽ! …… ምን አማራጭ አለን?››
‹‹ጎርፍ ምናምን የለም?›› ምህረት ጨዋታችንን ተቀላቀለች!
‹‹አንዳንዴ ይኖራል፡፡ ቤትም ይገባል፡፡ ተኝተሸ ከሆነ ደግሞ ልትበሰብሺም ትችያለሽ፡፡ …… ግን ያው ደግሞ ያልፋል፡፡››
ማህሌት ድክም እያላት ስለነበር በእጇትከሻዬን ተደግፋ መሄድ ጀመረች፡፡ በጣም ዳገታማ ሲሆንና ሲከብዳቸው ቀደም ብለን እየወጣን እጃችንን እንሰጣቸውና እየታገሉ ይወጣሉ፡፡ ወደ ተራራው ከፍ እያልንና ከቤቶቹ እየራቅን ስንመጣ ትንሽ እንድናርፍ ጠየቁን፡፡ አብዱኬ እየዞረ ሁሉንም ያበረታታቸዋል፡፡ ነቃ እንዲሉ እየዞረ ጀርባቸውን አሸት አሸት ያደርጋቸዋል፡፡ ትንሽ አርፈው ጉዟችንን ቀጠልን፡፡ በመጨረሻም የተራራው ጫፍ ላይ ደረስን፡፡ በጣም ደስ ብሏቸዋል፡፡ትንሽ አረፍ እንዳልን አንዱ ወንድ ከመፅሀፍ ቅዱስ እየጠቀሰ ትንሽ አስተማረ፡፡ ሀሳቤ ሌላ ቦታ ስለነበረ ምን እንዳለ አልሰማሁትም፡፡ ቦታው ስለሚያምር ሁላችንም በአንድነት በምህረት ስልክ ሰልፊ ተነሳን፡፡
ወደ ታች መውረድ ስንጀምር ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ተኩል ሆኖ ስለነበር ሰፈራችን የተለመደ ግርግሯን ጀምራለች፡፡ የውሀ ወረፋ ለመያዝ ቢጫ ጀሪካን ይዘው ወደ ታች የሚሮጡ ህፃናት …… በየቤቱ በር ላይ በቁምጣ ቆመው ፀሀይ የሚሞቁ ወጣቶች …… ከታች ውሀ ተሸክመው ዳገቱን የሚወጡ ሴቶችና ወንዶች …… ብዙ ትዕይንት ይስተዋላል፡፡
ማህሌት አይኗ በእንባ ሞልቶ ‹‹ሁሌም እንደዚህ ነው …… I mean ውሀም የላችሁም?›› አለችኝ፡፡
‹‹ታች ቦኖ አለ፡፡ ከዛ እንቀዳለን!››
‹‹ሁሌ ይኼን ዳገት መውጣት …… I don’t know ብቻ everything is abnormal!›› እንባዋ ፈሰሰ፡፡ አቅፌ ጠረግኩላት፡፡
‹‹you know what? I wanna see your home. ይቻላል?››
‹‹ቤታችንን …… እሺ!››
አብዱኬ ዳገቱን እስክንወርድ አንድ ጊዜ እንኳን ከእኔ ጋር አልነበረም፡፡ ልጆቹ ጨዋታው ስለተመቻቸው ከበው እየሰሙት እየቀደደላቸው ነው፡፡ እኔ፣ አቤላ፣ ማህሌት እና ምህረት ብቻ ተገንጥለን ወደ ቤት ሄድን፡፡ ወደ ቤታችን የምታስገባዋ ጠባብ ቁልቁለት ለእነማህሌት በጣም ፈተና ሆናባቸው ነበር፡፡
ቤት ስንደርስ ኢንቱዬ ድምፅ ሰምታ ብቅ ብላ አየችን፡፡ ፈገግ ብላ እየተመለከተቻቸው ‹‹እንዴ ጥቁር እንግዳ!›› አለች፡፡
በተራ በተራ እየሳሙ ተዋወቋት፡፡ ባለአንድ ክፍሏ ጎጇችን ውስጥ ገብተው አረፍ ብለው መቃኘት ጀመሩ፡፡ እማዬ ስላመማት ከመኝታዋ አልተነሳችም፡፡ ኢንቱዬ የሚቀመስ ነገር ለማዘጋጀት መንደፋደፍ ጀመረች፡፡ ወዲያው ምህረት ‹‹በቃ …… እንድረስባቸው!›› ብላ ተነሳች፡፡ ኢንቱዬ የሆነ ነገር እንዲቀምሱ ብትለምናቸውም በእጄ አላሉም፡፡ ከቤታችን ወጥተን ዋናውን መንገድ እንደያዝን የጥያቄ ናዳ ያዘንቡብኝ ጀመሩ፡፡
‹‹ኪችን የት ትጠቀማላችሁ?››
‹‹ሻወር የት ትወስዳላችሁ?››
‹‹ያለ አልጋ እንዴት ትተኛላችሁ?
ብዙ ብዙ ለእነሱ ውስብስብ የሆኑባቸውን ጥያቄዎች እየጠየቁኝ መለስኩላቸው፡፡
ከተራራው ወርደን መኪናዎቻቸው ወደቆሙበት ቦታ ስንደርስ ጁስ ከመኪና አውጥተው እየተከፋፈሉ ነበር፡፡ አብዱኬ ቺፕሱንም ጁሱንም እየዞረ ያከፋፍላል፡፡ ተቀላቅለናቸው ጁሳችንን መጠጣት ጀመርን፡፡
‹‹አብዱኬ ግን የሌለ ፈታ ያልክ ሰው ነህ ከምር …… can I get your number …… please?›› አለች ማህሌት ስልኳን እየሰጠችው!
‹‹ስልኬን ማለትሽ ነዋ …… ምን ጣጣ አለው ኧረ ያዥው ……›› ቁጥሩን ፃፈላት፡፡
ትንሽ እረፍት ከወሰዱ በኋላ ለመስተንግዶው ከልብ አመስግነውን ሄዱ፡፡
እኔና አብዱኬ ቦኖው ጋ ሄደን ከወገብ በላይ እና እግራችንን ተጣጥበን ወደ ቤት ተመለስን፡፡ ወደ ቤት ስገባ ኢንቱን መሬት ላይ ስትንከባለል አገኘኋት፡፡ ‹‹ኢንቱ!!!!!!›› እየሮጥኩ ተንበር
777 views15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 22:37:21 ያረብ ሀላል
.
.
.
ዱሀ
1.0K views19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 09:57:14 ተረጋጋሁ፡፡ ወደ ሳጥኑ ስመለከት የኢንቱ ማስታወሻ ደብተር በቦታው ተሰድሯል፡፡ መርፌ ቁልፌን አውጥቼ ማስታወሻ ደብተሩን ከፈትኩና ባለፈው ያቆምኩበት ቦታ ላይ ገለጥኩ፡፡ እነኢንቱ ሲመጡ እጅ ከፍንጅ እንዳልያዝ በሩን ከውስጥ ጠርቅሜ ንባቤን ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… የህይወት ሚዛን ይገርመኛል፡፡ አንዳንዱ ጋር ፍካቷ ፅልመት የለውም፡፡ ለአንዳንዱ ደግሞ አጠለሻሸቷን ብርሀን አይቀርበውም፡፡ የስራ ቦታዬ አካባቢ ተቀጥረው የሚሰሩ ብዙ ሴቶች አሉ፡፡ ትልቁ ምኞታቸው ምን እንደሆነ ታውቃለህ? አንዱን ቦስ ማግባት! ከፈለገ ሁለተኛም ሆነው ይሁን ብቻ በምንም መንገድ ሀብታም ወንድ ማግባት ነው የሚፈልጉት! እሱም ካልሆነላቸው ደግሞ ባለፈው እንደነገርኩህ የአንዱ ቅምጥ ሆነው መቀለብ! …… በቃ ይኸው ነው ምኞታቸው! ቸግሯቸው ምናምን እንዳይመስልህ! በስርዓቱ ራሱን የቻለ ቤተሰብ ያላቸው ልጆች ናቸው፡፡ ግን ገንዘብ በጣም ይወዳሉ፡፡ ጋብዛቸው እንጂ የትም ይኼዳሉ፡፡ በቃ ምን ልበልህ ከመብላትና ከመጠጣት ውጪ ሌላ ስራ የላቸውም፡፡ ቅዳሜ ቅዳሜ ደግሞ በየሺሻ ቤቱ ከአንዱ ቦስ ጋር ቀንጣሽ ሆነው ይኼዳሉ፡፡ አንዷ የሚያስፈርሻት አንድ ቦስ ካገኘች ስፖንሰር አለ ተባብለው ይጠራሩና አንዱን ቦስ ከበው ሲያሳስቁ ያመሻሉ፡፡ እና በዚህ ደግሞ በጣም ደስተኛ ናቸው፡፡ የእነሱ ሲገርመኝ አሁን ደግሞ እኔ ላይ ዞረውብኛል፡፡ ቦስሽን ለምን አትመቻቺውም ብለው መቆሚያ መቀመጫ አሳጥተውኛል፡፡ ቢጨንቀኝ ባለፈው በጣም ተናገርኳቸው፡፡ አሁን ስራቸው ሁሉ ተሰብስበው እኔን ማማት ሆኗል፡፡ ከአንድ ጓደኛዬ ውጪ ሌሎቹ አያናግሩኝም፡፡ አንዳንዴ ሆን ብለው ስራ ሊያበላሹብኝ ይሞክራሉ፡፡ በስንቱ እንደምፈተን አላውቅም፡፡ አሁን አሁን ስራ እንኳን የምሄደው በጣም እየቀፈፈኝ ነው፡፡››
ገለጥኩት …… በሌላ ቀን የተፃፈ ፅሁፍ አገኘሁ፡፡
‹‹ኢቦ የእማዬ የእግር ህመም እየባሰባት ነው፡፡ ባለፈው ራስ ደስታ ሆስፒታል ይዣት ሄጄ ነበር፡፡ ምርመራ አድርጋለች፡፡ እኔን ግን ጭንቀት ውርር እያደረገኝ ነው፡፡ አንዱን ስል አንዱ ይመጣል፡፡ ከጓደኛዬ ያስሚን ጋር ስናወራ እሷም እየጨነቃት እንደሆነ ነገረችኝ፡፡ ኢስላማዊ ትምህርት ብንማር እንረጋጋለን …… ተስፋ አንቆርጥም አለች፡፡ ያው ኢቦዬ እኛ ቤት ሙስሊም ከመሆናችን ውጪ በስርዓቱ ሀይማኖታችንን እየተማርን እንዳላደግን ታውቃለህ፡፡ እኔ እንኳን አያታችን ሳይሞቱ በፊት ቢያንስ ቁርዓን አንዴ አስከትመውኝ ነበር፡፡ አሁን ግን ሳይጠፋኝ አይቀርም፡፡ ያስሚን ትንሽ ቀርታለች፡፡ ከዛ አንድ ኢማን የሚባል የኢስላማዊ ትምህርትና የአረብኛ ቋንቋ ማዕከል ማስታወቂያ እንዳየች ነግራኝ እዚያ ለመመዝገብ ተስማማን፡፡ እሷም ሰፈሯ ወደ ገመቹ ስለሆነ ቅዳሜ ከስራ መልስ ቤተል ያለው ቅርንጫፍ ለመመዝገብ ሄድን፡፡ ማዕከሉ ያለው የመስጂዱ የመጨረሻ ፎቅ ላይ ነበር፡፡ እዛ ስንገባ ብዙ ሴቶችና ጥቂት ወንዶች ነበሩ፡፡ ከእነርሱ ውስጥ ደግሞ ድሮ ትምህርት ቤት ስማር የማውቃቸውን የሀብታም ልጆች አየሁ፡፡ ሁሉም አምሮባቸዋል፡፡ ከእነሱ ጋር ሰላም ተባብለን የመመዝገቢያ ቦታውን አሳዩን፡፡ ትምህርቱ የሳምንት ሙሉ እንዲሁም የቅዳሜናእሁድ አማራጭ ፈረቃ አለው፡፡ የሚመዘግበው ልጅ ቁርዓን አክትመን እንደሆነ ጠየቀን፡፡ ሁለታችንም እንዳከተምን ስንነግረው ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ማብራራት ጀመረ፡፡ ኢቦዬ …… ለመማር የሚያስፈልገውን ብር ስንሰማ ሁለታችንም ደነገጥን፡፡ ለመደበኛው ሁለትሺህ ምናምን ብር …… እኛ መማር ለፈለግነው የሳምንት መጨረሻ ትምህርት ደግሞ ስድስት መቶ ምናምን ብር! በእርግጥ ክፍያው የሴሚስተር ክፍያ ነው ግን ቅድሚያ ሙሉ ለሙሉ መክፈል ይኖርብሀል፡፡ ያስሚን ክፍያውን ስትሰማ እንባ አቀረረች፡፡ የሚመዘግበው ልጅ አቅማችን እንደማይችል ተረድቶ ነው መሰለኝ በየወሩ ሁለት መቶ ሀምሳ ብር እንድትከፍሉ አስተዳደሩን ላናግርላችሁ አለን፡፡ ልጁን አመስግነን ሹልክ ብለን ወጣን፡፡ ደረጃውን ስንወርድ ያስሚን እየተንሰቀሰቀች ማልቀስ ጀመረች፡፡ በሶስት ሺህ ብር ደሞዝ ቤተሰብ እያስተዳደርን በወር ሁለት መቶ ሀምሳ ብር የመክፈል አቅም ፈፅሞ የለንም፡፡ ቤተሰባችንን ከወር ወር አብቃቅተን ለማብላት ምሳ እየዘለልን በባዶ ሆድ የምናሳልፍ ነን፡፡ ከዚያ እንደወጣን ያስሚን እዚያው አካባቢ ሌላ ማስታወቂያ አይታ ስለነበር አንድ ህንፃ ላይ ወዳለ የቁርዓን ትምህርት ቤት ሄድን፡፡ እዚህ ደግሞ ቁርዓን ብቻ ነበር የሚያስተምሩት፡፡ እኛ ነፍሳችንን ለማረጋጋት ቁርዓን ማንበቡንም ቢሆን ድጋሚ ለመማር ፈልገን ነበር፡፡ ግን እዚህም ከቅድሙ የባሰ ነበር፡፡ ለሁለት ወር ሁለት ሺህ ምናምን ብር ጠየቁን፡፡ አንገታችንን ደፍተን ከህንፃው ወጣን፡፡
ያስሚን እያለቀሰች ‹‹በቃ ገንዘብ ከሌለን መቅራት አንችልም?›› አለችኝ፡፡ ታውቃለህ ኢቦ ሁሉም ነገር ፍትሀዊ አይመስልም፡፡ ሁሉም ገንዘብ ለማግበስበስ የሚሮጥ እንጂ እንደድሮ ኡስታዙ እየተቸገረ ተማሪውን በነፃ ማስተማር አይታሰብም፡፡ ሀብታም ካልሆንክ ሀይማኖትህን እንኳን በአግባቡ መማር አትችልም፡፡ የቲሞችስ የተቸገሩ ሰዎችስ እንዴት ይሆናሉ ብሎ የሚያስብ አንድም የለም፡፡ ይኼኔ እነዚህ መድረሳዎች ሲቋቋሙ ስንቱ ድሀ ልጁ የሚማርበት መስሎት ምግቡን ዘሎ ያለውን ዘርግቷል፡፡ ብቻ አለም ፍትሀዊ አይደለችም፡፡ ጊዜው ደግሞ በጣም ከፍቷል፡፡››
ኢንቱዬ ምሳ እንደማትበላ የፃፈችውን እያየሁ መንሰቅሰቅ ጀመርኩ፡፡ ሌላስ ስንት ያልተፃፈ መከራ አሳልፋ ይሆን ስል አሰብኩ፡፡ ቀጣዩን ገፅ ከፍቼ ላነብ ስል ከውጪ የኢንቱን ድምፅ ሰማሁ፡፡ ፈጠን ብዬ ደብተሩን ወደ ቦታው መልሼ በሩን ከፈትኩ፡፡ ኢንቱ ወደ ቤት ስትገባ ፊቷ ጥቁር ብሎ ነበር፡፡
‹‹ምነው ምን ሆነሻል?››
‹‹ምንም አልሆንኩም …… ትንሽ ደክሞኝ ነው፡፡›› አለችና ጋደም አለች፡፡
በልቤ ዛሬም ምሳ አልበላች ይሆን እያልኩ አስባለሁ፡፡ መፅሀፌን ከፍቼ ኢንቱዬን በስስት እያየሁ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
.
ይቀጥላል …
1.2K views06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 09:56:49 ከተራራው ላይ
ክፍል አምስት
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹ሰላም ለአንጀትሽ፣ የኔን ሆድ ሊሞላ ሲታጠፍ ለዋለ፣
ሰላም ለከንፈርሽ፣ ወዜን ለመጠበቅ ንጣት ለተኳለ!
ሰላም አለሜዋ!››
***
ከቀናት በኋላ ከማህሌት ጋር ቤተ-መፅሀፍት ተገናኘን፡፡ ለማውራት እንዲመቸን በሚል ወደ መኪናዋ ሄድን፡፡ እኔ፣ አቤላ፣ ማህሌት እና ጓደኛዋ ነበርን፡፡
ማህሌት ከእርሷ ጋር ጋቢና ያለችውን ጓደኛዋን ትከሻ እየደባበሰች ‹‹Okay አብርሽ …… እሷ ምህረት ትባላለች፡፡ ያልኩህ ህብረት ላይ የentertainment sector leader ናት፡፡ So እስኪ ስለ ተራራው ምናምን አስረዳት፡፡›› አለች፡፡ ምህረት ዝምተኛ ትመስላለች፡፡ ባለኮፍያ ሹራብና ረዥም ቀሚስ ለብሳለች፡፡
‹‹ያው ተራራ ነው ያላችሁኝ እኮ አይደል …… አንፎን አታውቁትም? …… እዛ ተራራ ላይ ነው የእኔም ቤት …… ቅርብ ስላላችሁኝ ብዬ ነው፡፡›› አልኩና ስለ ሰፈራችን አብራራሁላቸው፡፡ እነርሱ ሰፈሩን ከነመፈጠሩም አያውቁትም፡፡ ግራ ቢገባኝ ‹‹ሁላችሁም ህብረቱ ውስጥ ያላችሁት የቤተል ልጆች ብቻ ናችሁ እንዴ?›› አልኳቸው፡፡
‹‹በብዛት አዎ! ግን ወደ መሀንዲስ አካባቢም ልጆች አሉ፡፡ እና ……. ከዚህ ውሀ ይዘን ከምንመጣ እዛ ብታዘጋጅልንስ?›› አለች ምህረት!
‹‹ችግር የለውም አንድ ጀሪካን ባስቀዳ ይበቃችኋላ?››
ሁለቱም ከት ብለው ሳቁ፡፡ ያሳቃቸው ነገር አልገባኝም፡፡ ስቀው ሲያባሩ ምህረት ከኪሷ ብር እያወጣች ‹‹አንተ ቁምነገር ብቻ ሳይሆን ቀልድም ጎበዝ ነህ፡፡ እንካ የታሸገ ውሀ አንድ አራት ደርዘን ገዝተህ አዘጋጅና ጠዋት በዛው ስናልፍ እናነሳዋለን፡፡ መጨረሻ ላይ የሚያስፈልገውን ጁሱን ምናምን እኛ ከዚህ ይዘን እንመጣለን፡፡›› አለችኝ፡፡ ብሩን ተቀብያት ምህረት ስለ ህብረታቸው አንዳንድ ተጨማሪ ማብራሪያዎችን ከነገረችን በኋላ እኔና አቤላ ሰዓታችንን ለመጠቀም ወደ ንባብ ተመለስን፡፡ ከመኪናው እንደወጣን ‹‹አቤል አንተም እንዳትቀር እሺ!›› አለች ምህረት!
ፈገግ ብሎ ‹‹እሺ እሞክራለሁ!›› አለ፡፡
‹‹ኢባ ታቃለሀ ግን እነዚህ ሁለት ቺኮች …… ሌሎች ጀለሶቻቸውንም ሲመጡ አይተሀቸው ከሆነ ሁሌም ቀሚስ ነው የሚለብሱት!››
ለማስታወስ እየሞከርኩ ‹‹እኔ ልብ ብያቸው አላውቅም! …… ነው እንዴ?›› አልኩ፡፡
ወደ ቤተ-መፅሀፍቱ ተመልሰን ስናነብ ካመሸን በኋላ አብዱኬ መጣ፡፡ የተለመደችዋን ፓስቲ ከበላን በኋላ ከቤተ-መፅሀፍቱ ወጣን፡፡
አቤላን ስንሰናበተው አብዱኬ ‹‹ስሚ ግን አቤላ እናንተ ሰፈር ሀንግ ምናምን የለም እንዴ? ብቻሽን ስትገቢ ማንም አይጎራበጥሽም?›› አለው፡፡
‹‹ሀንግ መትተው መፅሀፍ ሊቀሙኝ ነው? ባክህ ሰላም ተባብለን ነው የምንተላለፈው …… የሚመቱትን ያውቃሉ፡፡››
‹‹ለነገሩ ልክ ነሽ አባቴ! ሌባ ራሱ የሚሰርቀውን ይለያል፡፡ ድሀን መዝረፍ የማይሰለቸው ሀብታም ብቻ ነው! ሊያውም በህጋዊ መንገድ!›› አብዱኬ የልቤን ስለተናገረልኝ ደስ አለኝ፡፡
ወደ ሰፈር እየሄድን አለምባንክ ስንደርስ ኢንቱ ደወለች፡፡
‹‹ወዬ ኢንቱ ……››
‹‹ኢቦዬ ቤት ነኝ እሺ! …… እንዳትጠብቁኝ ብዬ ነው፡፡ እየመጣችሁ ነው?››
‹‹አዎ አለምባንክ ደርሰናል፡፡››
ተሰነባብተን ስልኩ ተዘጋ፡፡ ስልኬን ኪሴ ውስጥ እየከተትኩ ‹‹አብዱኬ …… ስራውን መጀመር እፈልጋለሁ!›› አልኩት፡፡
‹‹አባቴ …… አባቴ …… በቃ አሁን ነቃሽ! ይኼ ነው ወንድነት!›› ትከሻዬን አቅፎ ነቀነቀኝ፡፡
‹‹እና እንዴት ነው የምጀምረው?››
‹‹ምንም ጣጣ የለውም ነገርኩሽ እኮ በቃ ስልኮቹን እያመጣሁ አስረክብሻለሁ፡፡ እነሱ የሚፈልጉበትን ነግሬሽ አንቺ ደግሞ ትርፍሽን ጨምረሽበት ዋጋ ታወጪለታለሽ! ገባሻ! ስትሸጪው ደግሞ በሰው በሰው ነው ተጠንቅቀሽ ማለት ነው፡፡ ደሞ አትፍሪ ትለምጂዋለሽ!››
‹‹እና መች ታመጣለህ?››
‹‹ዛሬ የገባ ስልክ ሳይኖር አይቀርም …… ካለ ነገ አመጣልሻለሁ፡፡››
ለጥቂት ደቂቃዎች በመካከላችን ዝምታ ነገሰ፡፡
‹‹አብዱኬ ታውቃለህ …… ከኢንቱ ጋር አብረን እራት ከበላን ሳምንት አልፎናል፡፡ እራት ታቀርብና እኔ በልቻለሁ ብሉ ትላለች፡፡ ምን አስቀይምያት እንደሆነ አላውቅም! እኔ ደግሞ ገና እሷ አልበላም ስትል የምግብ ፍላጎቴ ራሱ ይቆለፋል፡፡››
አብዱኬ ትኩር ብሎ እየተመለከተኝ ‹‹ነይ እስኪ!›› አለና ባጃጅ ተራ ጋር ያለ አንድ ሱቅ ገብተን ዳቦ፣ ሰላጣ፣ ቲማቲም እና ሸንኩርት ገዛ፡፡
‹‹ዛሬ እኔ በግድ እንድትበላ ካላደረግኳት ታያለህ!›› አለኝ፡፡
ቤት ስንገባ ኢንቱዬ የእማዬን እግር እያሸች ነበር፡፡ አብዱኬ የያዘውን ፌስታል መሬት ላይ እያስቀመጠ ‹‹ኢንቱዬ ዛሬ ቆንጆ እራት ሀኪም አዞልኛል በናትሽ …… ይህቺን ሰላጣ ፏፏ አድርጊያትና እንፈወሰው!›› አላት፡፡
እየሳቀች ‹‹ምግብ የሚያዝ ሀኪም ጋር መሄድ ጀመርክ ደግሞ ……›› አለች፡፡
‹‹ቀልዴን መስሎሽ ነዋ!? ይኸው ሊያውም ሰላጣ ይኼን ያህል …… ሽንኩርት ይኼን ያህል ምናምን ብሎ ነዋ! …… ይኸው እዪው!›› ፌስታሉን ከፍቶ አሳያት፡፡
‹‹አንተ ምናባህ ነው …… መብላት ፈልገህ ነው ወይስ ሀኪም አዞልህ ነው? ምንድነው የምታለምጠው?››
‹‹በቃ ጓ አትበያ! አምሮኝ ነው ሰራ ሰራ አድርጊያትና እናጣጥመው!››
ተነስታ ጉድ ጉድ ማለት ጀመረች፡፡ እማዬ እየሳቀች‹‹በቃ የአብዱልከሪም ነገር አይሆንልሽማ!›› አለች፡፡
‹‹ይኼ ሸፋፋ …… እዛ ታክሲ ለታክሲ ሲንጠላጠል ቢያንስ በዚህ ልጠግነው ብዬ እኮ ነው፡፡ ልፅደቅበት እንጂ!›› ሳቀች! ደስ አለኝ፡፡
ኢንቱዬ ሰላጣውን ሰራርታ በዳቦ እና በእንጀራ አቀረበችው፡፡ መብላት ጀመርን፡፡ ኢንቱዬም ምንም ሳታቅማማ አብራን መብላት ጀመረች፡፡ በጣም ደስ አለኝ፡፡ እየደጋገምኩ አጎረስኳት፡፡
በልተን ጨርሰን እየተጫወትን ኢንቱዬ ቋቅ እንደማለት አላት፡፡ ትንሽ ቆይታ ማስመለስ ጀመረች፡፡ ሁላችንም ደነገጥን፡፡ እኔ የማደርገው ጠፍቶኝ ስወናበድ እማዬ ደረቷን እንድደግፋት ነገረችኝ፡፡ በቀኝ እጄ ደረቷን ደግፌ ይዣት ‹‹አይዞሽ …… አይዞሽ›› እላለሁ፡፡ በህይወቴ ኢንቱዬ እንዲህ ሲያማት ያየሁበት ቀን ትዝ አይለኝም፡፡ ከበላችው ውስጥ አንድም አልቀረም፡፡ ሙሉ በሙሉ ወጣ፡፡ ትውከቱ ጋብ ሲልላት ውሀ እንድንሰጣት ጠየቀች፡፡ ሳላስበው ከአይኔ የእንባ ዘለላዎች መውረድ ጀመሩ፡፡ አብዱኬ ተቀምጦ በቁጭት ጉልበቱን ይደበድባል፡፡
ቦታውን አፅድቼ መኝታችንን አነጣጠፍኩ፡፡ ኢንቱዬ ድክም ብላለች፡፡ እቅፌ ውስጥ ተኝታ ‹‹ምንም አልሆንኩም እሺ …… ምግቡ ስላልተስማማኝ ነው፡፡›› አለችኝ፡፡ በልቤ ወደ አምላኬ ፀለይኩ፡፡ ኢንቱዬ ምንም እንዳትሆንብኝ …… ለእርሷ የመጣ በሽታ ካለ ለእኔ እንዲያደርገው ለመንኩኝ፡፡
ጠዋቱን ኢንቱዬ ነቃ አለች፡፡ ቁርስ ዳቦ ገዝቼ የተለመደውን ዳቦ በሻይ አቀራረብኩ፡፡ ኢንቱዬ ቀስ እያለች ትንሽ በላች፡፡ እንደማታው እንዳይጣላት ፈርታለች፡፡ አላስመለሳትም፡፡ ደስ አለኝ፡፡ እኔ ቤቱን ማስተካከል ስጀምር ኢንቱዬ ማስታወሻ ደብተሯን ከፍታ መፃፍ ጀመረች፡፡
አብዱኬ ሲመጣ ኢንቱ ነቃ ብላለች፡፡ እየሳቀ ‹‹አንቺ የማታው እኔን ለማክሰር ነው እንዴ ምንሼ? ማታ ስትታዪ እኮ ተሰናባች ነበር የምትመስዪው!›› አለ፡፡
ኢንቱ ዛሬ እንድታርፍ ተስማምተን ወደ ትምህርት ቤት ልሄድ ከአብዱኬ ጋር ወጣን፡፡ ወደ ትምህርት ቤት ስሄድም ሆነ ትምህርት ቤት ውስጥ ቀኑን ሙሉ የማስበው ስለ ኢንቱ ነበር፡፡ ትምህርት እንዳለቀ ወደ ቤት ስከንፍ ተመለስኩ፡፡ ኢንቱዬና እማ አልነበሩም፡፡ ኢንቱ ጋር ስደውል ሰፈር እንደሆነችና ትንሽ ቆይታ እንደምትመጣ ነገረችኝ፡፡ ደህና መሆኗን ስሰማ
981 views06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 09:05:20 ያተረፍኩት የወንድም እህቶቼን ስቃይ እየሰማሁ ማልቀስን ብቻ ነው፡፡ አልደርስላችሁ ነገር እኔም ከሰጋጁ ተለምኖ ወር መዝለቂያ የሚሰፈርልኝ ደሀ ነኝ፡፡ ሰጋጁን ደግሞ አንድ ሁለት ቀን ገንዘብ ጠይቀነው በሶስተኛው ቀን ከደገምን ይሰለችብናል፡፡ ሁሉም ነፍሴ ነፍሴ እንጂ ወንድሜን እህቴን አይልም፡፡ በዚህ ጊዜ ኢማም ከመሆን በላይ ትልቅ መዓት የለም፡፡ አሁን እኔም የማላክመውን ህመም በመስማት ልቤ ከሚቆስል ኢማምነቴን ትቼ እብስ ማለት ይሻለኛል፡፡›› ነበር ያሉኝ! ክብሬን የማተርፍበት ጭላንጭል ተስፋ የነበረኝ እዚህ ነበር፡፡ ዛሬ እንደማይሆን አረጋገጥኩ፡፡ ያሉኝን ቢሉኝ …… ያደረጉትን ቢያደርጉ ችዬ መስራት እንዳለብኝ አመንኩ፡፡ አዎን የገሀዱን አለም እውነታ መቀበል አለብኝ፡፡ አማኝ ነኝ የሚለው ህዝብ ሂጃቧ ተገለጠ …… ገላዋ ታየ እያለ በቻለው መጠን ከፈጣሪ ጋር የማጠቋቆር ስራ ከመስራት በዘለለ ሌላ አይፈይድህም! ብትቸገር አይረዱህም! …… የተሳሳትክ ሲመስላቸው ግን በቻሉት መጠን አንተን ከፈጣሪ ጋር ለማጠቋቆር ይጣደፋሉ፡፡ ቢመርም እውነታው ይኼ ነው፡፡››
አይኖቼ በእንባ እንደራሱ በሌላ ቀን የተፃፈውን ማንበብ ጀመርኩ፡፡ በሁለቱ ፅሁፎች መሀከል ረዘም ያለ የጊዜ ልዩነት ነበረው፡፡
‹‹ኢቦዬ …… በጣም ተናድጃለሁ፡፡ ያ ቆሻሻ ሰውዬ እኮ እንደሳመኝ ለአባዬ ሰው ልኮ አስነገረው፡፡ ልጅህን ሳምኳት ብሎ አንገቱን ሊያስደፋው ሞከረ፡፡ ሰውዬው ለአባቴ ጓደኛ እንደነበር ነበር ያሰብኩት! ግን በአባቴ በጣም ይቀና እንደነበር ተረዳሁ፡፡ ሰው እንዴት ሙት ገድሎ ይፎክራል? አባዬ ረጋ ብሎ ሁሉንም ነገር ማወቁን ከነገረኝ በኋላ ድጋሚ እዮስያስ የሚባል የሰው ሰይጣን ጋር እንዳልሄድ አስጠነቀቀኝ፡፡ ሀኪም ቤት የሚባል ላይሄድ …… መድሀኒትም ላይወስድ ምሏል፡፡ ‹‹ከዚህ በኋላ እኔን ትተሽ ለወንድምሽ እና ለእናትሽ በአቅምሽ የምትችይውን አድርጊ፤ እሱን ማድረግሽ ለእኔ ከበቂም በላይ ነው፡፡›› አለኝ፡፡ ሌላ ምን አደራ እንዳለኝ ታውቃለህ? ‹‹ጓደኛ ስትይዢ መልካም ሰው ምረጪ! እኔ በመታመሜ በገዛ ጓደኞቼ ብዙ ገንዘቤን ተክጃለሁ፡፡›› አለኝ፡፡ አሁን አባዬን አይኔ እያየ ሲሞት ከማየት ውጪ አማራጭ የለኝም፡፡ ለመንኩት ለመንኩት ግን ሊሳካልኝ አልቻለም፡፡ አሁን በሁሉም ነገር ተስፋ እየቆረጥኩ ነው፡፡ ሩጫውም ከአቅሜ በላይ እየሆነ ነው፡፡››
ገለጥኩት፡፡ ስለአባዬ መሞት የፃፈችውን አገኘሁ፡፡ የማውቀውን ማንበብ ስላልፈለግኩ ገለጥ ገለጥ እያደረግኩ ከለቅሶው ከሁለት ወር በኋላ የፃፈችውን ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ …… ለአንተ ብዬ ባልኖር ህይወት ትቀፋለች፡፡ አንዳንዴ የሰዎች መገልገያ ከመሆን የዘለለ ዋጋ እንደሌለኝ ይሰማኛል፡፡ አሰሪዬ ሲለው እያሳሳቀ …… ሲለውም በፈጣጣው ደስ ያለውን የሰውነቴን ክፍል ይነካካል፡፡ አናቱ ላይ የወጣበት ቀን ደግሞ ሙሉ ወጪሽን ሸፍኜ ካላስቀመጥኩሽ ይለኛል፡፡ ይኼ ለሽርሙጥና የተሰጠው አዲሱ ስያሜ ይመስለኛል፡፡ በባለትዳር ነጋዴዎች ዘንድ ደግሞ በጣም እየተለመደ ነው፡፡ ከትዳራቸው ውጪ ወጣት ሴቶችን በቅምጥነት መያዝ ማለት ነው፡፡ ቤት ይከራዩላቸዋል …… ሙሉ ወጪያቸውን ይሸፍኑላቸዋል …… ሲያምራቸው ብቅ እያሉ ደግሞ ይተኟቸዋል፡፡ እኔንም እንደዛው እንድሆን ብዙ ሰው ይጠይቀኛል፡፡ ግን እናንተን ላልጠቅምበት ራሴን ማጣት አልፈለግኩም፡፡ አሰሪዬን ድንገት ተናድጄ እንኳን ሰውነቴን እንዳይነካኝ ብናገረው ከስራ ያባረኛል፡፡ ያለ ተያዥ መቅጠሩን እንደትልቅ ውለታ ይዘከዝክልኛል፡፡ ያለኝ አማራጭ ልቤ እያረረ ጥርሴን ማግጠጥ ነው፡፡ በሳቅ እያባበሉ ነገሮችን ማለፍ! እስከመች እንደሆነ አላውቅም! …… ግን ህይወት ከብዳኛለች፡፡››
ቻርጅ እያደረገች የነበረችው ስልኬ ተንጫረረች፡፡ ደብተሩን ዘግቼ ቦታው መለስኩና እንባዬን እያበስኩ ወደ ስልኬ ሄድኩ፡፡ ማህሌት ነበረች፡፡ አነሳሁት፡፡
እየተፍለቀለቀች ‹‹hey አብርሽ …… እንዴት ነህ?›› አለች፡፡
‹‹አለሁ ሰላም ነሽ?››
‹‹አለሁ እደውላለሁ ብዬ ጠፋኋ?! Sorry በጣም!››
‹‹ኧረ ችግር የለውም!››
‹‹ደሞ ላይብረሪም ጠፋህ!››
‹‹ኧረ አለሁ አለመገጣጠም ነው፡፡››
‹‹So let me come to the point ምን መሰለህ hike ማድረግ አስበን ነበር ያው ነቃ ለማለትም ትንሽ መዝናናት አሪፍ ነው፡፡ እና ቅርብ የምታውቀው ተራራ አለ እንዴ?››
ጥያቄዋ አስገርሞኛል፡፡ እኛ ህይወት ተራራ ሆናብን ተራራ ተጠግተን እንኖራለን፤ እነርሱ ለመዝናናት ተራራ ይፈልጋሉ፡፡
‹‹ማለት? ተራራ ስትወጡ ትዝናናላችሁ? ማለቴ …… እሱን ነው ነቃ እንዲያደርገን ያልሽው?›› ሳቋን ለቀቀችው፡፡
‹‹stop joking …… ባይሆን የምታውቀው ካለ ንገረኝ!››
‹‹አለ የእኛ ቤት ራሱ ተራራ ላይ ነው፡፡ የኛን ሰፈር ተራራ ትወጣላችኋ በቃ!››
‹‹ደስ ይላል በቃ this Sunday እንወጣለና! የሚያስፈልጉ ነገሮችን ላይብረሪ ስትመጣ ደውልልኝና እናወራለን፡፡››
የማህሌት ጉዳይ እያስገረመኝ ስልኬን ቻርጅ ሰክቼ ስዞር ኢንቱ ከጀርባዬ ቆማ እየተመለከተችኝ ነበር፡፡ በዚህ ሰሞን ለምን እንደሆነ ባላውቅም ቶሎ ከስራ ትመለሳለች፡፡ ከማህሌት ጋር ያወራነውን ሰምታለች መሰለኝ በስለላ አይን ቃኘችኝ፡፡ ተነስቼ ሳምኳት፡፡ ኮስተር ብላ ‹‹ማናት?›› አለችኝ፡፡ አስረዳኋት፡፡ ፈገግ አለች፡፡ ደስ አለኝ፡፡ ፈገግታዋ ጥንካሬዬ ነው፡፡
እያነበብኩ እራት ሰዓት ሲደርስ ኢንቱ ምግብ አቀራረበች፡፡ እማዬ ሰፈር ጓደኞቿ ቤት አምሽታ መምጣቷ ነበር፡፡ ምግቡ እንደበፊቱ ለሶስት የሚበቃ አልነበረም፡፡
ኢንቱ አቀራርባ ስትጨርስ ‹‹እኔ በልቻለሁ እናንተ ብሉ!›› አለች፡፡
በልቻለሁ ማለቷ ገርሞኝ ‹‹እንዴ መች ነው የበላሽው ቅድም አይደል እንዴ የመጣሽው?›› አልኩ፡፡
‹‹አይ ቅድም ስራ ቦታ ምግብ መጥቶ በልተናል፡፡ ደሞ ጣፋጭ ስለነበር …… የሌለ ነው የዘጋኝ!››
እማዬም ትንሽ በልታ በቃኝ አለች፡፡ ኢንቱዬ በግድ አንድ ጎረሰችልኝ፡፡ ደስ አለኝ፡፡
መኝታችንን አነጣጥፈን ጋደም እንዳልን ስለ ኢንቱዬ ህይወት ማሰብ ጀመርኩ፡፡ በዚሁ ከቀጠልኩ ገና ሰባት አመታትን ከጫንቃዋ ላይ ላልወርድ መሆኑን ሳስብ አንገፈገፈኝ፡፡ አብዱኬ በሚለኝ መንገድ ተጉዤ እሷን ባላሳርፋት እንኳን ልደግፋት ወሰንኩ፡፡
.
ይቀጥላል
1.1K views06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 09:04:51 ከተራራው ላይ
ክፍል አራት
(ፉአድ ሙና)
.
‹‹መልካም ሰው አውቃለሁ፣ አያንስም ለራሱ፣
ያንቺ ያስገረመኝ ካንድ ነብስሽ ቀድሞ ለነብሴ መድረሱ፡፡
መልዓክ ነሽ አይደለ?››
***
ማህሌት አቀርቅራ በስሱ ተደግፋው የቆመችውን የደረጃ መደገፊያ ብረት በጣቶቿ በስልት እየመታች እየጠበቀችኝ ነበር፡፡ አጠገቧ ደርሼ ስቆም ፈገግ አለች፡፡
‹‹okay አብርሽ Thank you ስለመጣህ ……››
‹‹ምንም አይደል››
‹‹Okay ምን መሰለህ የሆነ ህብረት ነበረን basically ሀይማኖታዊ ነው ግን just we have also fellowships, fun, social responsibility and educational sections እና አንተ ደግሞ like ቀለሜ ስለሆንክና ቁምነገረኛም ስለመሰልከኝ join እንድታደርገን ልጠይቅህ ነበር፡፡››
‹‹ማለት …… እኔ እንደዚህ አይነት ነገር ላይ ተሳትፌ አላውቅም እና ……… ምን እንደሆነ ያልሽው አልገባኝም››
‹‹okay the main point is በአንድነት ሆነን በስርዓቱ መዝናናት፣ በአቅማችን ልክ ማህበረሰቡን ማገዝ እና ደግሞ እርስ በእርሳችን በትምህርት መደጋገፍ …… አሁን ገባህ?››
እውነቱን ለመናገር የተናገረችው ነገር ምንም አልገባኝም ግን በድጋሚ አልገባኝም ማለት ደበረኝ፡፡ ሳቅማማ ከፊቴ ላይ አነበበች መሰል ‹‹ችግር የለውም through a time በደንብ ይገባሀል like ቀጣይ ስንሰበሰብ እጠራሀለሁ፡፡ am sure ትወደዋለህ!›› አለችኝ፡፡ ትህትናዋ እንቢ ለማለት የሚያስችል አልነበረም፡፡
‹‹እሺ በቃ …… እንዳልሽው ይሁና!››
እየተፍለቀለቀች ‹‹thank you …›› አለችና ተጠመጠመችብኝ፡፡ ፈገግታዋ ደስ ይላል፡፡ ጉንጬን ስማ ተሰናበተችኝ፡፡
ወደ ወንበሬ ስመለስ አብዱኬና አቤላ በጥያቄ አይን አፈጠጡብኝ፡፡
‹‹ምንድነው?›› አስተያየታቸው አስገርሞኛል፡፡
‹‹ምን አለችህ?›› አብዱኬ ፈጠነ፡፡
‹‹ኧረ ኳስ በመሬት …… የሆነ ቡድን ምናምን ላይ እንድሳተፍ ልትጠይቀኝ ነው፡፡››
‹‹በቃ አባቴ ዱዓዬ ሰርቷል ማለት ነው፡፡ ሰሞኑን ጀብኜብሽ ነበር …… ጌታዬ ይሄን ልጅ እውቀት ሰጥተህ አጠቃቀሙን አትንሳው …… መልክ ሰጥተህ የማንፀባረቂያ ጥበቡን አትከልክለው …… እያልኩ …… በቃ ምን ልበልሽ ራሱን ነው ያወረደው ራሱን!››
‹‹ኧረ እኔ ምንም አላልኳትም ራሷ ነች የመጣችው ……››
‹‹እኮ አንተማ ፈዘህ ፈዘህ how to መጀንጀን የሚለውን እንኳን ስለማታርፈው ቀጥታ delivery ነው ‘ሚባለው? አዎ እንደሱ ነው ፈጣሪ ያመጣልህ!››
የአብዱኬ እንግሊዘኛ አጠቃቀም ፈገግ አስባለን፡፡
አቤል የአብዱኬን ትከሻ እየመታ ‹‹አባቴ ዛሬ ነክሰሻል መሰለኝ እንግሊዘኛ ሁሉ እየፈሰሰልሽ ነው፡፡›› አለ፡፡
በማህሌት ምክንያት በየመሀሉ ሲያዝጉኝ ከቆዩ በኋላ ሰዓቱ በጣም ስለገፋ ከቤተ-መፅሀፍቱ ወጣን፡፡ አቤላን አሰናብተን ወደ ሰፈር መሄድ እንደጀመርን ጠዋት ላይ አብዱኬ ያለው ትዝ አለኝ፡፡
‹‹አብዱኬ …… ስለ ኢንቱ ምን ማድረግ የምችል ይመስልሀል?›› አልኩት፡፡
‹‹አሁን እኮ ትልቅ ነህ …… ገባሀ …… እሷ ከትምሮ እንዳትዘናጋ ብላ አይደል አትወርክ የምትልህ? እሷ ሳትባትት የሆነ አየር በአየር ነገር መጀመር ነው ያለብህ!››
‹‹የምን አየር በአየር ነው?››
‹‹ይኸውልሽ እንደውም እኛጋ …… እዛ ተራ ጀለሶች አሉ እና አሪፍ አሪፍ ስልክ ያነሳሉ፡፡ እና እንደወረደ በትኩሱ ላንቺ እንዲመጣልሽ ማድረግ እችላለሁ፡፡ ከዛ አንቺ እዚህ ላሉ ቅባቴዎች በደንብ አትርፈሽ ትሸጪዋለሽ! ከትምሮሽ ጋር ምንም አይጋጭም …… ኢንቱም አትባንንም!››
‹‹ማለት የተሰረቀ ስልክ ተቀቡ ልሆን?››
‹‹እንደዛ አታስበው …… የሚመጡልሽ ስልኮች በጣም ውድ ውድ ናቸው፡፡ የተበሉትም …… የሚበሉትም ከቁሌት ላይ ነው፡፡ ሀብታም ጋር ያለው መላ ደግሞ የኛ መላ ነው፡፡ የኛን ገንዘብ ሊሰጠን ስለማይፈልግ እኛ እንቀበለዋለን፡፡ አንተም ድርሻህን ትወስዳለህ፡፡ይኼ ነው ስራው!››
‹‹አንተ ትሰርቃለህ እንዴ?››
‹‹እኔማ በየትኛው ጊዜዬ …… ጀለሶች ናቸው፡፡››
‹‹የተሰረቀው ሰው ሀብታም መሆኑን እንዴት ታውቃላችሁ?››
‹‹በጣም ውድ ስልኮች ናቸው የሚበሉት …… የሀያ ሺህ ብር ስልክ የሚይዝ ደሀ አይኖርም ገባሻ! ካለ ደግሞ መበላት ሲያንሰው ነው!››
በውስጤ ኢንቱ ልታውቅበት የምትችልበትን መንገድ ማሰላሰል ጀመርኩ፡፡
‹‹እኔ እኮ የኢንቱ ነገር ነው የሚያሳስበኝ!››
‹‹አቦ አትንቦቅቦቅ ካልነገርካት እንዴት ታውቃለች?! ለመላውም ቢሆን መንገድ አለው፡፡ አታስቢ!››
አስቤበት ልነግረው ተስማማን፡፡
ወደ ቤት ስገባ ኢንቱ መኝታችንን አነጣጥፋ …… እራት አቅርባ እየጠበቀችኝ ነበር፡፡ እማዬ ልክ ስገባ ፈገግ አለችና ‹‹ይኸው ንጉስሽ መጣ! አንተ ሳትመጣ ራት አንበላም ብላ ስትቀጣኝ አየህ አይደል?›› አለች፡፡
ኢንቱዬ እየሳቀች ‹‹እኔ አልበላም አልኩ እንጂ አንቺ አትብዪ አላልኩም፡፡›› አለች፡፡
‹‹ኢቦዬ አንተ እድለኛ ነህ ሁለት እናት ነው ያለህ!›› አለች እማ!
እራታችንን በልተን መኝታ ውስጥ እንደገባን ኢንቱዬ ‹‹ፈተና ምን ያህል ጊዜ ቀረው?›› አለችኝ፡፡
‹‹ሶስት ወር መሰለኝ …… ምነው?››
ጣራ ጣራውን እያየች ‹‹ምንም …… ለማወቅ ብዬ ነዋ! እና ዝግጅትስ እንዴት እየሆነልህ ነው?›› አለችኝ፡፡
‹‹አሪፍ ነው!›› ብያት ስለ ማስታወሻ ደብተሯ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ ስለ ቀፋፊው ሀብታም ተብዬ …… ስለ ኢንቱ ስቃይ …… አብዱኬ ስለነገረኝ አዲሱ ስራ ብዙ ብዙ አሰብኩ፡፡ በነጋታው ኢንቱ ወደ ስራ ሄዳ ማስታወሻዋን እስካነበው ጓጓሁ፡፡
በቀጣዩ ቀን ግን ኢንቱ አብራኝ ስለነበር ወደ ስራ የወጣችው ማስታወሻ ደብተሯን ወደ ትምህርት ቤት ወስጄ ማንበብ አልቻልኩም፡፡ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ሰሞኑን የማስታወሻ ደብተሯን ይዛው ትወጣለች፡፡
ለአንድ ሳምንት ያህል ምንም አዲስ ነገር ሳይፈጠር አለፈ፡፡ ከሳምንት በኋላ የኢንቱን የማስታወሻ ደብተር ማንም በሌለበት በቦታው አገኘሁት፡፡ ደቂቃ ሳላባክን በመርፌ ቁልፍ ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ፡፡
‹‹ኢቦዬ ሴት መሆን ፈተና ነው፡፡ ቆንጆ ስትሆን ደግሞ እሳት ነው፡፡ አላፊ አግዳሚው ሁሉ ወይ በምላሱ ወይ በአይኑ ከተመቸውም በእጁ ይነካካሀል፡፡ ስራ ቦታህ ላይ እንደሰራተኛ ብቻ አትታይም፡፡ እንደ ሰው ብቻ አትቆጠርም፡፡ ሴት ከሆንክ ዳሌህ ነህ … ጡትህ ነህ …… ከንፈርህ ነህ …… የሰውነት ቅርፅህ ነህ! አዎ ነብስህን ሳይሆን ገላህን ለመቀራመት ሁሉም ያኮበኩባል፡፡ ኢንቲሳር ሲባል ያቺ ቅርጿ የሚያምረው …… ከንፈሯ የሚስበው …… ቂጧ እንዲየሆነው ምናምን እየተባልክ በገላህ ትለካለህ፡፡ ዛሬ የስራ ቦታው ጫና ሲበዛብኝ ወደ መስጂድ ሄድኩ፡፡ የሚያግዙኝ ነገር ካለ ብዬ አንድም ቀን ሰግጄ ወደማላውቅበት መስጂድ ሄድኩ፡፡ የሴቶች መስጂድ ውስጥ ማንም አልነበረም፡፡ የሰላት ሰዓት ሲደርስም ከአስር የዘለለ ሴት አላየሁም፡፡ እነርሱም ቢሆን ልብሴ ሰውነቴ ላይ ልክክ ያለ ስለነበር ሁሉም እየገላመጡኝ የማናግረው ሰው አጥቼ ወጣሁ፡፡ የአጋጣሚ ነገር ሆኖ ከመስጂድ ስወጣ በወንዶቹ በኩል ሁለት ሴቶች ‹‹ኢማሙ ወጡ!›› ተባብለው ወደ አንድ ጠና ያሉ ሰው ሲሽቀዳደሙ ተመለከትኩ፡፡ ቀስ ብዬ ተከተልኳቸው፡፡ ሰውዬው በእርጋታ ሁለቱን ሴቶች ያደምጣሉ፡፡ ምን እንዳወሩ ባልሰማም አይናቸው እንባ ሞልቶ በአማኢማቸው ሲያብሱ አየሁ፡፡ ሴቶቹ እንደሄዱ አስቁሜ አወራኋቸው፡፡እያለቀስኩ ስለ አባዬ እና እኛ ስላለንበት ሁኔታ ነገርኳቸው፡፡ በድጋሚ አለቀሱ፡፡ ምን እንዳሉኝ ታውቃለህ? ‹‹እኔ ከኢማምነቴ
977 views06:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 23:09:29
መብሩክ


ማሻአላህ

እኛንም አደራ
1.0K views20:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 23:08:06
መብሩክ በሏቸው


ኢላሂዬ እኛንም ወፍቀን
961 views20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 23:04:34
መብሩክ በሏቸው


ያረብ እኛንም
935 views20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 23:01:02 …… ታምነኛለህ? …… አብረን እንድንተኛ ጠየቀኝ፡፡ ትልቅ ሰው እኮ ነው፡፡ አልቅሼ ለመንኩት፡፡ እሺ ልሳምሽ አለኝ፡፡ ያኔ አባ ሳይታመም በፊት ከኛ ቤት አይጠፋም ነበር! እኔን የምታህል ልጅ አለችው፡፡ እንደውም አንዳንዴ እኛ ቤት ይዟት ይመጣ ነበር፡፡ አስታወስከው? እኔ በጣም ለመንኩት፡፡ ጓደኛህ ሲሞት ዝም ብለህ ታያለህ ወይ ብዬ ተለማመጥኩት፡፡ ባቀረበልኝ አማራጭ ካልተስማማሁ ቢሮውን ለቅቄ እንድወጣ ጮኸብኝ፡፡ ኢቦዬ …… አማራጭ አልነበረኝም፡፡ አባዬ ከሚቃጠል የኔ ክብር ቢረክስ አይሻልም? እሺ አልኩት፡፡ ሰውየው ጨካኝ ነው፡፡ አውሬ! ሲስመኝ እንዴት እንደቀፈፈኝ አትጠይቀኝ፡፡ ይህን ሁሉ አድርጎ ሶስት ሺህ ብር ብቻ ሰጥቶኝ፤ አብሬው ለመተኛት ካልሆነ በቀር ድጋሚ እንዳልመጣ አስጠንቅቆ አባረረኝ፡፡ ኢቦዬ ልቤ ተሰብሯል፡፡ ሰው እንደዚህ አውሬ መሆን ይችላል እንዴ? የታመመ ጓደኛህን ልጅ? ምን አይነት ስብዕና ነው? መንገድ ላይ ስመጣ የሚያየኝ ሁላ የሚያውቅብኝ እየመሰለኝ ስሸማቀቅ ነበር፡፡ አሁንም ቤት ስገባ እንዳታውቁብኝ ለቅሶዬን ጨርሼ ልግባ ብዬ ነው መፃፍ የጀመርኩት፡፡››
ሰውነቴ እየተንዘፈዘፈ ነበር፡፡ ቀጣዩን ማንበብ አቃተኝ፡፡ ኢንቱ ያለችውን ሰውዬ አውቄዋለሁ፡፡ ለጥቂት ደቂቃ ካነባሁ በኋላ ቀጣዩን ገፅ ለማንበብ ስገልፅ በር ላይ የእናቴን ድምፅ ሰማሁ፡፡ ቶሎ ብዬ ደብተሩን ዘጋሁና ቀድሞ ወደነበረበት ቦታ መለስኩት፡፡
እማዬ ከኢንቱ ጋር ነበር የገባችው፡፡ ኢንቱ ስራ አለመሄዷ ግራ አጋባኝ፡፡
‹‹እንዴ ኢቦ …… ዛሬ ላይብረሪ አልሄድክም እንዴ?››
‹‹አዎ ዛሬ ልረፍ ብዬ እኮ ……›› ቀረብ ብላ አየችኝ፡፡ አገጬን በቀኝ እጇ አቃንታ አይኔ ላይ አፈጠጠች፡፡
‹‹አልቅሰሀል አይደል? …… ምን ሆነህ ነው?!››
‹‹አላለቀስኩም እኮ አይኔ ውስጥ ትንኝ ገብታብኝ ነው፡፡ እሱ አቃጥሎኝ ነው አይኔ የቀላው! ወጥታለች፡፡›› አላመነችኝም፡፡
‹‹ምሳ አልበላህም እንዴ? …… ምን የሚያስፈልግ ነገር አለ ትምህርት ቤት?›› አጠገቤ ተቀምጣ እያቀፈች ጠየቀችኝ፡፡
‹‹እኔ እኮ ህፃን አይደለሁም …… ራበኝ ብዬ የማለቅሰው! እሱን ተይውና …… ዛሬ እንዴት ስራ አልገባሽም?››
‹‹ስራ እረፍት ወጥቼ ነው፡፡ እማዬ ብቻዋን እንዳትሆን!›› ተነስታ ቤቱን ማስተካከል ጀመረች፡፡
‹‹ከመች ጀምሮ ነው እረፍት መውጣት የጀመርሽው ባክሽ? አሁንም አስራ ሁለት አመቴ ነው እንዴ የሚመስልሽ?››
‹‹አንተ አትጨቃጨቅ በቃ! ተነስ እንደውም ላይብረሪ ሂድና አጥና!›› አንባረቀችብኝ፡፡ ተነስቼ ወደ በሩ ተንደረደርኩ፡፡ መንገዱን ዘጋችብኝ፡፡ አቀፈችኝ፡፡ ስታቅፈኝ ማልቀስ ጀመርኩ፡፡ ድምጿን ቀንሳ …… ጆሮዬ ላይ ማንሾካሾክ ጀመረች፡፡
‹‹ኢቦዬ እንደ ትንሽ ልጅ አይቼህ አይደለም፡፡ ግን አሁን አንተ ትኩረት እንድታደርግልኝ የምፈልገው ትምህርትህ ላይ ነው፡፡ ማወቅ ያለብህን ጊዜው ሲደርስ ማወቅህ አይቀርም! …… አታስጨንቀኝ እሺ?›› ንዴቴ ከሸፈ፡፡
‹‹ግን እስከመቼ አንቺ ብቻ ስለሁሉም ነገር ትጨነቂያለሽ?››
‹‹አንተ እስክትመረቅ ብቻ! ያኔ እኔንም እማዬንም ያለሀሳብ ታስተዳድረናለህ!››
ከእቅፏ ውስጥ አውጥታ እንባዬን ጠረገችልኝ፡፡ ከቤት ወጥቼ ከራሴ ጋር እየተወዛገብኩ ወደ ቤተል ቤተ-መፅሀፍት ሄድኩ፡፡ ስልኬ ካርድ ስላልነበራት አቤላ ጋር ሚስኮል አደረግኩኝ፡፡ አቤላ የቀራንዮ ሰፈር ልጅ ነው፡፡ ወዲያው ደወለና የቤተ-መፅሀፍቱ ፎቅ ላይ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ ገብቼ መቸከል ጀመርኩ፡፡ እያነበብን እዚያው በአይን ብቻ የማውቃት ልጅ ወደ ጠረጴዛችን መጥታ ከአቤላ ጎን ተቀመጠች፡፡
‹‹እናቱ ሰው አለው ምናምን ብለሽ አትጠይቂም እንዴ?›› አቤል የማያውቀው ሰው ከአጠገቡ ሲቀመጥ አይወድም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰው አለው እያለ ሲመልስ አይቻለሁ፡፡
ልጅቷ ፈገግ ለማለት ሞከረች፡፡ ‹‹አይ ቦታ አለኝ …… አንዴ እሱን አናግሬ ልሄድ ነው፡፡›› ወደ እኔ ነበር የጠቆመችው፡፡
‹‹ይቅርታ እንተዋወቅ ማህሌት እባላለሁ፡፡›› እጇን ዘረጋችልኝ፡፡ ጨበጥኳትና ‹‹ኢብራሂም›› አልኳት፡፡
‹‹okay Can I call you አብርሽ? Alright …… ካላስቸገርኩህ ይህቺን እንድታሰራኝ ፈልጌ ነበር፡፡›› ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠችውን ወረቀት ወደኔ ገፋችው፡፡
‹‹በራስሽ አትሰሪም እንዴ! ያንቺን ሲሰራ ሰዓት እና ኢነርጂ ያባክናል እኮ! እሱ ምን ይጠቀማል?›› አቤላ ከዚህ ቀደም እንዳስረዳቸው ብለው የሚመጡ ልጆች ላይ እንዲህ ሲሆን አይቼው አላውቅም፡፡ ከአጠገቡ ስለተቀመጠች ደብሮት እንደሆነ ገመትኩ፡፡ ከኔ አጠገብ እንድትቀመጥ ወንበሩን ሳብኩላት፡፡ በአቤላ በኩል ዞራ ከጎኔ ተቀመጠች፡፡ ሽቶዋ ጥሩ መዓዛ አለው ግን ደግሞ የሰው ትኩረት ስለሚሰርቅ ደስ አላለኝም፡፡ ፊዚክስ ወርክ ሽት ነበር፡፡ ጥያቄዎቹን ሳያቸው የደከሙ የደከሙ ሆኑብኝ! በቀላሉ አስረዳኋት፡፡
እየተሽኮረመመች ‹‹can I get your number …… የከበደኝ ካለ ለመደወል ምናምን? Just if it’s okay›› አለችኝ፡፡ ስልኬን ሰጠኋት፡፡ ድክሞ ቀፎዬን ተቀብላኝ ስልኳን መዘገበችው፡፡ አቤላ ፈገግ አለ፡፡ ልጅቷ ስትሄድ ‹‹አውቀሀታል?›› አለኝ፡፡
‹‹አላውቃትም ያው በአይን እዚሁ ስታጠና ምናምን ……››
‹‹የሆነ ነገር ውረጂ ብትላት ትወርድ ነበር፡፡ የቅባት ልጅ ናት፡፡ መኪና ይዛ ነው የምትመጣው ሁላ!››
‹‹ለምን በፕሌን አትመጣም?! እኔ ምናገባኝ! ለማኝ ለማኝ አትጫወት ባክህ!››
‹‹አባቴ ሞኝ አትሁኚ! እሷ ይኼኔ ስልኩን እቀበለዋሁ አልቀበለውም ምናምን ጭዌ ተወራርዳ ነው፡፡ እሷን የምታስረዳበትን ስንት ፓርት ከቨር ታደርግበት ነበር!››
በውስጤ ብር ብቀበላት ይሻል ነበር እንዴ ብዬ ከራሴ ጋር ሙግት ውስጥ ገባሁ፡፡ ኢንቱዬ ደግ ስሆን በምላሹ ምንም እንዳልፈልግ የነገረችኝን ሳስታውስ እንዳልተሳሳትኩ አረጋገጥኩ፡፡
እያነበብን ሲመሽ አብዱኬ ተከሰተ፡፡ ከአብዱኬ ጋር ተቀምጠን ማህሌት ደወለች፡፡ ቀና ብዬ የተቀመጠችበትን ቦታ ሳስስ ቦርሳዋን ይዛ እየቆመች በጣቷ አንዴ እንድመጣ ጠየቀችኝ፡፡ከወንበሬ ስነሳ ወደ ደረጃው ሄደች፡፡ ተከተልኳት፡፡
.
ይቀጥላል
1.0K views20:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ